Saturday 21 June 2014

የሀዋሳ ከተማ ባለስልጣናት ለሁለት ተከፍለው አመሹ – የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በነገው እለት ሰኔ 15/2006ዓ.ም የሚያካሂደውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ በቅስቀሳ ላይ የነበሩ ከ30 በላይ የፓርቲው አባላት በፖሊስ መታሰራቸውን ተከትሎ የሀዋሳ ከተማ ባለስልጣናትና የከተማው ፍትህ መምሪያ ሐላፊ በተገኙበት የተካሄው ስብሰባ መታሰር አልነበረባቸውም፤አሁንም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መፈታት አለባቸው በሚሉና ማሰራችን ትክክል ነው ከተለቀቁ ነገ ሰልፉን ከማድረግ ወደኋላ አይሉም በሚል ለሁለት ተከፍለው ሲሟገቱ ማምሸታቸውንና በመጨረሻም አቶ መንድሙ ወታንጎ የተባሉት የደህንነት ሀላፊ በተዓምር መፈታት የለባቸውም መፍታት እንኳን ካለብን የሰልፉ ሰዓት ካለፈ ከ6፡00 በኋላ ነው በማለታቸው በእስር ቤት እንዲያድሩ መወሰኑን ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡እንደ ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ገለፃ ከሆነ ወረቀቶች የተበተኑ በመሆኑ ህዝብ ሊመጣ ስለሚችልከፍተኛ ቁጥጥር እንዲደረግ በደህንነት ሃላፊው መታዘዙን አያይዘው ገልፀዋል፡፡10259772_655212097897061_3392444628732776967_n
1511415_655210944563843_5317006338479666664_n
10489779_655072781244326_5432986543854877449_n

0 comments:

Post a Comment