
በምዕራብ ወለጋ በመንዲ እና ጉሊሶ “መንግሥት አድማ በታኞችንና የአግዓዚ ጦርን አሠማርቶ ብዙ ተማሪዎችንና
የከተማዪቱን ነዋሪዎች በቁጥጥር ሥር አውሏል” ሲል አንድ ስሙ እንዳይገለፅ የጠየቀ ነዋሪ ከቪኦኤ ጋር ባደረገው ቃለ
መጠይቅ ገልጿል።
“በተጨማሪም ከላይ በተጠቀሰው ዞን ውስጥ ጉሊሶ በተባለ ከተማም እንዲሁ ዛሬው ተማሪዎች የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ እንደተሰባሰቡ ፖሊስ በአድማ በታኝ ጢስ ሠልፉን በትኗል” ስትል አንዲት ተማሪ ገልፃለች።
በጉሊሶ ወረዳ የሰላም እና መረጋጋት ኃላፊ የሆኑት አቶ ፍቅሩ ሙለታ “ተማሪዎቹ ሠላማዊ ሰልፍ የማካሄድ ፈቃድ ሳይሰጣቸው የወጡ በመሆኑ እንዲበተን አድርገናል” ብለዋል፡፡
በምሥራቅ ሸዋ ጊንጪ ከተማ ባለፈው ሣምንት የተካሄደውን የተማሪዎች ተቃውሞ ተከትሎ “ሰባ...