Monday, 30 November 2015

በምህራብ ኦሮሚያ የተጀመረው ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው

በምዕራብ ወለጋ በመንዲ እና ጉሊሶ “መንግሥት አድማ በታኞችንና የአግዓዚ ጦርን አሠማርቶ ብዙ ተማሪዎችንና የከተማዪቱን ነዋሪዎች በቁጥጥር ሥር አውሏል” ሲል አንድ ስሙ እንዳይገለፅ የጠየቀ ነዋሪ ከቪኦኤ ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ ገልጿል። “በተጨማሪም ከላይ በተጠቀሰው ዞን ውስጥ ጉሊሶ በተባለ ከተማም እንዲሁ ዛሬው ተማሪዎች የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ እንደተሰባሰቡ ፖሊስ በአድማ በታኝ ጢስ ሠልፉን በትኗል” ስትል አንዲት ተማሪ ገልፃለች። በጉሊሶ ወረዳ የሰላም እና መረጋጋት ኃላፊ የሆኑት አቶ ፍቅሩ ሙለታ “ተማሪዎቹ ሠላማዊ ሰልፍ የማካሄድ ፈቃድ ሳይሰጣቸው የወጡ በመሆኑ እንዲበተን አድርገናል” ብለዋል፡፡ በምሥራቅ ሸዋ ጊንጪ ከተማ ባለፈው ሣምንት የተካሄደውን የተማሪዎች ተቃውሞ ተከትሎ “ሰባ...

Saturday, 28 November 2015

“ረሃቡና ኢህአዴጋዊ እውነታዎች!” (ኤርሚያስ ለገሰ)

ህወሃት መራሹ መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ ረሃብ በተከሰተ ቁጥር የረሃቡን ዋነኛ ምንጭ “የአየር ንብረት መዛባት” በሚል ውጫዊ ምክንያት ማላከኩ የተለመደ ሆኗል። ለአብነት ያህል የዛሬ ዘጠኝ አመት በኢትዮጵያ ረሃብ በተነሳ ወቅት “የሰሞኑ የረሃብ ፖለቲካ” በሚል ረዕስ የውስጥ ድርጀት ሰነድ ተዘጋጅቶ ነበር ደራሲው ጓድ መለስ ዜናዊ ነበሩ። በማስከተልም የፓርቲው ከፍተኛ ካድሬዎች እና የመንግስት ባለስልጣናት ውይይት እንዲያደርጉበት ተደረገ። በዚህ ሰነድ ገፅ 6 ላይ የረሃቡን ዋነኛ ምንጭ እንደሚከተለው ይገልጻል።   “ረሃቡ ከምን እንደሚመነጭ በትክክል ማስቀመጥ መፍትሄውን ለማስቀመጥ ወሳኝ ነው። የረሃቡ ቀጥተኛ ምንጭ ከአየር ንብረት መዛባት ጋር ተያይዞ የተከሰተው ድርቅ ነው። የአየር ንብረቱ...

የሕወሓት አስተዳደር አዲስ አበባን “እናሰፋለን” በሚል ሰበብ የሚሰራው ሸፍጥ ተጋለጠ (ምስጢራዊውን ደብዳቤው ይዘናል)

(ዘ-ሐበሻ) በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ከተሞች ከባለፈው ዓመት ጀምሮ ሕዝቡ ሕወሓት የሚመራው መንግስት ያዘጋጀው የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን በመቃወም አደባባይ በመውጣቱ ለበርካቶች ሕይወት መጥፋት እና ለበርካቶች መቁሰል ምክንያት እንደነበር ይታወሳል:: እነዚህ ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ የሃገራችን ፍሬዎች ምክንያታቸው በአዲስ አበባን የማስፋፋት ምክንያት ምስኪን ገበሬዎችን በማፈናቀል መሬታቸውን ለባለሃብቶች ለመሸጥ ነው የሚል ነው:: ሕወሓት የሚመራው መንግስት “በልማት” ስም የተለያዩ የሃገራችንን መሬቶች ገበሬዎቹን በማሰናበት ለውጭ ባለሃብቶች በመሸጥ ይታወቃልና ወትሮም እነዚሁ በኦሮሚያ ክልል ያሉ ሕዝቦች አደባባይ ወጥተው ይህን በአዲስ አበባ ዙሪያ ያሉ ገበሬዎችን ያፈናቅላል ያሉትን አዲሱን ማስተር...

