Sunday 31 July 2016

Massive protest held in Gondar city

Tens of thousands marched in Ethiopia’s northwestern city of Gondar on Sunday morning. Residents descended to the city center “piazza” around 9 am. The rally lasted until noontime.

In placards and chants, the protesters denounced what they see as putting Amhara people at a disadvantage. Among the slogans in the protest: 

“Restore the historic border”, “Wolqait is Amhara”, “Qimant and Amhara are one” and “Return the land given to Sudan”. 

The protesters demanded: “Respect for Amhara-ness”, “Amhara is not terrorist”, “Stop mass killing Amhara people” and an end to alleged TPLF dominance in the region.

The protesters also held slogans showing solidarity with Oromo Protests, detained Muslim activists and the ailing politician Habtamu Ayalew.

The government refused to authorize demonstrations planned for last Sunday and today, claiming the city is yet unstable. The protesters went ahead with the protest today anyway.








Saturday 30 July 2016

በአቶ ዮናታን ተስፋዬ ጉዳይ ዐቃቤ ህግ ያዘጋጃቸው ምስክሮች እንዳይሰሙ ፍርድ ቤት አዘዘ


                                                                            ዮናታን ተስፋዬ
የቀድሞ የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ በነበረው በአቶ ዮናታን ተስፋዬ ላይ ዐቃቤ ህግ ያዘጋጃቸው ምስክሮች መሰማት እንደማያስፈልጋቸው ፍርድ ቤቱ ወሰነ። ለብይንም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል።
አቶ ዮናታን ያቀረበውን አዲስ አቤቱታም በጽሑፍ እንዲያስገባ ፍርድ ቤቱ አዟል።
በቂሊንጦ ማረምያ ቤት ሰብአዊ መብቶቻችን ተጥሰዋል ብለው ባለፉት ዘጠኝ ቀናት በረሃብ አድማ ላይ ከነበሩት ዘጠኝ ሰዎች መካከል አንዱ እና የቀድሞ የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ በነበረው አቶ ዩናታን ተስፋዬ ላይ ዐቃቤ ሕግ ቀጥሯቸው የነበሩት ሁለት ምስክሮች እንዳይሰሙ ፍርድ ቤቱ በየነ።
ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።
http://amharic.voanews.com/pp/3440622/ppt0.html 

የረሃብ አድማ ላይ ያሉት ብርሃኑ ተ/ያሬድ እና ዮናታን ተስፋዬ ፍርድ ቤት ቀረቡ


በቂሊንጦ የሚደርስባቸውን በደል በመቃወም ለ9 ቀን የረሃብ አድማ ያደረጉት እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ እና ዮናታን ተስፋዬ ትላንት ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር። እነ ብርሃኑ (ብርሃኑ ተ/ያሬድ፣ እየሩስ ተስፋው፣ ፍቅረማርያም አስማማው እና ደሴ ካህሳይ) የቅጣት ማቅለያ እንዲያመጡ ነበር የተቀጠሩት።

የተሰጣቸው ቀጠሮ አጭር ስለነበረ እና የእስር ቤቱ አስተደዳደር በሚያደርስባቸው በደል ከቤተሰብ ጋር ባለመገናኘታቸው ማቅለያው ሊደርስላቸው እንዳልቻለ ተናግረዋል። በተጨማሪም አራተኛ ተከሳሽ ደሴ ካህሳይ ቤተሰቦቹ ሩቅ ሃገር በመሆናቸው ከነሱ ጋር ተነጋግሮ ማቅለያ ለማስገባት ጊዜ ስለሚፈልግ ረጅም ቀጠሮ እንዲሰጣቸው ቢጠይቁም ዳኛዋ የተሰጣችሁ ጊዜ በቂ ነው በማለት ከሃምሌ 29 በፊት በቢሮ ማቅለያዎቻቸውን እንዲያስገቡ እና ሃምሌ 29,2008 ፍርድ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥታለች። አቃቢ ህግ የቅጣት አስተያየቱን (ማክበጃ) አስገብቷል።

ብርሃኑ በረሃብ አድማው ምክንያት በመድከሙ ይሰጠው የነበረው ጉልኮስ ጠዋት ወደ ፍርድ ቤት ሲመጣ ነው የተነቀለለት። በዚህም ምክንያት ችሎት ውስጥ መቆም ባለመቻሉ ቁጭ ብሎ ነው የተከታተለው። ዮናታንም በተመሳሳይ ምክንያት ችሎት ውስጥ መቆም አልቻለም ነበር። ዮናታን ተቀጥሮ የነበረው የአቃቤ ህግን የደረጃ ምስክሮች ለመስማት የነበረ ቢሆንም የደረጃ ምስክሮቹ የሚሰጡትን ምስክርነት ዮናታን የሚክደው ስላልሆነ ምስክርነታቸው መሰማቱ ውድቅ ተደርጎ ለሃምሌ 28, 2008 ይከላከል ወይም አይከላከል የሚል ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ተሰጥቷል።

Alarming condition of political prisoners on hunger strike

Political prisoners who were on hunger strike for over a week now have become frail and a wife of one of the prisoners told ESAT that she was worried they were not taken to a hospital.

Aselefech Mulatu, wife of Dejene Tafa said the prisoners were instead given intravenous fluid while still in their isolated dark room.

Prison administrators have kept nine prisoners of conscience separately from others in a dark room saying they were organizing the prison population for a revolt.

Bekele Gerba et al were charged with terrorism by the regime that uses its anti-terror law to stifle dissent and muzzle the press.

Thursday 28 July 2016

Wednesday 27 July 2016

የዜጎችን ሕይወት ለመታደግ አስቸኳይ ጥሪ እናደርጋለን:: ከኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ የተሰጠ መግለጫ


ከሕገመንግስታዊ አግባብ ዉጭ በዜጎች ላይ የሚወሰዱ የመንግስት እርምጃዎች እንዲቆሙ በፓርቲያችንም ሆነ የትግል ጓዶቻችን በሆኑ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሲሰጡ የቆዩ ጋዜጣዊ መግለጫዎችንና ጋዜጣዊ ኮንፌረንሶች እናስታዉሳለን፡፡ በተለይም የዜጎቻችን ከፊንፊኔ ዙሪያ የማፈናቀል ድርጊት እንዲቆም ሲቀርቡ የቆዩ ተማፅኖዎች የመንግስት ባለሥልጣኖች ጆሮ እንዳልገባ አረጋግጠናል፡፡ በሥልጣን ላይ ያለዉ ሥርአት ደጋፊዎች ጥቂት የማይባሉና ከአንድም በላይ ቤት ሲኖራቸዉ በመኖሪያ ቤት እጦት የሚቸገሩ ዜጎች ቁጥር የትየሌለ መሆኑና እነዚህም ዜጎች ከራሳቸዉና ከልጆቻቸዉ ጉሮሮ ቆጥበዉ የሰሩት መጠለያ፤ ለዚያዉም የክረምቱ ጊዜ ከፍተኛ ደረጃ ላይ በደረሰበት ጊዜ ላይ ሲፈርስባቸዉ ማየት ምን ያህል ዘግናኝና አሳዛኝ እንደሆነ መድረክ ከሰጠዉ መግለጫ ለመረዳት ይቻላል፡፡
 
ምንም እንኳን መንግስት ሕግና ሕጋዊነትን የማስከበር ግዴታ ቢኖርበትም፤ ሰርቶ ለአገሪቱ ገቢ እያመጣ ጎጆዉን የሚቀልስ ብቻ ሳይሆን በእንፉቅቅ እየተንቀሳቀሰ ጎሮሮዉን ለሚዘጋ ዜጋ ሳይቀር መንግስት ኃላፊነት እንዳለበት ተዘንግቶ ዜጎች በድቅድቅ ጨለማ ክረምት ሜዳ ላይ መጣላቸዉ አሳዝኖናል፡፡

ቀደም ሲልም በልማትና እንቬስትመንት ስም በተለይም በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ስም ሁሉንም ዜጎች ተጠቃሚ የማያደርገዉንና በፊንፊኔ ዙሪያ የሚገኙ የኦሮሞ ሕዝብን ከቀዬያቸዉ የሚያፈናቅል ልማት ተብዬ እንቅስቃሴ እንዲቆም የኦሮሞ ሕዝብና የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ ከ2006 ጀምሮ በመቃወማችን በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ መንግስት በተወሰደዉ የኃይል እርምጃ 74 ዜጎች ተገድለዋል፡፡ በዚህ በ2008፤ በተለይም ከስምንት ወራት ወዲህ መንግስት ከሕዝብ ፍላጎት ዉጭ ጥቂቶች የሥርአቱ ደጋፊዎችን ብቻ ተጠቃሚ የሚያደርገዉን፤ ነገር ግን መላዉ የኢትዮጵያ ሕዝቦች፤ በተለይም የኦሮሚያ ክልል ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ የተቃወመዉን የሕዝብን ድምፅ እንደመስማት በማን አለብኝነት በወሰደዉ ያልተገባ እርምጃ እስካሁን ከ400 በላይ የኦሮሞ ዜጎች በመንግስት ኃይሎች ተገድለዋል፤ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ታስረዋል፤ ከቀዬያቸዉና ከሥራቸዉ የተፈናቀሉና የተሰደዱ ዜጎች ቁጥር ማወቅ አይቻልም፡፡

በመንግስት ኃይሎች በተወሰደዉ እርምጃ ነፍሰ ጡሮች፣ ዕድሜያቸዉ ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ለጋ ወጣቶች፣ ምሁራን፣ እናቶችና አዛዉንቶች ተገድለዋል፡፡ በቅርቡ እንኳን በምዕራብ ሸዋ ዞን በግንጪና በእጃጂ ወረዳዎች እንዲሁም በምስራቅ ሐረርጌ ዞን በጉራዋና ሐረማያ ወረዳዎች ታዳጊ ወጣቶች የሆኑ ተማሪ እሸቱ ወርቁ ሞረዳ፣ ተማሪ ታረቀኝ ላቺሳ፣ ተማሪ ሣብሪና አብደላ እና ተማሪ ሪሐና አህመድ የተባሉት ራሳቸዉን በኦሮሞ ሕዝብ ጠላትነት በፈረጁ የመንግስት ኃይሎች ተገድለዋል፡፡ የእነዚህ ለጋ ወጣቶች ሕይወት መቀጠፍ የሚፈጥረዉን ስሜት ምን ሊመስል እንደሚችል የወላድ አንጀት ይፍረድ ከማለት ባለፈ ምንም ሊባልአይቻልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝቦችም ሆኑ የዓለም ሕብረተሰብ እንደሚመሰክረዉ የኦሮሞ ሕዝብ በበቀል ስሜት ተነሳስቶ በአንዳችም የሌላ ብሔር ዜጎች ላይ ግድያ መፈጸም ቀርቶ ያሳየዉ የጥላቻ እርምጃ እስካሁን አልነበረም፡፡ ይህ ደግሞ የኦሮሞ ሕዝብን አርቆ አስተዋይነት ከማሳየቱም በላይ፤ ላቅ ባለ ደረጃ ደግሞ የኦሮሞ ሕዝብ ትግል ከአፋኝ ሥርአት ጋር እንጂ ከጠባብ ፍላጎት ያልመነጨና ከንፁኃን ዜጎች ጋር አንዳች ቅራኔ እንደሌለዉ ያሳያል፡፡

