Monday 16 June 2014

የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ አደረገ – ፍኖተ ነፃነት

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ብሔራዊ ምክር ቤት በትላንትናው ዕለት ተሰብስቦ በመኢአድና አንድነት እንዲሁም በዲሲፕሊን ኮሚቴ መመሪያ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ አንድነት ፓርቲና መኢአድ በተፈራረሙት ቅድመ ውህደት መሰረት የጉባኤ ጠሪ አብይ ኮሚቴ አዋቅሯል፡፡ በዚህም መሰረት ጉባኤው ጠሪው 7 አባላት ሲኖሩት ከ 7ቱ አባላት 5ቱ የሁለቱን ጉባኤ ለማመቻቸት የተሰየሙ ናቸው፡፡ እንዲሁም በፓርቲው የዲሲፕሊን ኮሚቴ መመሪያ ላይ ተወያይቶ ማጽደቁን የብሔራዊ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አበበ አካሉ ለፍኖተ ነፃነት ገለጹ፡፡10374919_653041704780767_6415396503762933119_n
10376844_739632452762173_2761724339676231039_n
10457560_739632516095500_7654517645336374807_n

0 comments:

Post a Comment