Tuesday, 24 November 2015

“በአዛዙ የአፈና መዋቅር የኢትዮጵያ ህዝብ የነፃነትና የእኩልነት ትግል አይቀለበስም” – ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

ህወሓት/ኢህአዴግ በህገ መንግስቱና በሌሎች ራሱ ባወጣቸው ህጎች በርካታ መብቶችን ለይስሙላ ቢደነግግብ ቅሉ፤ በተግባር ግን እነዚህን መብቶች ሆነ ብሎ ባደራጀው የአፈና መዋቅሩ እየደፈቃቸው ይገኛል፡፡ ምንም እንኳን አገዛዙ የመደራጀት መብትን በወረቀት ቢያሰፍርም ‹‹እግር እስኪያወጡ እንጠብቃለን፤ እግር ሲያወጡ ግን እንቆርጣለን›› በሚል መርህ ፓርቲዎችን በዚሁ የአፈና መዋቅሩ በገሃድ እያፈረሰ ቀጥሏል፡፡ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትን ፈቅጃለሁ ቢልም ጋዜጠኞችን በማሰር፣ በማሳደድና ሚዲያዎችን በመዝጋት አማራጭ ሀሳብ እንዳይራመድ አድርጓል፡፡ የመሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብትን ወረቀት ላይ ቢደነግግም በአስተዳደራዊ መዋቅሩ መሰረት ክርችም አድርጎ ዘግቶታል፡፡ የዜጎችን የመዘዋወር መብት ቢደነግግም...

ፖሊስ የቤተሰብ አባላትን እየጠረነፈ ነው

ፖሊስ ቤተሰብን በወረዳ፣ በብሎክ ብሎም በቤት ደረጃ በማደራጀት እየጠረነፈ መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልፀዋል፡፡ ከአሁን ቀደም በየካ ከፍለ ከተማ በየግቢው የታደሉ ‹‹የቤተሰብ ተጠሪ ፎረም›› የሚሉ ቅፆችን በማስደገፍ መዘገባችን የሚታወቅ ሲሆን ሰሞኑን በሳሪስ በተመሳሳይ አደረጃጀት ቤተሰቦችን ለመጠርነፍ እየተሰራ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ቅፁ ላይ የቤተሰብ አባላት ‹‹በመኖሪያ ቤታችን ውስጥ የሚፈጠሩ ያለ መግባባቶችን በራሳችን ለመፍታትና ብሎም የአካባቢውን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ እንዲሁም ከፖሊስ ጎን ሆነን በማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት የድርሻችን ለመወጣት›› በሚል ከቤተሰብ መካከል ለፖሊስ ተጠሪ እንዲወክሉ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህ የቤተሰቡ የፖሊስ ተወካይም ግቢው ውስጥ ተፈጠሩ...

Sunday, 22 November 2015

CPJ Awards Zone9 Bloggers of Ethiopia: International Press Freedom Award

In April 2014, Ethiopian authorities arrested six bloggers affiliated with the Zone 9 collective. The bloggers–Abel Wabella, Atnaf Berhane, Mahlet Fantahun, Natnail Feleke, Zelalem Kibret, and Befekadu Hailu–were charged with terrorism. The Zone 9 blogging collective was formed in May 2012 in response to the evisceration of the independent press and the narrowing of space for free expression. The name, “Zone 9,” is derived from the zones...