ዛሬ በመቶዎች የሚቆጠሩ የኦፌኮ አባላትና ደጋፊዎች እንዲሁም የኢህአዴግን አገዛዝ የተቃወሙ የኦሮሞ ዘጎች በየእስር ቤቶች ታጉረዉ መገኘታቸዉ የሚታወቅ ሲሆን፤ ከነዚህ ዉስጥም አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ አቶ ጉርሜሳ አያኖ፣ አቶ አዲሱ ቡላላ፣ እነዮናታን ተስፋዬ፣ በረሃብ አድማ ላይ ናቸዉ፡፡ እነዚህ ዜጎች ያለ ወንጀል የታሰሩ መሆኑ እየታወቀም ቢሆንም፤ ነገር ግን በፍርድ ቤት የተያዘ ጉዳይ ስለሆነ ቤተሰቦች፣ የትግል ጓዶችና ወገኖች ዉሳኔዉን እየተጠባበቁ ይገኛሉ፡፡ ታሳሪዎቹ ወገኖቻችን በታሰሩበት ቦታ ላይ የሚደርስባቸዉን የሰብአዊ መብት ረገጣ በመቃወም ለፍትሕ አካል ያቀረቡት አቤቱታ ሰሚ በማጣቱ በራሳቸዉ ላይ የወሰዱት ቀጣይ የተቃዉሞ እርምጃ እንጂ የቅንጦት አይደለም፡፡

እነዚህም ሆኑ ሌሎች ዜጎች ፍትሕ የማግኘት መብታቸዉ እንደተጠበቀ ሆኖ፤ አቤቱታቸዉ እንዲሰማላቸዉ በራሳቸዉ ላይ በወሰዱት የምግብ አለመመገብ አድማ መሞት የለባቸዉም፡፡ የሕክምናና የነፍስ ማዳን ዕርዳታ ሊደርግላቸዉ ይገባል፡፡ እነዚህ ዜጎች በእንክብካቤ እጦት ቢሞቱ ዉሎ አድሮ የሚያስከትለዉ ጉዳት ቀላል እንደማይሆን ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡ ስለሆነም የኢትዮጵያ ሕዝቦች፣ የኢፌዲሪ መንግስት፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የሰብአዊ መብት ተከታታዮችና የዓለም ሕብረተሰብ በተለይም በአገር ዉስጥም ሆነ ከአገር ዉጭ የሚትገኙ ዜጎች ይህንን የይድረሱልን ጥሪያችንን በመቀበል የእነዚህ ንፁኃን ዜጎች ሕይወት ከሞት አፋፍ እንዲያተርፉልን የበኩላችሁን ድጋፍ እንዲታደርጉልን በእግዚአብሔርና በኢትዮጵያ ሕዝብ ስም እንማፀናለን፡፡

በመብት ረገጣና እንግልት የሕዝቦች የመብትና የነፃነት ትግል አይገታም!

የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ
ሐምሌ 20 ቀን 2008
ፊንፊኔ


Regime forces arresting protesters in West Arsi, Oromo region of Ethiopia

Special Forces of the TPLF regime, locally known as Agazi, were on Tuesday going door to door in towns in West Arsi, Oromo region arresting people suspected of taking part in protests that reignited this week.

The Oromo regional administration meanwhile said one woman was killed and five others were injured in the protest that has also resumed in East Hararge.

Tensions were high in the West Arsi towns of Dodola, Adaba, and Asasa where there was high presence of federal forces.

Security forces killed at least 400 protesters in the last eight months of uprising in the Oromo region. Tens of thousands people have been detained without due process of law.

Tuesday 26 July 2016

ይድረስ ለኢትዮጵያ ሕዝብ! (የጎንደር ሕብረት መግለጫ)

የትግራይ ነጻ አዉጭ ግንባር በጎንደር የከፈተዉ የዕብሪት ጦርነት የኢትዮጵያን ሕዝብ በባርነት ለመግዛት ያለመዉ ቅጀት ነዉ
በቅድሚያ፤ የፍርሃት ጨለማን ደፍረዉ የባንዳ አጋዚ አፋኞችን ዘርረዉ መስዋዕትነት ከፍለዉ ክብር ላላበሱን የጎንደር ኢትዮጵያዊ ሰማዕታት ጀግኖችን ስም እንዘክራለን፦

ጀግና አቶ ሲሳይ ታከለ
ጀግና አቶ ሰጠኝ ባብል ከበደ
ጀግና አቶ ደሳለኝ
ጀግና አቶ ጌታዉ ጎዳናዉ አምዴ

ሌሎችም ስማቸዉን ያላገኘናቸው ጀግኖች ሁሉ ስማቸዉ በጎንደር/በኢትዮጵያ የታሪክ የወርቅ መዝገብ እንደሚሰፍር ስንገልጽ ከፍ ባለ ኩራት ነዉ።

የዛሬዉ መግለጫችን የሚያተኩረዉ የትግራይ ነጻ አዉጭ ዘረኛ ቡድን የሚያካሂደዉን በጎንደር ክፍለሃገር የተፈጸመዉን አፈና ለመቋቋም የህብረት ተሳትፎ ጥሪያችን ለማስተላለፍ የታሰበ ነዉ። መላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደሚያዉቀዉ፤ የወልቃይት ጠገዴን/ጠለምት ህዝብ የ30 ዓመታት የዘር ማጥፋትና ማጽዳት ግፍ ተፈጽሞበታል። በተመሳሳይ መልኩ በሌሎችም የኢትዮጵያ ምድር ያሉ ዜጎች ሁሉ የወያኔ እስረኛ ከሆኑ 25 ዓመታት ተቆጥሯል።

በወለጋ፤ በጋምቤላ፤ በአፋር የመሬት ቅርምት ሰለባ የሆኑ ወገኖቻችን፤ በአዲስ አበበባና አካባቢዊ ቤታቸዉ ፈርሶ ሜዳ ላይ ዝናብ እየወረደባቸው የተበተኑና ስደተኛ የሆኑት፤በሃረር ፤በጎንጎፋl በኤሊባቡር በአሪሲ፤ በባሌ፤ በሃረር ፤ በኡጋዴን፤ በትግራይ፤ በጎጃም መተከል በወያኔ አጋዚ የሚገደለዉ፤ የሚታሰረዉ ፤የሚሰደደዉ በአጠቃላይ ኢትዮጵያዊያን የተዋረዱበት ዘመን ቢኖር በወያኔ ዝመን ነው።
[ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]


Monday 25 July 2016

በምእራብ አርሲ ህዝባዊ አመጽ እንደገና አገረሸ

የአካባቢው ነዋሪዎች መብታችን ይከበር፣ የታሰሩ ዜጎች በአስቸኳይ ይፈቱ፣ ለአነሳናቸው የፍትህ ጥያቄዎች አፋጣኝ መልስ ይሰጠን፣ በወያኔ መተዳደር አንፈልግም የሚሉና ሌሎችንም ጥያቄዎች በማንሳት ተቃውአቸውን አሰምተዋል።

በዳባ፣ ዶዶላ፣ ኢዶ በሚባሉ ከተሞች ከፍተኛ ተቃውሞ ሲካሄድ የዋለ ሲሆን፣ በአካባቢው የሚገኙ መንገዶች ሙሉ በሙሉ በድንጋይ ተዘግተው ውለዋል። በተለይ ከሻሸመኔ ወደ ባሌ የሚወስደው መንገድ መዘጋት መኪኖች ቀኑን ሙሉ ቆመው እንዲውሉ አድርጓቸዋል።

የታጠቁ የፌደራል ፖሊስ አባላት ወደ አካባቢው በመሄድና ጥይቶችን በመተኮስ ሰልፎችን ለመበተን የሞከሩ ሲሆን፣ ስለደረሰው ጉዳት ለማወቅ አልተቻለም



Saturday 23 July 2016

በጨለማ ቤት የሚገኙ የህሊና እስረኞች በቂሊንጦ እስር ቤት የረሃብ ኣድማ ላይ ናቸው

በቂሊንጦ እስርቤት "እስረኛ እያሳመፃችሁ ነው" ተብለው ከሌሎች እስረኞች ተለይተው በጨለማ ቤት የሚገኙ የህሊና እስረኞች በቀለ ገርባ፣  ፍቅረማርያም አስማማው፣  ብርሃኑ ተ/ያሬድ፣ ዮናታን ተስፋዬ፣ አበበ ኡርጌሳ ማስረሻ ታፈረ ደጀኔ ጣፋ፣ ጉርሜሳ አያና  እና አዲሱ ቡላላ ካለፈው እሮብ ጀምሮ የረሃብ አድማ ላይ ናቸው።

እነ አቶ በቀለ ገርባ እና እነ ብርሀኑ ተክለያሬድ ሐምሌ 13 የጀመሩት የረኀብ አድማ 4ኛ ቀኑን ያስቆጠረ ሲሆን የፖለቲካ እስረኞቹ ሕይወት አስጊ ደረጃ ላይ መድረሱን ቤተሰቦቻቸው  ገልጸዋል።

ከ9 በላይ የሆኑት እና በቂሊንጦ የሚገኙት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በጨለማ ቤት ሆነው ባለ5 ነጥብ ጥሪ አስተላልፈዋል::
ይህን መስዋዕትነት የሚከፍሉት ለሕዝብ ነውና ሕዝቡ ከጎናቸው እንዲቆም ቤተሰቦቻቸው ጥሪ አቀርበዋል።

Two Ethiopians try self-immolation in Cairo

Two Ethiopians tried self-immolation at the headquarters of the UNHCR in Cairo, Egypt after the office refused their request for immigration to a third country.

The two Ethiopians came to Egypt escaping from the cruel hands of Ethiopian regime forces cracking down on ongoing uprising in the Oromo region.

