Monday, 30 June 2014

“እንደ ከሳሾቼ 100 ሺ የማከራየው ቤት የለኝም” ሲሉ አቶ ገብረውሃድ ተናገሩ

መንግስት በሙስና ወንጀል የከሰሳቸው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ የቀድሞዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ እና የሕግ ማስከበር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ገብረ ዋህድ ወልደጊዮርጊስ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት የሰጡ ሲሆን፣ አቶ ገብረውሃድ “በኢትዮጵያቴሌቪዥን 16 ቤት አለው ተብሎ በካሜራ ተቀርፆ መነገሩ የሚያሳዝ ንመሆኑን ፣ እርሳቸው በአዲስአበባ ውስጥ አንዲት ጐጆ እንደሌላቸውና ቢኖራቸው ኖሮ ልጆቻቸው መጠለያ እንደማያጡ ተናግረዋል። ‹‹እንደከሳሾቼ 100,000 የማከራየውቤትየለኝም፤›› በማለት ንጽህናቸውን ለማስረዳት የሞከሩት አቶ አቶ ገብረውሃድ፣ ከሳሾቼ ያሉዋቸውን ሰዎች በስም ከመጥቀስ ተቆጥበዋል። ሪፖርተር እንደዘገበው አቶ ገብረውሃድ...

ዞን ዘጠኞችን የእምነት ክህደት ቃል በኃይል አስፈርመዋቸዋል (ጽዮን ግርማ)

መዝገቦቹ መልሰው ተቀራረቡ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በስድስቱ ጦማሪያንና በሦስቱን ጋዜጠኞች ላይ የፌደራል ፖሊስ የተለያየ ምክንያት እየሰጠ ቀጠሮ የሚያራዝመውን ሁለት መዝገብ አንዴ ሲያቀራርበው መልሶ ደግሞ ሲያራርቀው ቆይቶ አሁን ደግሞ መዝገቦቹን መልሶ አቀራርቧቸዋል፡፡እስረኞቹ ራሳቸውን መከላከል በማይችሉበት ኹኔታ ፖሊስ ያረቀቀውን የእምነት ክህድት ቃል ተገደው እንዲፈርሙ አድርጓቸዋል፡፡ የሦስቱ ብሎገሮች አቤል ዋበላ፣በፍቃዱ ኃይሉና ማኅሌት ፋንታሁን ቀጠሮ ለዛሬ ሰኔ 22 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲቀርቡ የሚል የነበረ ሲኾን ከጠዋት ጀምሮ ችሎቱን ለመታደም የመጣውን ቤተሰብ፣ጓደኞቻቸው፣ጋዜጠኞች፣ዲፕሎማቶችና የወጣቶች ደጋፊዎች በአጠቃላይ ወደ ሦስት መቶ የሚጠጋ ሰው ከችሎት...

ምርጫ ይራዘምን ምን አመጣው? ማንን ይጠቅማል? በግርማ ሰይፉ ማሩ (የፓርላማ አባል)

የሰላማዊ ትግል አማራጮች ብዙ እንደሆኑ የሰላማዊ ትግል መስመር የመረጡ ዜጎች እንደሚረዱት እሙን ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ፅሁፍ ያቀረበው ጄን ሻርፕ ከአንሰታይን ኢንስቲትዩት አንዱ ሲሆን ይህም በህዳር 1998 ወደ አማርኛ ተመልሶዋል፤ እርገጠኛ ነኝ ይህ ፅሁፍ እንዲተረጎም ያደረጉት ሰዎች ድህረ ምረጫ 97 የገጠመንን የሰላማዊ ትግል ክፍተት የተረዱ ናቸው፡፡ አሁን ደግሞ  “የሰላማዊ ትግል 101” በሚል አንድ መፅኃፍ በሰላማዊ ትግል አቀንቃኙ ግርማ ሞገስ ለገበያ ቀርቦዋል፡፡ ይህ መፅሃፍ የቀረበበት ጊዜም ከምርጫ 2007 መቃረብ ጋር ሰናያይዘው ብዙ እንደምንማርበትና ስላማዊ ትግል ፈታኝ መሆኑን የሚያስረዳ ነው፡፡ የሰላማዊ ትግል ያልገባቸው እንደሚሉትም የፈሪዎች መሰመር አይደለም፡፡ በሁለቱም መፅሃፎች...

Why is Ethiopia the second poorest country on the planet? by prof. Alemayehu G. mariam

                                          Recently, a well-known correspondent for one of the major American media outlets stationed in Ethiopia sent me an email grousing about my article urging boycott of Coca Cola in Ethiopia. He wrote, “I’m sorry to be blunt, but I don’t understand the thrust of this article [on boycotting Coca Cola]. You seem...

Sunday, 29 June 2014

የዞን ዘጠኝ ጦማርያን ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ

ኢ.ኤም.ኤፍ – በድረ ገጾች ላይ ሃሳባቸውን በጽሁፍ ሲገልጹ የነበሩ፤ የዞን ዘጠኝ ጦማርያን ማህሌት፣ ኣቤልና በፈቃዱ በተሰጣቸው ቀጠሮ መሰረት ዛሬ እሁድ አራዳ ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር። ሆኖም እንደተለመደው ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸው ለተጨማሪ ምርመራ እንደገና ወደ እስር ቤት ተመልሰዋል። በዚህ አይነት የፍርድ ቤት ምልልስ ወጣት ጦማሪዎቹ ሁለት ወራትን አስቆጥረዋል።ከጦምሪዎቹ መካከል አቤል፣ ማህሌትና በፍቃዱ በፍርድ ቤቱ የተገኙት ከጠበቃቸው ኣመሃ መኮንን ጋር ነበር። የዛሬውን ውሎ ከዘገቡት ድረ ገጾች መካከል ኢትዮ ሪፈረንስ እንዲህ በማለት ዘገባውን አቅርቧል። ጠበቃ አምሃ እንዳሉት ፖሊስ እንደለመደው 28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ጠይቆ የነበረ ሲሆን፣ ዳኛዋ የጠበቆቹን አስተያየት ሳትጠይቅ 14 ቀን ጦማሪዎቹ...