Saturday, 21 November 2015

የሀብታሙ አያሌው መልዕክት ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት

በሞት ጥላ መካከል ብሄድ እንኳን ክፉን አልፈራም !!! የልቤን ምጥ ልፃፈው ብዬ ደጋግሜ ብዕሬን ይዤ ወረቀቱ ላይ ብፅፍም እንደተራበው ወገኔ ሆድ ብዕሬ ባዶ ሆኖ ቀለም አልነጥበው አለ፡፡ በቅሊንጦ ማጎሪያ ቤት ሰማይ ስር ነፍሴ ሀዘን አቆርዝዛ በማይገፉ ቀንና ሌሊቶች ውስጥ ባዘነች፡፡ ለወትሮው ወገኔ እንደከፋው ስሰማ እንደወፍ በርሬ ችግሩን ልጋራው ከመሃሉ እደርስ ነበር፡፡ ዛሬ ግን የህዝቤ ስቃይ ወደ ሰማይ ጉኖ በጠኔ ሲንበረከክ እንደ ጅብራ ተገትረው በማያንቀሳቅሱኝ ወታደሮች ተከብቤ በጭንቀት እየባዘንኩ ከመጠውለግ በቀር አደርገው ነገር አጣሁ ፡፡ ወይ ሀገሬ!!! ወይ ወገኔ!!! ….. እመነኝ እንዳልኩህ አሁንም እመነኝ … አሁንም እመነኝ !!! እመነኝ ደርግ ወድቋል ኢህአዴግ ይወድቃል፡፡ ዛሬ...

Friday, 20 November 2015

Ethiopia’s Zone9 bloggers say “We are still prisoners”

Evidently six members of the Zone9 & three journalists are released from prison after they spent 14 to 18 months in prison. The three journalists and the two bloggers were released as the charges were ‘withdrawn’ in July. While the other four bloggers were acquitted in October. And one member the blogging collective, Befeqadu, was released on bail and he is yet to defend himself later this year in December on charges related with inciting...

Thursday, 19 November 2015

እነ የሺዋስ አሰፋ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መልዕክት አስተላለፉ

‹‹ርሃቡን ለዓለም ለማሳወቅ ከፍተኛ የህዝብ ግንኙነት ስራ መሰራት አለበት›› በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የሽብርተኝነት ክስ ተመስርቶባቸው በፌደራል ክፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲሰናበቱ ከተበየነላቸው በኋላ አቃቤ ህግ ይግባኝ ጠይቆባቸው ጉዳያቸው በጠቅላይ ፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት የሰማያዊ፣ የአንድነትና የአረና ፓርቲዎች አመራሮች በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለህዝብ መልዕክት አስተላለፉ፡፡ መልዕክቱን ያስተላለፉት በቃሊቲ እስር ቤት የሚገኙት የሺዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታና ዳንኤል ሺበሽ ሲሆኑ በተለይ ርሃቡ ለዓለም ማህበረሰብ እንዲታወቅ የተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ ሲቪክ ማህበረሰቦች፣ ሚዲያውና ሌሎችም የቻሉትን ሁሉ እንዲያደርጉ አደራ ብለዋል፡፡ በተለይ ከመንግስት...

Wednesday, 18 November 2015

በውጭ ሃገር ያሉ ኢትዮጵያውያን የተራቡ ኢትዮጵያውያንን እንዳይረዱ የኢትዮጵያ ኢምባሲዎች በየሃገራቱ መግለጫ እያወጡ ነው (ይዘናቸዋል)

(ዘ-ሐበሻ) 15 ሚልዮን ሕዝብን ለረሃብ የዳረገው የድርቅ አደጋ በየቀኑ የሰው ሕይወትን እየቀጠፈ መሆኑን የተረዱ ኢትዮጵያውያን በረሃብ ለተጎዱ ወገኖች የሚያደርጉትን እንስቅቃሴ የኢትዮጵያ ኢምባሲዎች ሕገወጥ ነው በሚል መግለጫ በማውጣት ኢትዮጵያውያን ወገኖቻቸውን እንዳይረዱ በማከላከል ላይ እንደሚገኙ ታወቀ:: ዘ-ሐበሻ ከትናንት በስቲያ ባቀረበችው ሰበር መረጃ መሠረት መንግስት በድርቁና ረሃቡ የተነሳ መልካም ስሜ እየጠፋ ነው በሚል “ረሃብ አልተከሰተም… የሞተ ሰውም የለም” በሚል እያስተባበለ ይገኛል:: የመንግስት ሚዲያዎችና ኢምባሲዎች እንዲሁም ከፍተኛ ባለስልጣናት ከጠ/ሚ/ር ጽሕፈት ቤት; የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እና የመንግስት ኮምዩኒኬሽን መስሪያ ቤት በተላለፈላቸው ት ዕዛዝ መሰረት ይህንኑ...