Police and other Ethiopians at the scene stop the two from killing themselves but video obtained by the Oromo Media Network show one of them with severe burn to his body.

The UN Agency recently rejected a request by hundreds of Ethiopians for an immigration to a third country. Most of the immigrants run away from the Oromo region of Ethiopia where security forces are unleashing deadly force against students who have been protesting against the tyrannical regime.
Hundreds of Ethiopians die in the high seas of the Mediterranean while trying to cross to Europe as the UN agency refuse to recognize them as legitimate immigrants who fled persecution in their home country.

The condition of the two individuals is not known but reports say they have sustained serious burn to their bodies.


በኢትዮጵያ የሚደረጉ ህዝባዊ ተቃውሞዎች ከቁጥጥር ውጭ ሊሆኑ ይችላሉ ተባለ

በኢትዮጵያ ለበርካታ ሰዎች ሞት ምክንያት የሆኑ እና በተለያዩ ክልሎች በመካሄድ ላይ ያሉ ህዝባዊ ተቃውሞዎች በሂደት ከቁጥጥር ውጭ ሊሆኑ እንደሚችሉ አንድ አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም አርብ አሳሰበ።

መቀመጫውን በአሜሪካ ያደረገውና በሃገሪቱ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታዎችን ዙሪያ ሪፖርቱን ያወጣው ፍሪደም ሃውስ፣ መንግስት በብቸኝነት ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ቁጥጥርን ተግባራዊ ማድረጉ ተቃውሞዎች እንዲቀሰቀሱና እየተባባሱ እንዲሄድ ምክንያት መሆኑን አስታውቋል።

ለወራት በኦሮሚያ ክልል ሲካሄድ የቆየው ህዝባዊ ተቃውሞ ወደ አማራና የደቡብ ክልል መዛመቱን ያወሳው ድርጅቱ፣ መንግስት ድርጊቱን ለመቆጣጠር እየወሰደ ያለው እርምጃ በሃገሪቱ ያለውን ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት አደጋ ውስጥ እንደከተተው ገልጿል።

በስልጣን ላይ ያለው ገዢው የኢህአዴግ መንግስት አማራጭ የሆኑ የፖለቲካ አመለካከቶች እንዳይበራከቱ ለማድረግ እየወሰደ ያለው አፈናና ቁጥጥር በርካታ ሰዎች ለተቃውሞ አደባባይ እንዲወጡ ምክንያት ሆኖ መገኘቱን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋሙ አስታውቋል።


በሃገሪቱ በተደጋጋሚ በመካሄድ ላይ ያሉት እነዚሁ ህዝባዊ ተቃውሞዎች በሂደት ከቁጥጥር ውጭ ሊሆኑ እንደሚችል በፍሪደም ሃውስ የአፍሪካ ፕሮግራም ሃላፊ የሆኑት ጄኒፈር ቻሬቲ በኢትዮጵያ ስላለው የፖለቲካ ሁኔታ ባሰፈሩት ጽሁፍ አሳስበዋል።
ገዢው የኢህአዴግ መንግስት የፓርላማ መቀመጫን በብቸኝነት እንዳሸነፈ ካሳወቀ ከስድስት ወር በኋላ ሃገሪቱ በመካሄድ ላይ ያሉት እንደዚሁ ህዝባዊ ተቃውሞዎች በአጠቃላይ ለሃገሪቱ የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ስጋት እየሆኑ መምጣታቸውን ሃላፊዋ ገልጸዋል።


ከህዝብ ለሚነሱ የተለያዩ ፖለቲካዊና የብሄር ጥያቄዎች ምላሽን የማይሰጥ መንግስት ዘላቂ ልማትን ሊያካሄድ አይችልም ሲሉ ያስታወቁት ጀኒፈር ቻሪቴ በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውን ተቃውሞ ተከትሎ በርካታ ሰዎች ለእስር መዳረጋቸውን አመልክቷል። በቅርቡ ተመሳሳይ ሪፖርትን አውጥቶ የነበረው ሂውማን ራይትስ ዎች በክልሉ ለወራት ከዘለቀው ተቃውሞ ጋር በተገናኘ ወደ 400 ሰዎች አካባቢ በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች መገደላቸው ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።


መንግስት በሃገሪቱ ባሉ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ላይ ጠንካራ እርምጃዎችን እየወሰደ ቢገኝም በርካታ ኢትዮጵያውያን ተቋማቱ በሰብዓዊ መብትና በዴሞክራሲ እድገት ላይ አስተዋጽዖ እንዳላቸው ማንነታቸው ሊያረጋግጥ መቻሉን ፍሪደም ሃውስ ያካሄደውን ጥናት ዋቢ በማድረግ በሪፖርቱ አስፍሯል።


ኢሳት

Thursday 21 July 2016

People of Borena, south Ethiopia stage protest rally

People in Borena, Oromo region in south Ethiopia held a demonstration on Thursday denouncing the maladministration, corruption and injustice under a tyrannical regime.

Students and residents of Yabelo town in Borena have also expressed their outrage that they were being administered by incapable, uneducated and corrupt officials directly appointed by the regime in Addis Ababa.

The demonstrators also spoke of lack of infrastructural and educational developments in the area.
They said the town of Moyale and its environs has been administered by two regional governments – the Somali and Oromo regional governments – which they said was the reason for the region to remain underdeveloped.

The eight month old protest in the Oromo region of Ethiopia has gained momentum this week as the people in east and west Hararge, as well as west Shewa held protest rallies in their respective localities of Asebot, Hirna and Jeldu.




Wednesday 20 July 2016

እነ ብርሃኑ ተክለያሬድ ተከላከሉ ተባሉ

አርበኞች ግንቦት 7ትን ሊቀላቀሉ ሲሉ መንገድ ላይ ተይዘዋል በሚል ክስ የተመሰረተባቸው ብርሃኑ ተክለያሬድ ፣ እየሩሳሌም ተስፋው፣ ፍቅረማርያም አስማማው እንዲሁም የግንባሩ አባል ነው የተባለው ደሴ ካሳይ ፍርድ ቤት ቀርበው ጥፋተኞች ተብለዋል፡፡

14ኛው ወንጀል ችሎት ውሳኔውን ያስተላለፈው ተከሳሾች የመከላከያ ምስክሮችን ባላቀረቡበት ሁኔታ ነው። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጨምሮ የተለያዩ ታዋቂ ሰዎችንና የገዢው ፓርቲ ባለስልጣናትን በመከላከያ ምስክርነት ለማቅረብ አስመዝግበው የነበረ ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ ምስክሮቻችሁን አቅርባችሁ ማሰማት አትችሉም ብሎአቸዋል።

ተከሳሾች በጸረ ሽብር አዋጁ አንቀጽ 652/2001 መሰረት ሃምሌ 22 ቀን 2008 ዓም የፍርድ ውሳኔ እንደሚያገኙ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።

ለአቶ በረከት በቅርበት የምትሰራው ጋዜጠኛ ሳምራዊት ስንታየሁ ተሰደደች – የመንግስት ጋዜጠኞች ስርዓቱን ጥለው መኮብለሉን ተያይዘውታል

                                                                 ሳምራዊት ስንታየሁ
(ዘ-ሐበሻ) በታች በኦሮሚያ በኩል በላይ በጎንደር በሕዝብ አመጽ የተወጠረው የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ መንግስት የሚያስዳድረው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኤጀንሲ (የኢትዮጵያ ራድዮና ቴሌቭዥን) በዜና እና በወቅታዊ ዝግጅት ክፍል በምክትል ዋና አዘጋጅነት ስትሰራ የነበረችው ጋዜጠኛ ሳምራዊት ስንታየሁ ሃገሯን ጥላ ተሰደደች።

ለአቶ በረከት ስም ዖን የሚዲያ ሞኒተሪንግ ኢንፎርሜሽን ኤክስፐርት በመሆን ያገለገለችው ጋዜጠኛ ሳምራዊት በተለይ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት የሙያዋ ስነምግባር የሚያዛትን የሕዝቡን ብሶትና ወቅታዊ ጉዳዮችን ጨምሮ በኢትዮጵያ የተከሰተውን ረሀብ የሃገሪቱን መልካም ገጽታ ስለሚያጠፋ በማንኛውም መንገድ ለሕዝብ በሚዲያ መነገር የለበትም በሚል እንዳትዘግብ በሚደርስባት ጫና እና አፈና የተነሳ ስራዋን ለቃ ለመውጣት እንደተገደደች የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታውቀዋል።

እንደምንጮች ገለጻ ከሆነ በማንኛውም መንግስታዊ ሚድያ እንዳይዘገብ የተከለከለው በኢትዮጵያ የተከሰተው ረሃብ፤ በኦሮሚያና በጎንደር ሕዝባዊው ቁጣ አይሎ ከወጣ በኋላ የመንግስት ጋዜጠኞች እውነተኛውን የሕዝቡን ብሶትና እየደረሰ ያለውን እውነታ እንዳይዘግቡ ተከልክለዋል። በተለይም የሕዝቡን ተቃውሞ በነፃነት እንዘግብ ብለው የተነሱ ጋዜጠኞች እንደሚገመገሙና ወደ እስር እንደሚወረወሩ የሚመጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ይህ ሕዝባዊ ቁጣ ከተቀሰቀሰ ወዲህ በርከት ያሉ የመንግስት ሚድያ ጋዜጠኞች ሃገራቸውን እየጣሉ እየተሰደዱ ስለመሆኑ ዘ-ሐበሻ መዘግብው አይዘነጋም።

የኢትዮጵያ ራድዮ ቴሌቭዥን በዜና እና ወቅታዊ ዝግጅት ክፍል በምክትል ዋና አዘጋጅነት ስታገለግል የቆችው ጋዜጠኛ ሳምራዊት ተቀማጭነቱ በ እንግሊዝ የሆነ መንግስታዊ ያለሆነ ድርጅት ውስጥም በኮምዩኒኬሽን አስተባባሪነት ታገለግል እንደነበር ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመልክቷል።

ይህ በ እንዲህ እንዳለ በጎንደር የተከሰተውን የሕዝብ አመጽ ተከትሎ የአማራ ክልል መንግስታዊ ጋዜጠኞች በከፍተኛ ጫና ውስጥ እንደሚገኙ ታወቀ። ጋዜጠኞች ስለሕዝባዊው ተቃውሞ እንዳትዘግቡ የሚል ት ዕዛዝ የወረደላቸው ሲሆን መንግስት ከሚያወጣው መግለጫ ውጭ ምንም ዓይነት ዘገባ እንዳይሰሩ ታዘዋል። አንዳንድ ጋዜጠኞች ይህ ሁሉ የሕዝብ አመጽ ተከስቶ ምንም እንዳልተፈጠረ ዝም ማለት አንችልም፤ የሙያ ስነምግባራችንም አይፈቅድልንም በሚል እያግሩረመረሙ እንደሚገኙ ተሰምቷል።

ኢሕአፓ ለጎንደር ሕዝብ ትግል ሙሉ ድጋፉን ያረጋግጣል

ኢሕአፓ የትግል ታሪክ ውስጥ ጎንደርና የጎንደር ሕዝባ ያላቸው ቦታ ከፍተኛ ነው። የጎንደር ሕዝብ ኢሕአፓንም ሌሎች ሀገር ወዳድ ድርጅቶችንም ደግፎ ከፍተኛ መስዋዕትነትን ከፍሏል። . . . የጎንደር የሰማዕት ታሪክ የኢሕአፓ ታሪክ ማዕክል ሆኖም ቆይቷል። ኢሕአፓ በጎንደር እየተካሄደ ያለውን ጸረ ወያኔ ትግል ሙሉ በሙሉ ይደግፋል። . . . ወቅቱ የመራራና የቆራጥ ትግል ወቅት ነው። ወያኔ ሕዝብን በጅምላ በመፍጀት ትግሉ ለማፈን መጣሩ የሚጠበቅ ነው። በግድ ወደ ትግራይ የተጠቃለለው መሬትና ማንነቱ የተካደውም ሕዝብ ቆርጦ መነሳቱ የሚመሰገን ነው። የአፍራሽና የቅጥረኞች አዞ እንባ ረግጦ ትግልን መቀጠል አስፈላጊ መሆኑን ትግልን ለሚያውቀው የጎንደር ሕዝብ ሊያስተምር የሚቃጣ ሊኖርም አይችልም። ከጎንደር ሕዝብ ጎን በተጨባጭ መቆም ጊዜው አሁን ነው። ሀገርን ማስመለስና ድንበርን ማስከበር፤ ማንነትን ማስረገጥ ለነገ የሚባል ትግል አይደለም። በመሆኑም ኢሕአፓ በአካባቢው ያሉትን አባላትና ደጋፊዎች የትግሉ አካል ሆነው እንዲሰለፉ ጠርቷል። በሰበብ አስባቡም ከወያኔ ጎን ቆመው የነበሩትም በጊዜ ከሕዝብ ጎራ እንዲቀላቀሉም ጥሪ ያደርግላቸዋል። ይህ ጸረ ወያኔ ትግል መጠቃት የለበትምና ሀገር ወዳድ ሀይሎች ሁሉ–በያሉበት–ሊታደጉት፤ ሊረዱት፡ ሊያጠናክሩት መነሳት አለባቸውም ይላል። ሙሉውን መግለጫ ያንብቡ …

Thursday 14 July 2016

አርበኞች ግንቦት 7 ለጎንደር ህዝብ አጋርነቱን እየገለጸ እንደሚገኝ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናገሩ

አርበኞች ግንቦት 7 መስዋዕትነት እየከፈለ ለሚገኘው የጎንደር ህዝብ አጋርነቱን እየገለጸ እንደሚገኝ ሊቀመንበሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናገሩ። የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በምስልና ድምፅ ከኤርትራ ረቡዕ ዕለት ባስተላለፉት መልዕክት የአማራም ህዝብ ሆነ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ አጋርነቱን እንዲያሳይ ጥሪ አቅርበዋል።

የወልቃይት ህዝብ ማንነቱን በተመለከተ በህጋዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ያቀረበው ጥያቄ በህወሃት በኩል የሃይል ምላሽ መሰጠቱ የቀሰቀሰው ተቃውሞ ወደግጭት ማምራቱን በጥሪያቸው ያስታወሱት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ በጎንደር የታየው ህዝባዊ ዕምቢተኝነት በስርዓቱ ሰለባ ለሆኑትና ለውጥ ለሚሹ ሁሉ መነቃቃትን የፈጠረ እንደሆነ አመልክተዋል።

“ከተባበርን አንጸናለን፣ ከተከፋፈልን እንወድቃለን” በማለት ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የአጋርነት ጥሪ ያቀረቡት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ “ዛሬ በጎንደር ከተማ እና አካባቢዋ እየተዋደቁ ካሉ ወገኖቻችን ጎን ካልቆም በህወሃት የሚደርስብን አፈና ማለቂያ አይኖረውም በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለመከላከያና ለፌዴራል ፖሊስ አባላት ለብዓዴን፣ ኦህዴድ፣ ደህዴን እንዲሁም ለህወሃት አባላት ጭምር በገዳዮችና ዘራፊዎች ላይ ተነሱ በማለት ጥሪ አቅርበዋል።
አገዛዙን በመቃወም የሚደረጉ ህዝባዊ እንቅስቃሴዎች የትግራይን ህዝብ ለማጥቃት የተካሄደ በማስመሰል የሚቀርበውን አሳፋሪ ሴራ እንዲያጋልጥም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።


የኦሮሚያና የአማራ ክልል የፖሊስና የሚሊሺያ አባላት ለነበራችውና አሁንም ላላችሁ በጎ ሚና ህዝቡ አክብሮቱን ይሰጣችኋል በማለት ከኤርትራ በምስልና በድምፅ መልዕክት ያስተላለፉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከዚህ ውጭ በወንጀል ተባባሪ የሆኑና በግድያ ተሳታፊ የሆኑ የጸጥታ ሃይሎች በማናቸውም መንገድ ከተጠያቂነት ነጻ እንደማይሆኑ አሳስበዋል።


“በአንድነት ከተነሳት የነጻነት ቀን ቀርባለች” በማለት ወደንግግራቸው ማጠቃለያ የመሩት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ በሁሉም የሃገሪቱ ክልሎች የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች እንደሚገኙ አመልክተው፣ “ስትሞቱ እየሞትን ስትቆስሉ እየቆሰልን፣ ሊገድሏችሁ ያኮበኮቡትን እየታገልን እስከመጨረሻው የድል ምዕራፍ ከውስጣቸው እንደማንለይ ዕወቁት” ሲሉ መልዕክታቸውን አጠቃለዋል።


ኢሳት

Wednesday 13 July 2016

The Revolt in Gondar, Ethiopia continued for the second day

In one of the deadliest days in the town of Gondar, northern Ethiopia, six residents and four members of regime forces were killed on Tuesday.Deadliest days in the town of Gondar, northern Ethiopia.

The killings began when TPLF forces from Tigray came to the town of Gondar in the wee hours of the morning on Tuesday and apprehended four members of a committee that spearheads the political demands by the people of Wolkait and Tegede as regards their identity as Amharas. The people of north Gondar have been peacefully demanding the government to recognize them as Amharas and abolish the Tigrayan identity imposed on them by the regime 25 years ago.

The TPLF forces were at the door of the fifth committee member, Col. Demeke Zewde at 5 a.m. on Tuesday when shots were fired as the Colonel refused to surrender to the forces, according to witnesses.Shops and vehicles belonging to the business empire of the regime were set ablaze.

The Colonel returned fire, killing two of the TPLF security operatives, witnesses told ESAT on the phone. Having heard the Colonel was besieged by the forces, residents of Gondar in turn surrounded the TPLF forces resulting in hours of standoff.

The whereabouts of the Colonel is not known but sources told ESAT that the residents had overpowered the TPLF forces and secured the release of the Colonel and took him to safety.

Gunfire was heard all day in Gondar on Tuesday and the regime has been moving the army and security into the town. Witnesses said they saw heavy artillery and convoys of soldiers entering the town.

Having heard the news of the fight, armed people from Armacheho came to Gondar in several buses to defend their compatriots who were under attack by the regime.

Shops and vehicles belonging to the business empire of the regime were set ablaze by the irritated residents, some armed, and who were seen on the street all day chanting anti TPLF slogans.



በጎንደር ህዝባዊ አመጹ ለሁለተኛ ቀን ቀጥሎአል

ትናንት እስከ ምሽቱ አራት ሰአት በተደረገው የተኩስ ልውውጥ በርካታ የህወሃት ታጣቂዎች ተገድለዋል። ጥቃቱን የፈጸሙት የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት ጥያቄ አቅራቢዎችን ለመታደግ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ወደ ጎንደር ከተማ የገቡ ነዋሪዎች ናቸው። በተኩሱ ልውውጥ መሃል ከወልቃይት ጠገዴ ጥያቄ አቅራቢዎች መካከል አቶ ሲሳይ ታከለ፣ አቶ ሰጠኝ፣ አቶ አለቃ እስበሶም እና ሌሎች ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ሰዎችም ሲገደሉ፣ በፌደራል ፖሊስና በህወሃት ደህንነት አባላት በኩል ደግሞ በርካታ ወታደሮች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል። በርካታ ወጣቶች እንደተገደሉም መረጃዎች እየወጡ ነው።

ተቃውሞው ዛሬም የቀጠለ ሲሆን አንድ የህወሃት የንግድ ድርጅትና አንድ የፌደራል ፖሊስ መኪና መቃጠላቸው ታውቋል።
በተጣቂዎች ተከበው የነበሩት ኮ/ል ደመቀ ዘውዱ እርሳቸውን ሊረዱ በመጡ ሰዎች ታግዘው እየተኮሱ ማምለጣቸውን እየተነገረ ነው  ግን በትክክለ ስለማምለጣቸው ማረጋገጥ አልቻለም።


Monday 11 July 2016

ዜጎችን ማፈናቀል መግደልና ማሰደድ የህወሃት አይነተኛ መግለጫዎች ናቸው!!! (አርበኞች ግንቦት 7)

ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ወደ ስልጣን ከመጣበት ጊዜ አንስቶ በአገራችንና በህዝባችን ላይ ሲፈጽም የቆየውና እየፈጸመ ያለው ግፍና ስቃይ ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደልም። አፈና ፣ እስር፣ ግድያና ዜጎችን ማፈናቀል አይነተኛ መግለጫዎቹ የሆነው ይህ የህወሃት አገዛዝ፣ ሰፋፊ የእርሻ መሬቶችንና የከተማ ቦታዎችን በመቸብቸብ ሃብት ለማካበት ባለው ዕቅድ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን እትብታቸው ከተቀበረበት ቀዬና የትውልድ መንደሮቻቸው በግፍ እንዲፈናቀሉ አድርጎአል። አሁንም እያደረገ ነው ።

Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracyሰሞኑን በአዲስ አበባ በንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ቀርሳና ኮንቶማ በተባሉ ቀበሌዎች ከ30 ሺ በላይ የሚገመት ህዝብ ለአመታት ከኖረበት መኖሪያ ቤቶች በሃይል ተገፍትረው በመውጣት ጎዳና ላይ እንዲበተኑ ተደርጎአል። በዚህም እርምጃ ምክንያት አቅመደካማ የሆኑ አዛውንቶች፤ ነፍሰጡሮችና ከወለዱ ገና ሳምንታት ያልሞላቸው እመጫቶች፤ የሚያጠቡ እናቶች፤ ህጻናትና ለጋ ወጣቶች ለከፋ ችግር ተዳርገው ለቅሶና ዋይታ በማሰማት ላይ ናቸው ። በስንት ልፋትና ድካም ከሰሩዋቸው ቤቶች ተለዋጭ ቦታ ሳይሰጠን ወይም ካሳ ሳይከፈለን አንወጣም በማለት ለማንገራገር የሞከሩ 10 ሰዎች በፖሊስ ጥይት ተገደለዋል፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ደግሞ ለእስር ተዳርገዋል።

ህወሃት እንዲህ አይነት የጭካኔ እርምጃ እየወሰደ ያለው በክፍለ ከተማው የሰፈሩት ሰዎች “ህገወጦች ናቸው” በሚል ሰበብ ነው። ትናንት ባዶ እግራቸውን ነፍጥ አንግበው ቤተመንግሥቱን የተቆጣጠሩና ጄሌዎቻቸው ከመሃል ከተማው ዜጎችን እያፈናቀሉ ቪላና ሰማይ ጠቀስ ፎቆች ሲገነቡ ህገወጥ ያልተባሉት ሰዎች፣ አረብ አገር ድረስ ተጉዘው በግርድና ሥራ ሳይቀር በመሥራት ባገኙት ገንዘብ በአገራቸው መሬት ላይ ጎጆ የቀለሱ ለምንድነው ህገወጥ የሚባሉት የሚለውን ለታሪክ ፍርድ እንተወውና እነዚህ ህገወጥ የተባሉ ሰዎች በመንግሥት ይዞታ ሥር ካሉ የአገልግሎት ድርጅቶች ጋር ተዋውለው መብራትና ውሃ አስገብተው ሲጠቀሙ መኖራቸው ፤ ገንዘብ በማዋጣት መንገድ ፤ ጤና ጣቢያዎችንና ትምህርት ቤቶችን በከተማው አስተዳደር ድጋፍ ማስገነባታቸው ፤ የህወሃት የንግድ ድርጅቶች በሚሊዮኖች የሚቆጠር ትርፍ ለሚዝቁበት የአባይ ግድብ ቦንድ በየመኖሪያቤታቸው ቁጥር ሲሸጥላቸው የነበረና የምዕራቡን አለም ለማደናገር በየአምስት አመቱ የሚደረገውን የምርጫ ድራማ ለማድመቅ በግዳጅ እንዲመዘገቡና ድምጽ እንዲሰጡ ሲደረጉ መቆየታቸው ብቻውን አገዛዙ ሲመቸው እውቅና ሰጪ ሳይመቸው ደግሞ እውቅና ነሺ መሆኑን የሚያሳይ፣ ለፍትህና ለርእትዕ የማይሰራ የዘራፊዎች ቡድን በመሆኑ፣ የድሆችን ቤቶች ለማፍረስ የወሰደው እርምጃ በየትኛውም መስፈረት ተቀባይነት የሌለው ህገወጥ ድርጊት ነው። ለነገሩ ህገወጥ ከሆነ ቡድን ህጋዊነትን መጠበቅ አይቻልምና ወያኔ በህግ ሽፋን የሚወስዳቸው እርምጃዎች ሁሉ ህገወጥነታቸውን አይለውጠውም።

አባቶቻችን አገራቸውን ከባዕድ ወረራ ለመከላከል ደማቸውን ያፈሰሱትና አጥንታቸውን የከሰከሱ መጪው ትውልድ በአገሪቱ አንገት ማስገቢያ ጎጆ እንዲኖረው በማሰብ እንጅ፣ በደምና በአጥንት የተገዛው መሬት ለውጭ አገር ዜጎች እንዲቸበቸብ ወይም በመንግስት ስም የተደራጁ ሽፍቶች እንዲዘርፉት አልነበረም።

ሌላው አስገራሚና አሳዛኙ ነገር እንዲህ አይነት ሰቆቃ የተፈጸመባቸውና በዚህ ክረምት ወቅት ቤቶቻቸው ፈርሶና ንብረቶቻቸው ወድሞ ወደ ፍጹም ድህነት እንዲገቡ በተደረጉት ዜጎች መሬት ላይ ፣ ህወሃት ኮንዶሚኒዬሞችን ገንብቶ ለዲያስፖራ ለመቸብቸብ ዕቅድ ያለው መሆኑ ነው ። ዲያስፖራው አገዛዙ በወገኖቹ ላይ የሚፈጽማቸውን ሰቆቃና ግድያ በማጋለጥ ሥራ ላይ በመጠመዱ የህወሃት መሪዎች እረፍት አጥተዋል። በተለይ ከምርጫ 97 ወዲህ አጋዚ የተባለው ሃይል በሰብአዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል የቀን ጉዳይ ካልሆነ በቀር በአለም አቀፍ ወንጀል እንደሚያስጠይቅ ወያኔ ይረዳል። ይህንን ስጋት ለማስቆም የዲያስፖራን እንቅስቃሴ ማዳከም እንደስትራቴጂ ነድፎ መንቀሳቀስ የጀመረው የነ ቴዎድሮስ አድሃኖም አገዛዝ፣ ዲያስፖራውን በጥቅም በመከፋፈል ስጋቱ ይቀነሳል ብሎ ያምናል። ከዚህም በተጨማሪ አገር ውስጥ የሚደረገውን አልገዛም ባይነት ትግል ለማጠናከር የዲያስፖራው እምቅ ሃይል የሚፈጥረውን ተአምር ህወሃት አውቆታል። ላፍቶ ክፈለ ከተማ 40 በ60 በተባለው ፕሮጄክት የኮንዶሚኒዬም ባለቤት በመሆን የአገራቸውንና የወገኖቻቸውን ስቃይ ለማራዘም ላኮበኮቡ የዲያስፖራ አባላት እየተመቻቸች ያለ ሰፈር ነው። ከውስጧ እየተሰማ ያለው ለቅሶና ዋይታ የማይቆረቁራቸው ፤ ኮንዶሚኒዬም ቤት የሚያማልላቸው ዲያስፖራዎች አይኖሩም አይባልም።

አርበኞች ግንቦት 7 የህወሃት አገዛዝ ዜጎችን በመግደልና በማሰር ከቀያቸውና ከመኖሪያቤታቸው በሚያፈናቅለው የከተማም ሆነ የገጠር መሬት ላይ ማንም ሰው በህግ ፊት በዘላቂነት የሚጸና መብት ሊያገኝ ይችላል ብሎ አያምንም። ህወሃት በሚወረውርላቸው የጥቅም ፍርፋሪ የወጎኖቻቸውን ስቃይና መከራ ዕድሜ እያራዘሙ ያሉ ከየማህበረሰቡ የተገዙ ስላሉ በተለመደው ርካሽ ዋጋ በንጽጽር ደህና መኖር እየቻለ ካለው የዲያስፖራ ማህበረሰብ ሰዎችን መሸመት እችላለሁ ብሎ ህወሃት እየተንቀሳቀሰ ነው። በቴዎድሮስ አድሃኖም ጽ/ቤት ተዘጋጅቶ በተግባር እንዲተረጎም በውጪ አገር ባሉ የወያኔ ኤምባሲ ሁሉ የተበተነው የዲያስፖራ ፖሊሲ አላማ ይሄ ነው። ቀርሳና ኮንቶማ በእንዲህ አይነት ርካሽ ጥቅም የሚሸመቱ የዲያስፖራ አባላትን ለማሰባሰብ እየተዘጋጀ ያለ ሰፈር ነው።

አርበኞች ግንቦት 7 የሶስት ቀን አራስ በተገደለችበት፤ በርካታ እናቶች ፤ አቅመደካማ አዛውንቶችና ታዳጊ ህጻናት ተፈናቅለው ለጎዳና ተዳዳሪነት በተዳረጉበት ቦታ ላይ የሚገነባውን ኮንዶሚኒዬም፤ ለተለያዩ አገልግሎት የሚሆኑ ህንጻዎች ወይም ሌላ ኢንቬስትመንት ባለቤት ለመሆን በየዋህነት ያሰፈሰፉ ካሉ ውሳኔያቸውን ቆም ብለው እንዲያጠኑት ይመክራል። ከቤታቸው ተፈናቅለው እንባቸውን እያፈሰሱና በየሜዳው ተበትነው የሚንከራተቱ ወገኖቻችን እንባ ሳይደርቅ ህወሃት ወደ መጨረሻው ከርሰመቃብር ይወርዳል። ይህ ምኞት ሳይሆን የቆምንለትና እየሞትንለት ያለው ትግል ውጤት ነው።

ወያኔ ሃብት ለማካበት በሚያጧጡፈው የመሬት ንግድ የሚፈናቀሉ ወገኖቻችን ህይወት ሁላችንንም ይመለከታል። የአገሪቱን ዜጎች ለጎዳና ተዳዳሪነት በመዳረግ የሚገነቡ አዳዲስ ህንጻዎችና መንገዶች ልማት ሳይሆን ማህበራዊ ቀውስ በመፍጠር ህብረተሰቡን ለከፍተኛ ችግር የሚዳርግ አደጋውም ለአገር የሚተርፍ ነው። አልጠግብ ባይ ጥቂት የህወሃት አመራሮች ህዝባችንን ሲያፈናቅሉትና አገር አልባ ሲያደርጉ ዝም ብሎ መመልከት ችግሩ እንዲባባስና እያንዳንዳችን የጥቃቱ ሰለባ እንዲንሆን መጋበዝ ነው። አርበኞች ግንቦት 7 ይህንን የህወሃት ዜጎችን የማፈናቀል እርምጃ ለማስቆምና በግፍ ለተገደሉ ወገኖቻችን በህግ ለመፋረድ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በያለበት ጸረ ወያኔ ትግሉን እንዲያፏፉምና ትግሉን እንዲቀላቀል ወገናዊ ጥሪውን ያቀርባል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በመከላከያ ምስክርነት ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ሰበር ችሎት አዘዘ