Sunday, 15 November 2015

ጋዜጠኞች ረሀቡን እንዳይዘግቡ ገደብ ተቀመጠ

(ዋዜማ ሬዲዮ) በሀገሪቱ የተከሰተውን ረሀብ በአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ለዓለም ህዝብ ይፋ መሆኑን ተከትሎ መንግስት መረጃዎችን ለማፈንና ለመደበቅ እየሞከረ ነው። መንግስት ለክልል መንግስታትና በውጪ ሀገራት ላሉ ኤምባሲዎቹ ባስተላለፈው መመሪያ ረሀብ ወደ ተከሰተበት አካባቢ ጋዜጠኞች እንዳይሄዱ፣ የረድዔት ድርጅት ሰራተኞችም መረጃ እንዳያቀብሉ ብርቱ ጥረት እንዲደረግ አሳስቧል። “ሁኔታውን ተጠቅመው የልማት ስኬታችንን ለማንኳሰስ ያሰፈሰፉ ፅንፈኛ ተቃዋሚዎችንና ለኢትዮዽያ በጎ አመለካከት የሌላቸውን ግለሰቦችና ተቋማትን መመከት ይገባል” ሲል መክሯል መመሪያው። ሁሉም መንግስታዊ አካላት ኢትዮዽያ የድርቁን አደጋ ለመቋቋም የሚያስችል በቂ አቅም እንዳላትና ጅምር የልማት ስራዎችን ላለማደናቀፍ አለም አቀፍ...

Saturday, 14 November 2015

‹‹ርሃቡን ያመጣው የኢህአዴግ የስልጣን ስስት ነው!›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

 ነገረ ኢትዮጵያ • ‹‹ለመፍትሄው መረባረብ አለብን›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ የሰጡት አስተያየት ‹‹የርሃቡ የቅርብ ጊዜ ምክንያቱ የዝናብ እጥረት ነው፡፡ የዝናብ እጥረት ድርቅን እስከተለ፡፡ ርሃቡን ያመጣው ግን የኢህአዴግ የስልጣን ስስት ነው፡፡ የኢህአዴግ የስልጣን ስስት ለረዥም ጊዜ፣ ለሀገር በሚጠቅም መልኩ ታቅዶ እንዳይሰራ አድርጎታል፡፡ ኢህአዴግ የሚሰራው ለአጭር ጊዜ የፖለቲካ ጥቅም እንጅ ለህዝብ አይደለም፡፡ ኢህአዴግ የሚሰራው አቅዶ ቢሆን፣ 10 አመት አደግን ተብሎ የ2 ወር ዝናብ መጥፋት ይህን ያህል ርሃብ ባላስከተለ ነበር፡፡ አሁን በየቀኑ የሚያወሩልን የውሸት ክምር ነው፡፡ የጭካኔያቸው ጭካኔ ደግሞ፣ ያኔ ርሃብን የስልጣን መወጣጫ እንዳላደረጉት አሁን...

Thursday, 12 November 2015

Center for the Rights of Ethiopian Women welcomes Reeyot Alemu

Center for the Rights of Ethiopian Women (CREW) is delighted to announce the arrival of the award winning journalist, Reeyot Alemu to the United States on Saturday, November 7, 2015. CREW sent invitation to the respected journalist and freedom of speech advocate, Reeyot Alemu and her sister Eskedar Alemu to speak at the upcoming Women and Leadership Conference which will be held sometime in the coming month. . Reeyot has been imprisoned for...