በሽብር ድርጊት ወንጀት ተጠርጥረው በተመሠረተባቸው ክስ እንዲከላከሉ ብይን በተሰጠባቸው በእነ ዘመኑ ካሴ መዝገብ አቶ አሸናፊ አካሉ፣ አቶ ደህናሁን ቤዛ፣ አቶ ምንዳዬ ጥላሁንና አቶ አንሙት የኔዋስ በመከላከያ ምስክርነት የቆጠሯቸው አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ቀርበው እንዲመሰክሩ፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት አዘዘ፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠውን የመጨረሻ ትዕዛዝ መሠረት በማድረግ፣ ክሱን ሲመረምር የከረመው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት፣ ሰኔ 30 ቀን 2008 ዓ.ም. ለፌዴራል ማረሚያ ቤት ባስተላለፈው ትዕዛዝ፣ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት አቶ አንዳርጋቸውን ሐሙስ ሐምሌ 7 ቀን 2008 ዓ.ም. ያቅርብ ብሏል፡፡

የግንቦት ሰባት ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ አንዳርጋቸው በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡላቸው አራቱ ተከሳሾች በተደጋጋሚ ለፍርድ ቤት አመልክተው፣ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግለሰቡ እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ ከሳሽ ዓቃቤ ሕግ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ በማለቱና በማሳገዱ ሳይቀርቡ ቀርተዋል፡፡

ተከሳሾቹ በዋናነት የተጠረጠሩበት ወንጀል አቶ አንዳርጋቸው የግንቦት ሰባት አመራር በነበሩበት ወቅት፣ ከተከሳሾቹ ጋር ኤርትራ ውስጥ በመገናኘት የተለያዩ ትዕዛዞችን ማስተላለፋቸው በክሱ በዋናነት በመጠቀሱ፣ ክሱን በሚመለከት ራሳቸው አቶ አንዳርጋቸው ቀርበው እንዲመሰክሩላቸው መሆኑ በተደጋጋሚ ተዘግቧል፡፡

የሥር ፍርድ ቤት ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው በመከላከያ ምስክርነት ቀርበው እንዲመሰክሩላቸው ሲያስመዘግቡ ዓቃቤ ሕግ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ያሳገደ ቢሆንም፣ መዝገቡን መርምሮ ይግባኙ እንደማያስቀርብ ብይን ሰጥቷል፡፡ ዓቃቤ ሕግ መሠረታዊ የሕግ ስህተት እንዳለበት በመጠቆም ለሰበር ሰሚ ችሎት በማቅረብ ለጊዜው መዝገቡ ታግዶ የከረመ ቢሆንም፣ ግንቦት 11 ቀን 2008 ዓ.ም. ሰበር ችሎቱ ትዕዛዝ ሰጥቶበታል፡፡

ፍርድ ቤት በሰጠው ትዕዛዝ ላይ ይግባኝ እንደማይባል ትርጉም እንደተሰጠበት አስታውሶ፣ የቀረበለትን የይግባኝ አቤቱታ ውድቅ በማድረግ በመከላከያ ምስክርነት የተቆጠሩት አቶ አንዳርጋቸው ቀርበው እንዲመሰክሩ የሥር ፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዲሰጥ በማለቱ፣ የሥር ፍርድ ቤትም ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

አቶ አንዳርጋቸው ከዱባይ ወደ አስመራ ሲሄዱ የመን ሰንዓ ላይ በፀጥታ ኃይሎች ተይዘው፣ ከሁለት ዓመት በፊት ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸው ይታወሳል፡፡

የተለያየ አስተያየት ሲሰጡ በቴሌቪዥን መስኮት ከመታየታቸው በስተቀር አቶ አንዳርጋቸው የት እንዳሉ በግልጽ አይታወቅም፡፡ በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር የነበሩት ሚስተር ግሬግ ዶሪ በተለያዩ ጊዜያት ስለደኅንነታቸው ሲገልጹ ነበር፡፡ በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩት የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፊሊፕ ሀሞንድ፣ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በአግባቡ እንደተያዙና በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆናቸውን መናገራቸው ይታወሳል፡፡

Saturday 9 July 2016

U.S. Senators condemn Ethiopian abuses, urge ‘review’ of security assistance

(REPRIEVE)— A US Senate Committee has given initial approval to a Senate resolution calling on the White House to review American assistance to Ethiopia, amid concerns over the kidnap and detention of activist Andy Tsege and other abuses in the country.UK “stands shoulder to shoulder” with Ethiopia

The resolution, ‘Supporting respect for human rights and encouraging inclusive governance in Ethiopia’, is set for a vote in the full Senate during this legislative session, after passing its first stage of approval by Senators on the Committee on Foreign Relations.

The text urges the Ethiopian government to “release dissidents, activists, and journalists who have been jailed”, and to repeal laws that have been used to imprison critics of the government. It also calls on the US Secretary of State, John Kerry, to “conduct a review of security assistance to Ethiopia.”

The resolution comes as concerns grow for the fate of an opposition activist with links to the U.S. who is held on Ethiopia’s death row. Andargachew ‘Andy’ Tsege, a British man whose partner and children are US citizens, was kidnapped by Ethiopian forces at an airport in June 2014 and forcibly taken to Ethiopia. He is held under a death sentence that was imposed in absentia in 2009, during a trial that was condemned by US diplomats at the time as a form of “political retaliation” that was “lacking in basic elements of due process.”

The resolution’s sponsor is Senator Ben Cardin, who recently described his case as “one of many that gives cause for concern” in Ethiopia. Senator Cardin represents the state of Maryland, where Andy’s American relatives are from.

Mr Tsege is a prominent figure in Ethiopian opposition politics, and has previously spoken in Congress about Ethiopia’s human rights situation. Speaking to US lawmakers in 2006, he said that “the scale of repression [by the country’s government] has exceeded Ethiopia’s darkest hours during the military dictatorship.”

Since his kidnap, the Ethiopian authorities have heavily restricted Mr Tsege’s access to the outside world, including his family, and have aired videos of him being ‘interrogated.’ Torture is common in Ethiopian prisons, and there are fears for Mr Tsege’s wellbeing.

Last year, President Obama used a historic visit to Ethiopia to condemn the country’s ruling party for “stifl[ing] voices”, and for not upholding the rule of law. International human rights organization Reprieve – which is assisting Mr Tsege’s family – has written to the Obama Administration asking officials to raise Mr Tsege’s case with their Ethiopian counterparts, but no reply has been received.

Commenting, Maya Foa, director of the death penalty team at Reprieve, said:
  “Senators are right to condemn the Ethiopian government for the wave of repression that it has unleashed on journalists, bloggers and opposition activists in recent years. Among the victims is Andy Tsege, who has suffered a litany of abuses – from kidnap to torture and an in absentia death sentence – and whose young American family are desperate to have him home with them. If the Obama Administration is serious about improving democracy and the rule of law in Ethiopia, the White House must urgently heed these warnings from Congress – and demand the urgent release of political prisoners like Andy.”

Thursday 7 July 2016

An open letter to Dr. Tedros Adhanom Ghebreyesus, Minister of Foreign Affairs

SMNE urges Minister Tedros Adhanom to take swift and comprehensive action in helping Ato Habtamu Ayelaw gets proper treatment abroad and addressing the shameful treatment of the Ethiopians who are forced from their homes, resulting in wide scale displacement, homelessness and desperate life and health conditions.

July 6, 2016
Dr. Tedros Adhanom Ghebreyesus
Minister of Foreign Affairs
Federal Democratic Republic of Ethiopia
Addis Ababa, Ethiopia.
                                                                       SMNE's Open Letter to Ernst & Young Ltd.
Dear Minister Tedros Adhanom,

On behalf of the Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE), I am coming directly to you, to ask you as the Ethiopian Minister of Foreign Affairs, whose role is to represent the interests and image of Ethiopia internationally, to take immediate action to protect the vulnerable people in your own country. These people are experiencing a government-created health and human rights crisis of huge proportions.

You are also a top-decision-maker within the TPLF/EPRDF led Ethiopian government, someone who seeks to take the top leadership position in the World Health Organization (WHO) and also someone with a significant healthcare professional background. In light of your strategic position, I ask you to take immediate action to protect the people you represent.

Failure to do so will only intensify the increasing tensions within Ethiopia. In fact, even today (July 6) on the occasion of the ending of Ramadan and the celebration of Eid Mubarak; people involved turned the celebration into a protest against the government for their violent and unjust suppression the people.

This public outcry of discontent is a continuation of the ongoing uprising in the Oromia region that began in November 2015. A root cause of these protests is the strong opposition to the TPLF/EPRDF’s Addis Ababa Master Plan, which would displace countless Oromos from their homes. It was brought to a new level of outrage this past week when 30,000 Ethiopians, mostly of Oromo ethnicity from Lafto Sub-city of Addis Ababa in the villages of Qarsa, Kontoma, Mango, Wragenu and Hanamarim were forced from their homes, resulting in wide scale displacement, homelessness and desperate life and health conditions for those affected. Some residents of Lafto were allegedly given $1,500 per house and sent off, without recourse. Their homes were then bulldozed until demolished to make way for other uses of their land within the city limits of Addis Ababa.

Resistance to these evictions triggered a backlash of protest against TPLF/EPRDF authorities who were forcing the people from their homes. Government police and security forces cracked down on many of these civilians and some retaliated. The clash resulted in needless deaths on both sides. Two police officers and one civilian were killed; others were wounded. A mother and her newborn infant were also allegedly killed when the home they were in was bulldozed.

These tens of thousands of people are now left to fend for themselves; many with no place to go. Disturbing pictures have been on the social media of mothers with babies as young as five-days-old, families with children, and elderly victims, some as old as 93-years-of-age, all suddenly without shelter and protection. Conditions for the displaced are even more difficult due to it being the rainy season.

On July 1, 2016 another incident of violence broke out in a small town of Awaday in East Hararge. This incident started when authorities assumed a crowd of local people that had gathered around a burning house was not merely onlookers, but a protest. Many local people had raced to the location of this house fire and found no fire fighters present. Shortly thereafter, security officers rushed to the scene, assuming the gathering was another protest.

When they saw it was a fire, not a protest, the security forces started forcefully pushing the people away. The people reacted. Security officers then opened fire on the civilians, killing five young people, all under the age of 15, and wounding 8 others. Pictures of the aftermath of the horrific scene were circulated. Tensions remain high in the Oromia region; yet, these kinds of evictions and harsh crackdowns are going on throughout Ethiopia.

It is a matter of time before the people of Ethiopia unite across previous lines of division to fight back and stop the senseless killing of the people by the TPLF regime.