Wednesday, 11 November 2015

በኢትዮጵያ ድርቅ ባስከተለው ረሃብ የተነሳ በቆቦ ወረዳ አንድ ትንሽ መንደር ውስጥ ብቻ በየቀኑ 2 ህፃናት ይሞታሉ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኢትዮጵያ በተከሰተው ከባድ ድርቅ የተነሳ 15 ሚሊዮን ህዝብ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልገው አስታወቀ:: ድርጅቱ ባወጣው መግለጫውም በሃገሪቱ ሰሜናማው ክፍል ለዘገባ በተመረጠ ቦታ ብቻ በረሃብ የተነሳ (በቆቦ ወረዳ አንድ ትንሽ መንደር ውስጥ ብቻ) በቀን 2 ህፃናት ሕይወታቸው እንደሚያልፍ አስታውቋል::ዝናብ ባለመዝነቡ የተነሳ ሰብል ማምረት እንዳልተቻለ ያስታወቀው የተባበሩት መንግስታት የሚጠበቀውን ያህል ማምረት እንዳልተቻለ ጠቅሷል:: በዚህም መሠረት የተባበሩት መንግስታት በድርቁ የተነሳ የተጎዱትን ለመርዳት ከ330 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ እንደሚያስፈልግ አስታውቋል::ጠቅላይ ሚኒስተር ኃይለማርያምም ሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በቅርቡ በሰጧቸው ቃለምልልሶች በዚህ ረሃብ የሞተ ሰው የለም ሲሉ መናገራቸው የሚታወስ ሲሆን ይህ የቢቢሲ ዘገባ ሁለቱንም ሚኒስተሮች እርቃናቸውን ያስቀረ እንደሆነ የፖለቲካ ተንታኞች...

Tuesday, 10 November 2015

They can jail the journalist but not journalism

Abebe Gellaw On November 7, 2015, journalist Serkalem Fasil posted a Facebook reminder. It was her husband’s birthday. “Four years and two months have passed since we physically separated,” she wrote. “No matter how long it takes, I will persevere and will never give up hope with the help of Almighty God,’” she promised to her husband. Sentenced to 18 years in jail on trumped-up terrorism charges in Ethiopia, Eskinder Nega cannot read the...

Monday, 9 November 2015

እነ የሺዋስ ለሶስተኛ ጊዜ ባልተገኙበት ቀጠሮ ተሰጠባቸው

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የሽብርተኝነት ክስ ተመስርቶባቸው በፌደራል ክፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲሰናበቱ ከተበየነላቸው በኋላ አቃቤ ህግ ይግባኝ ጠይቆባቸው ጉዳያቸው በጠቅላይ ፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት የሰማያዊ፣ የአንድነትና የአረና ፓርቲዎች አመራሮች ዛሬ ጥቅምት 29/2008 ዓ.ም ለሶስተኛ ጊዜ ባልቀረቡበት ለህዳር 6/2008 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ጥቅምት 17/2008 ዓ.ም፣ ጥቅምት 22/2008 ዓ.ም እንዲሁም ዛሬ ጥቅምት 29/2008 ዓ.ም እንዲቀርቡ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸው ለሶስተኛ ጊዜ በሌሉበት የተቀጠረባቸው አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ አብርሃ ደስታ፣ አቶ ሀምታሙ አያሌው፣ አቶ ዳንኤል ሽበሺና አብሯቸው ይገብኝ የተጠየቀበት አቶ አብርሃም...

Saturday, 7 November 2015

ከዞን ዘጠኝ በኋላስ-ዝምታ?

የዞን ዘጠኝ ጦማርያን መፈታትን ተከትሎ በኢትዮዽያ ውህኒ የሚማቅቁ ሌሎች ጋዜጠኞች ጉዳይ ተገቢውን ትኩረትና ድጋፍ እንዳላገኘ የሚያመላክቱ ፍንጮች እየታዩ ነው። አለም አቀፍ ተቋማትም ሆኑ የመብት ተቆርቋሪ ወዳጆች ስለ ቀሪዎቹ ታሳሪዎች አስታዋሽ የሚፈልጉ ይመስላሉ። በኢትዮጵያ መንግስት የታሰሩ የፖለቲካ እስረኞች አያያዝ ኹኔታ እየከፋ መምጣቱን ከታሳሪዎቹ ቤተሰቦች በሚሰሙ ቅሬታዎች እየተተገለጹ ነው። ዋዜማ ያነጋገረቻቸው የጋዜጠኛው ተመስገን ደሳለኝ ቤተሰቦች ተመስገን ከጤናው መታወክ በተጨማሪ በቤተሰቦቹ እንዳይጎበኝና ምግብ እንዳይገባለት በመደረጉ ያለበትን እስር የከፋ ደረጃ ላይ እንዳደረሰው ተናግረዋል። ቤተሰቦቹ ከሚኖሩበት 165 ኪሜ ርቀት ላይ በሚገኘውየዝዋይ እስር ቤት የታሰረው ተመስገን ይህን...

Thursday, 5 November 2015

ረሃብ የመንግሰት ፖሊሲ ብልሹነት እንጂ የዝናብ እጥረት ዉጤት አይደለም!

ከኤፍሬም ማዴቦ...............ከአርበኞች መንደር !! ደርግ የቀዳማዊ ኃ/ሥላሤን ስርዐት ከደመሰሰ በኋላ ወሎ፤ ትግራይና ሰሜን ሸዋ ዉስጥ ህዝብ እንደ ቅጠል ሲረግፍ እሳቸዉ የልደት በዐላቸዉን ለማክበር ከዉጭ አገር ኬክ ያስመጣሉ ብሎ ነበር ንጉሰ ነገስቱንና ስርዐታቸዉን የከሰሰዉ። በአስራ ሰባቱ የደርግ ዘመን ሁለት ግዜ ከባድ ረሃብ ተነስቶ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎቻችን አልቀዋል። በተለይ በ1977 ዓም ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ የተከሰተዉና የአለምን ህዝብ ያስደነገጠዉ ረሃብ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያንን እንደ ቅጠል ሲያረግፍ ደርግ የስብሰባ አዳራሽ ለመስራትና የኢሠፓን ምስረታ ለማክበር ብዙ ሚሊዮን ዶላር እንዳባከነ ይታወሳል። ህወሃት የደርግን ስርዐት ሲዋጋ የኢትዮጵያን ህዘብ ከጎኑ ለማሰለፍ...

መንግስት በርሃብ ለተጠቁት ዜጎች እርዳታ እየሰጠ እንዳልሆነ ታወቀ

• በርሃብ የተጠቁት ዜጎች ቀያቸውን ለቀው እየተሰደዱ ነው • ‹‹ሰው በርሃብ እያለቀ ነው›› • ‹‹የሚላስ የሚቀመስ የለም፡፡ ቤተሰባችን ፈርሷል›› • ‹‹እርዳታ ቢሰጥማ ከዚህ ድረስ አንመጣም ነበር፡፡››  ነገረ ኢትዮጵያ መንግስት በርሃብ ለተጎዱት ዜጎች እርዳታ እየሰጠ እንዳልሆነ ቀያቸውን ለቀው አዲስ አበባ የገቡት የርሃቡ ሰለባዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ ከወሎ የተለያዩ አካባቢዎች በርሃብ የተጠቁ ዜጎች ህይወታቸውን ለማትረፍ ወሎ ውስጥ ከሚገኙት ከተሞች አልፈው ወደ ጎጃም፣ ጎንደርን እንዲሁም አዲስ አበባ እየተሰደዱ ሲሆን አዲስ አበባ በርካታ ተጎጅዎች ህፃናትን አዝለው እየለመኑ ይገኛሉ፡፡ የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ካነጋገራቸው መካከል ሁሉም መንግስት ለርሃቡ ተጎጅዎች...

Wednesday, 4 November 2015

የታማኝ እዳ (እንግዳ ታደሰ)

እንግዳ ታደሰ – ኦስሎ በቃል የምነት እዳ ሸክፎ ሸክሙን እንደ ሴባስቶፖል ሽቅብ ቁልቁለቱን ሲወጣና ሲወርድ ቋጥኝ አቀበቱን እስቲ እንካፈለው የሃገር እዳውን ፡፡ እዳው በግል የናት አባት እዳ አይደለም ፡፡ የርሱ እዳ የዕምነቱ እዳ ነው ፡፡ ለሸክም የከበደ ፥ የሰው ፊት የሚያስገርፍ፥ ዕረፍት የሚነሳ ፥ ከወለዳቸውና ከሚወዳቸው ቤተሰቡ ለወራት የሚያቆራርጥ፣ እንደ አጼ ቴዎድሮስ መድፍ ሴባስቶፖል ሽቅብና ቁልቁል የሚያስሮጥ፣ ኢሳትን በግሩ ለማቆሞ የሚደረግ ትግል ፡፡ ይህ ሰው በህወሃት ቀንበር ሥር ተሸብቦ ድምጹ የታፈነውን የዘጠና ሚልዮን ህዝብ መከራና እዳ ብቻውን የተሸከመ እስኪመስል ከምድር ጫፍ ሰሜን ዋልታ ኖርዌይ ፣ እስከምድር ግርጌ ደቡብ አፍሪቃ ፥ ከዚያም አውስትራልያ ረጅም የጢያራ...