Mr. Minister,

A second case that speaks to the very difficult conditions facing Ethiopian political prisoners is represented by Habtamu Ayelaw, a 39-year-old husband and father of little girl who was arrested in July 2014 and accused of “terrorism” for his leadership role in the Unity for Democracy and Justice (UDJ) opposition political party. Like notable others, despite his well-known stance against violence and deep commitment to bring sustainable democratic change through a lawful political process, Habtamu was seen as a threat preceding the 2015 national election.

Mr. Habtamu was healthy and in the prime of his life when he entered the notorious Maekelawi and Qilinto Prisons. Now, Habtamu is in a life-threatening physical condition, believed to be linked to the torture, abusive mistreatment, intolerable conditions and lack of medical care while in prison. Although he was recently released, he now faces such serious health challenges that he has been told to seek care abroad as it is unavailable in Ethiopia.

                                                         Habtamu in a hospital bed in Addis Ababa.

Due to a TPLF/EPRDF imposed travel ban, he is unable to leave the country without permission from the Court Unfortunately, two requests to the Court by his attorney in his behalf have been denied despite the medical urgency. Mr. Habtamu is not a criminal; he only has a different political viewpoint and this should not cost him his life. Should he pass away without getting proper treatment; TPLF/EPRDF authorities would be held responsible. This would further destabilize the country which is already in turmoil.

Mr. Minister,

What is your position on these cases? Will you take necessary measures to uphold rights and save lives? It will require moral courage, especially because it involves taking some political risk in a country where TPLF survival mechanisms are in panic mode. Yet, unless someone steps up to restore justice, morality and reason to a nation in danger of imploding; we are all in danger, including the TPLF and the small minority ethnic group they represent— many of them innocent of wrongdoing.
Such decisions at key moments in our history can change the course of lives and nations. Conversely, inaction and refusal on your part and on the part of the TPLF Central Committee— who are running the county— can fuel an even larger crisis. In fact, it may present a greater risk to all of us, especially if more of our young people are killed or if someone like Habtamu dies because he was refused the emergency medical care that could have saved his life.

Mr. Minister,

Show your humanity and recognize our individual accountability before our Creator. How long can God-given laws and principle be flagrantly broken without consequence?
If we seek to do right in Ethiopia, individuals like yourself could help lead our country to a better place. Put yourself in the shoes of those Ethiopians who have lost loved ones. Put yourself in the place of these homeless families, trying to care for your children or elderly parents with no resources. If this was happening to you or to your loved ones or your ethnic group, what would you or other key top TPLF officials want done?

There are so many things with which I disagree in regard to the actions and policies of the TPLF/ERPDF, but when it comes to saving the lives of Ethiopians, regardless of ethnicity, I will set those differences aside and save lives.

We must all do this for the sake of others, not only ourselves or our own ethnic group. Hardening one’s heart against the right and humane thing to do will only plant the seeds of hatred, destruction, vengeance, division, and grudges that will pass on the consequences of these grievances to the descendants of all parties.
No matter how many wrong things some may have done in the past recognition of our own part, reconciliation and real transformative change is still possible. This is the only way we can save ourselves from ourselves. This is the only way to prevent our mutual destruction and to leave our children, grandchildren, communities and ethnic groups in a better and more harmonious place where they are not hated or excluded because of our actions or inaction today.

Mr. Minister,

The violent actions, disregard for human life and blatant ethnic favoritism being carried out in Ethiopia under current TPLF policies, are exactly the ingredients that will push people to the edge. Symptoms of impending destruction are everywhere.

Let us face it instead of blindly and naively celebrating at Adwa and lying to the donor countries about the double-digit economic growth and stability in order to receive more foreign aid while buying still more guns to crush more people.

Those supporting this TPLF regime through the many arms and branches of the EPRDF should not be complicit, but should follow righteousness instead of the TPLF. For anyone who loves Ethiopia, it is time to do the right thing and that right thing will show strength, not weakness.

I call on Ethiopians of faith to pray for these decision makers and those supporting them so that people repent of wrongdoing, forgive and reconcile; following it up with evidence of inner transformation.

That means being part of a movement to bring meaningful changes and the restoration of justice to Ethiopia. This means valuing the humanity of others instead of judging a person’s value based on ethnicity or some other identity factor. This means caring about the injustice of others as we care about our own. This is not only right, but no one group can bring sustainable freedom and harmony to only themselves. No one is free until all are free. We are to love our neighbors and even our enemies!
Ethiopia is at a critical place. For the last hundred years or more, we have learned to harden our hearts, wounding others and they wounding us in an endless cycle that must end. May you do the right thing.

May God protect all of us Ethiopians from our mutual destruction and bring reconciliation and justice to Ethiopia.

Sincerely yours,
Obang Metho,
Executive Director of the SMNE

Wednesday 6 July 2016

የአዲስ አበባ መስተዳድር ዜጎችን የማፈናቀሉን እርምጃ እንዲያቆም የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ሰመጉ) ጠየቀ

የአዲስ አበባ መስተዳድር ዜጎችን የማፈናቀሉን እርምጃ እንዲያቆም የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ የአሁኑ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ሰመጉ) ጠየቀ

አብዛሃኞቹ ዜጎች ካርታ ባይኖራቸውም ግብር ሲከፍሉ መቆየታቸውንና የመብራትና ውሃን የመሳሰሉትን አገልግሎቶችን ሲያገኙ እንደነበር ሰመጉ ገልጿል።

“እነዚህ ዜጎች አስቀድሞ ሕጋዊነትን በያዘ መልኩ መኖሪያዎችን እንዲሰሩ መደረግ ነበረበት። ይህ ከሆነ በኋላ ሕገወጥ ናችሁ በማለት አፍራሽ ግብረኃይል አሰማርቶ በክረምት ነዋሪዎች ላይ ቤት ማፍረስ ኢሰብዓዊ ነው” ሲል ሰመጉ ድርጊቱን በጽኑ ኮንኗል። በ አፍራሽ ግብረኃይሉ ቤቶቻቸው በክረምት ወራት የፈረሰባቸው ዜጎች ቁጥራቸው ከአስር ሽህ እንደሚበልጥና ታዳጊ ሕጻናትና አዛውንት ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸውን ጠቅሷል።

ሰመጉ ሰኔ 24 ቀን 2008 ዓ.ም. ባወጣው አስቸኳይ መግለጫ ፣ እየተፈጸመ ያለው ድርጊት ሕገ መንግሥቱንና ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜያት የፈረመቻቸውን የተለያዩ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ስምምነቶች በተለይም የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊና የባህላዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳንን በግልጽ የሚጻረር ነው ብሎአል።


ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ነዋሪዎች በደላቸውን በወኪሎቻቸው አማካኝነት ለሰመጉ አሰምተዋል። በቦሌ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ወረገኑ በሚባል ቦታ ላይ ለበርካታ ዓመታት ቤት ሠርተው፣ ትዳር መሥርተው የሚኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ፈርሰው ቆርቆሮ፣ በርና መስኮታቸው እየተነቃቀለ በአፍራሽ ግብረ ኃይል መወሰዱን ተጎጂዎቹ ማስረዳታቸውንና ሰመጉም ባለሙያዎችን ልኮ ጉዳዩን በአካል በመገኘት ማረጋገጡን አስታውቋል። በተጨማሪም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቀጣና 01 መንደር 06 በተለምዶ አጠራር ቀርሳና ኮንቶማ ቁጥራቸው ከ9 ሽህ 617 በላይ አባወራዎች በጠቅላላ 19 ሽህ 624 ነዋሪዎች ከ10 እስከ 15 ዓመት ከኖሩበት ቦታ፣ ‹‹ሕጋዊ አይደላችሁም ቦታው ለቄራ አገልግሎት ስለሚፈለግ ልቀቁ›› እንደተባሉ ሰመጉ ሪፖርት እንደደረሰው ጠቅሷል።


በግጭቱ ለዜጎች ሕይወት መጥፋት፣ አካል መጉደልና ንብረት መውደም ተጠያቂ የሆኑ አካላት ለፍርድ እንዲቀርቡ፣ የዜጎች መፈናቀል እንዲያቆም፣ ጉዳዩ በጥንቃቄ ተጠንቶ ካሳ ለሚገባቸው ሁሉ ካሳ እንዲከፈልና ቤታቸው ለፈረሰባቸውና በየቦታው ተበትነው ለሚገኙ ዜጎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ጉዳዩ የሚመለከታቸው መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ አካላት ሁሉ ሕጋዊ፣ ሰብዓዊና ቁሳዊ እገዛ፣ እንዲሁም መፍትሔ እንዲሰጧቸው ድርጅቱ ጠይቋል።


 





Exiled prominent journalist, activist wrote open letter to Ethiopia’s security chief

Exiled prominent journalist, activist wrote open letter to Ethiopia’s security chief following threats to their family back home by security operatives

Exiled journalist Sisay Agena and Tamagn Beyene, an activist and a well-known critic of the Ethiopian government wrote an open letter to the country’s security chief, Getachew Asefa following intimidation against their family back home in order to silence their criticism of the government.
In a joint letter released on Tuesday, Sisay and Tamagn, who now live in exile in the United States, wrote that agents of the regime and operatives of the Security and Intelligence Service paid a visit to their respective families on June 29, 2016, and offered briberies and intimidations in what they called “an attempt to stop us from our efforts to bring freedom to our country.”

“We are well aware that our everyday effort to realize our dream of having a free country would not be welcomed by the powers that be in Ethiopia; but we have never expected that your intelligence and security operatives would pay a visit to our family back home to threaten them or offer enticements so we would stop our struggle,” said the joint letter.

Sisay, managing editor at ESAT and producer of several programs, is known for his sharp criticism of the tyrannical regime back in his country, which is known to be one of the World’s top jailers of journalists. He was in and out of jail for several years before he was finally forced into exile.
A former comedian known for his wit and a man who once dominated the stages of theaters in his homeland, Tamagn Beyene left his country two decades ago. But having seen the sufferings of his fellow Ethiopians at the hands of tyrants, he decided to use his influence and skills to be a voice to the voiceless. He also runs a weekly talk show at ESAT.

“Threats against our families, holding them hostages and presenting enticements would not in any way stop us from our struggle for freedom,” their joint letter said in conclusion.

Tuesday 5 July 2016

Security forces detain hundreds protesting home demolition

Security forces have detained over 200 people in the capital Addis Ababa after thousands of homes, deemed illegal by the government, were demolished.

Six people, including two police officers, were killed in the confrontation last week and authorities are carrying out mass arrests in connection with the killings of the officers. The residents said the regime was indiscriminately arresting citizens who had nothing to do with the killing of the officers. Reports also said over 40 police officers, who sustained injuries in clashes with residents, have been admitted to the hospital.

Some residents told local media that not only their houses were torn down but security forces have beaten and harassed them.

Of the over 30,000 houses built in the area, authorities plan to demolish most of them that were deemed illegal. There are also plans by the city administration to carry out further demolition of houses in other areas of the capital.




ከኦሮሚያ ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተያያዘ የታሰሩት ዜጎች ቁጥር 50ሺህ እንደሚደርስ ዶ/ር መረራ አስታወቁ

በኢትዮጵያ ኦሮሚያ ክልል ከመንፈቅ በላይ የዘለቀው ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ ወደ እስር ቤት የተጋዙ ዜጎች ቁጥር ከ40ሺህ እስከ 50ሺህ እንደሚገመት የኦፌኮ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና ገለጹ። ወጣቶቹ በስርዓቱ ላይ ተቃውሟቸውን ከሚገልጹባቸው መንገዶች አንዱ ባለስልጣናት ስርዓቱን እንዲያወግዙና መንገድ በድንጋይ እንዲዘጉ ማስገደድ እንደነበርም አመልክተዋል። ኦህዴድ ኦሮሚያ ክልል ውስጥ መቶ በመቶ አሸነፍኩ ብሎ መስከረም ወር ላይ ስራ ጀምሮ፣ በህዳር ወር የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ስለምርጫው ውጤት በራሱ የሚናገረው ነገር መኖሩን ያመለከቱት ዶ/ር መረራ ጉዲና፣ ምዕራብያውያኑ በምርጫው ከ50 እስከ 60 ወንበር ለተቃዋሚዎች ይለቀቃል የሚል ዕምነት እንደነበራቸውም አስታወሰዋል። 

ምርጫው በኢህአዴግ አሸናፊነት ተጠናቀቀ በተባለ ማግስት ኦሮሚያ ክልል ግንጪ ውስጥ የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ከህጻናት እስከ አዛውንት ሌላው ቀርቶ የአካባቢው ሚሊሺያዎችን ጭምር ያሳተፈ እንደነበር ገልጸዋል። ወሊሶ አካባቢ በአንድ ባለስልጣን ላይ ወጣቶች የፈጸሙትንና በማስገደድ መንገድ ያዘጉበትንም ሁኔታ ዶ/ር መረራ ለኢሳት በሰጡት ቃለ-ምልልስ አስታውቀዋል። ወሊሶ ላይ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ሃላፊ ወጣቶች ሲመጡባቸው ጠረጴዛ ስር ለመደበቅ ያደረጉትን ሙከራ በኋላም አስገድደዋቸው ድንጋይ እየተሸከሙ መንገድ መዝጋታቸውን በዚሁ ቃለምልልስ አስታውሰዋል። በኢትዮጵያ ኦሮሚያ ክልል ተቃውሞ በተቀጣጠለበት ወቅት የሃገሪቱ የደህንነት ሃላፊዎች የመድረክ አባል ፓርቲዎችን ከኦፌኮ ነጥለው በማነጋገር ስብስቡን ለመከፋፈል መሞከራቸውንም አስታውቀዋል። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እንዲሁም ከሚኖሩበት መኖሪያ ቤት ተገደው መውጣታቸውን የገለጹት ዶ/ር መረራ ጉዲና፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚደንት የነበሩት እንድርያስ እሸቴ ከየትኛውም ተቋም የፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሳይሰጣቸው ፕሮፌሰር እየተባሉ ሲጠሩ መቆየታቸውን በዚሁ ቃለምልልስ “የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎችና አልታረቅ ያሉ ህልሞች” በሚለው መጽሃፋቸው በዝርዝር ተመልክተዋል።

 ኢሳት

Sunday 3 July 2016

Journalist Reeyot Alemu roasted TPLF agent Gebrekiros Abraha

A few weeks ago Ethiopians from all walks of life gathered in Nashville, Tennessee, to support ESAT and discuss issues of concern. Reeyot Alemu known for her courage and unwavering stand against tyranny was a guest of honor. Gross human rights violations was top on the agenda.

The inconvenient truth was too uncomfortable for a TPLF spy who sneaked in the meeting hall. The TPLF agent, who even worked at the spying entity called Information Network Security Agency, was full of himself. Gebrekiros Abraha, wanted to lecture and dictate what freedom-loving Ethiopians gathered should and should not do. He told them not to raise money for ESAT. According to him, the only enemy for oppressed Ethiopians was poverty. “You should know your enemy,” he lectured.
“If you don’t know your enemy, weha bewektut enboch” he said with a mix of faltering English and Amharic.

People took turns to vent out their anger at his arrogance and ignorance. But it was Reeyot Alemu who roasted the TPLF agent. “Let alone our money, we will give our blood” she told him.

Watch the full video(Amharic)


Saturday 2 July 2016

በናይሮቢ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የረሀብ አድማ አደረጉ

በኬንያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞችና የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ሀብታሙ አያሌው እገዳው ተነስቶለት የውጪ ህክምና እንዲያግኝ በናይሮቢ-አምነስቲ ቢሮ ፊትለፊት በረሀብ አድማ ጥያቄ ሲያቀርቡ ዋሉ። ሥርዓቱ በፈጠረባቸው ጫና ለስደት የተዳረጉት እነኚህ ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች በቀድመው አንድነት ፓርቲ አመራር በሀብታሙ አያሌው ምስል የተሰራ ቲሸርት በመልበስ ፤በቀድሞው አንድነት ፓርቲ አመራር በሀብታሙ አያሌው ላይ የተጣለበት የፍርድ ቤት እግድ እንዲነሳና በውጪ ሀገር ተገቢውን ህክምና እንዲያገኝ የሰብዓዊ መብት ተቋሙ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ግፊት እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

ሀሳባቸውን በነጻ በመግለጻቸውና ሙያቸውን ተግባራዊ በማድረጋቸው ሳቢያ በአገዛዙ አለስቃይና እንግልት የተዳረጉ በርካታ ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች ወደ ኬንያ ኡጋንዳና ወደሌሎች የተለያዩ ሀገራት ተሰደው በችግርና በስጋት እንደሚገኙ ይታወቃል። 

በረሀብ አድማ ላይ ሆነው በናይሮቢ የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ጽህፈት ቤት በመገኘት ጥያቄ ሲያቀርቡ የዋሉት እነኚህ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የሀብታሙ አያሌው ህይወት ላይ የከፋ አደጋ እንዳይደርስ ያደረባቸውን ስጋት በመግለጽ እንደ ሀብታሙ ሁሉ በተለያዩ እስር ቤቶች እየተገረፉና በህመም እየተሰቃዩ ያሉ የህሊና እስረኞች እንዲለቀቁና ተገቢውን ህክምና እንዲያገኙ ተማጽነዋል። ኢትዮጵያውያን የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ትናንት እና ዛሬ ሐብታሙ አያሌው የጉዙ እግዱ ተነስቶለት በውጪ ሀገር ህክምና እንዲያገኝ በዘመቻ መልክ እየጠየቁ ይገኛሉ። 

ዓለማቀፉ የሰብዓዊ መብት ተቋም አምነስቲ ኢንተርናሽናል በበኩሉ በዚሁ ጉዳይ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማፘም ደሳለኝ ደብዳቤ እንደጻፈ ትናንት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።


Friday 1 July 2016

በአወዳይ በተነሳው ተቃውሞ ህጻናትን ጨምሮ በትንሹ 4 ሰዎች ተገደሉ

(ኢሳት) በምስራቅ ሃረርጌ በአወዳይ ከተማ የተነሳውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ የወረዳው አስተዳዳሪ በከፈተው ተኩስ  ሁለት ህጻናት እና  አንድ ጎልማሳ ተገድለዋል። ነዋሪዎች ማምሻውን ለኢሳት እንደገለጹት ከሆነ የሟቾች ቁጥር 7 ድርሷል።

ኢብራሂም ሙሜ የሚባል ባለ ጸጉር ቤት እና አህመድ አልዬ የሚባል ባለሞባይል ቤት አሊ መሰራ ህንጻ እና አዋሽ ባንክ መሃል የሚገኘው ቤታቸው  ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ሌሊት ላይ መቃጠሉን ተከትሎ ህዝቡ ለተጎጂ ቤተሰቦች የእርዳታ ገንዘብ ማሰባሰብ ሲጀምሩ ፖሊሶች ጣልቃ ገብተው ለምን ተሰባሰባችሁ በማለት ተኩስ ከፍተዋል።

የአወዳይ 01 ቀበሌ ሊቀመንበር የሆነው አቶ አብዲ እድሪስ በከፈተው ተኩስ ሁለት ህናጻንት ጨምሮ 3 ሰዎች ተገድልዋል።  ፌደራል ፖሊሶች ደግሞ 4 ሰዎችን መግደላቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል። ትክክለኛውን የሟቾቾችን ቁጥር ለማወቅ ኢሳት ያደረገው ጥረት አልተሰካም።  በድርጊቱ የተበሳጨው ህዝብ ወደ ሊቀመንበሩ ቤት በማምራት ሁለቱንም መኖሪያ ቤቶቹን ያቃጠለ ሲሆን፣ ሊቀመንበሩ ወደ ሃረር ሸሽቶ ሲያመልጥ ፌደራል ፖሊሶች ደግሞ ባለቤቱንና ልጆቹን ይዘው ከከተማ አስወጥተዋቸዋል።

ከጅጅጋ እና ሃረር የተነሱ ተሽከርካሪዎች መንገድ ተዘግቶባቸው  ወደ ሃረር የተመለሱ ሲሆን፣ የመንግስት መስሪያ ቤቶችና ባንኮች ተዘግተው ውለዋል። የተሰባበሩ ተሸከርካሪዎች መኖራቸውንም የአይን እማኞች ገልጸዋል። ሃሮማያ ዩኒቨርስቲ የሚያስተምሩ መምህራን መንገድ በመዘጋቱ ምክንያት ወደ ስራ ሳይሄዱ ወደ ሃረር ተመልሰዋል።

የኦሮሞ ወጣቶች ህዝባዊ እንቅስቃሴ ከተጀመረበት ወቅት ጀምሮ በአካባቢው የሚታየው ተቃውሞ እስካሁን አልቆመም። ተቃውሞችን ተከትሎ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በግፍ ተገድለዋል። ሂማንራይትስ ወችና ሌሎችም የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ግድያው በገለልለተኛ ወገን እንዲጣራ በመጠየቅ ላይ ናቸው።