Tuesday, 3 November 2015

ለጥቅምት 22 ሰማዕታት የመታሰቢያ ፕሮግራም ተካሄደ

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ምርጫ 1997 ዓ.ምን ተከትሎ ጥቅምት 22/1998 ዓ.ም በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ቀጥታ ትዕዛዝ በ‹‹ፀጥታ ሀይሎች›› በጭቃኔ ለተገደሉት ሰማዕታት እና ለቆሰሉት ኢትዮጵያውያን በሰማያዊ ፓርቲ ፅ/ቤት መታሰቢያ ተደረገ፡፡ የፕሮግራሙ ተሳታፊዎች ጥቅምት 22/1998 ዓ.ም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የገጠማቸውን በተለይም ኢትዮጵያውያን ሲገደሉ ያዩትንና የራሳቸውን ገጠመኝም አካፍለዋል፡፡ የፕሮግራሙ ተሳታፊዎቹ የተገደሉትን በክብር መቅበር እንዳልቻሉ እና ታፍሰው በተለያዩ እስር ቤቶች መታሰራቸውን አስታውሰዋል፡፡ አዛውንቶችንና ህፃናትን በጭካኔ ተገድለው ባንክ ሊዘርፉ ነው የተባለበትና የሥርዓቱን የህግና ሞራል የማይገድበው መሆኑን ያሳየበት ነውም ብለዋል፡፡...

Sunday, 1 November 2015

ኢትዮጵያ የኢንተርኔት ነጻነትን ክፉኛ ከሚገድቡ አገራት አንዷ ናት ተባለ

     በኢንተርኔት ነጻነት ከ12 የአፍሪካ አገራት የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች ቻይና የኢንተርኔት ነጻነት በመገደብ 1ኛ ናት  የኢንተርኔት ነጻነት በአለማቀፍ ደረጃ ለአምስት ተከታታይ አመታት እያሽቆለቆለ እንደሚገኝና ኢትዮጵያም የኢንተርኔት ነጻነት ከሌለባቸው የአለማችን አገራት አንዷ መሆኗን “ፍሪደም ሃውስ” የተባለው አለማቀፍ ተቋም ሰሞኑን ባወጣው አመታዊ ሪፖርት አስታወቀ፡፡ተቋሙ በ65 የአለማችን አገራት ላይ ያካሄደው የ2015 የኢንተርኔት ነጻነት ጥናት ሪፖርት፣ ከአለማችን አገራት የከፋ የኢንተርኔት ነጻነት የተንሰራፋባት ቻይና መሆኗን ጠቁሞ፣ ጥናቱ ካካተታቸው 12 የአፍሪካ አገራት...

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የለሊቱ የቪኦኤ ሚስጥራዊ ጉባኤ

በአበበ ገላው (ትርጉም በታኬ) በቅርቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድኃኖም እና አምባሳደር ግርማ ብሩ በዩናይትድ ሰቴትስ አሜሪካ ዋሽንግተን ዲ.ሲ በሚገኘው የቪኦኤ ሬዲዮ ጣቢያ በሌሊት በድብቅ በመግባት ሕጋዊ ስልጣኑ ሳይኖራቸው ስለስርጭቱ ለጥቂት የድርጅቱ ሠራተኞች የኢዲቶሪያል መመሪያ ከሰጡ በኋላ በአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው አገልግሎት (ቪኦኤ) እና በህወሀት የበላይነት በሚመራው የኢትዮጵያ መንግስት መካከል ያለው የሻከረ ግንኙነት ያልተጠበቀ አቅጣጫ ይዟል፡፡ ስብሰባው በሚስጥር በተካሄደበት ጊዜ የአምባገነኑ አገዛዝ ባለስልጣኖች ለሬዲዮ ስርጭቱ ሰራተኞች ስለዜና አዘጋገብ፣ እንደዚሁም ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ ስለሚተላለፈው የስርጭት ጥራት ሁኔታ መመሪያ የመስጠት ሙከራ ያደረጉ ለመሆናቸው ከታመኑ...