Thursday 4 June 2015

ዳኛ ብርቱካን ማሙሸትን ፈታች – ፖሊስ በራሱ ውሳኔ አልፈታውም!

Mamushet_court_order_062015

አሳዛኝ ዜና – ተፈታ ታሠረ
(ለገሰ ወ/ሃና)
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዝደንት አቶ ማሙሸት አማረ ዛሬ ግንቦት 25/2007 ዓም ጠዋት 3:00 አካባቢ የተሠየመው ችሎት ማሙሸት አማረ ክሱ ተቋርጦ ይፈታ ብሎ ወስኗል።

በዚህ መሠረት የማስፈቻ ወረቀት ይዘን ታስሮበት የነበረው ቦሌ ፓሊስ መምሪያ ከጠዋት ጀምሮ ብንጠብቅም እስረኞች ሲመለሱ ማሙሸት አልተመለሰም የቦሌ ክ/ከተማ ፓሊስ ሀላፊዎች ማሙሸት ለምን እንዳልመጣ ስንጠይቃቸው ጠብቁ ሲሉን ቆይተው ከቀኑ 11:55 ላይ ማሙሸት አዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን መወሰዱን ነግረውናል እስካሁን ያለበትን ማወቅ አልቻልንም ነበር ፡፡


አሁን በደረሰን ዜና በሌላ ክስ ሳይከሰስ እንዳልቀረ የሚጠቁም ነገር እየሠማን ነው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድረጅት ( መኢአድ) አባላት እና ቤተሰቦቹ ማሙሸት አማረ ታስሮበት የነበረው ቦሌ ፓሊስ መምሪያ ተሰባስበን የፕሬዝዳንታችንን መፈታት አስመልክቶ ደስታቸንን ለመግለጽ ተሰባስበን ነበር ይህንን ዜናም ለአለም ለማብሰር ዝግጅታችንን ጨርሰን ባለንበት ሰአት አስደንጋጭ ዜና ሰማን ማሙሸት አዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን እንደተወሰደ ነገሩን የኛ ሰዎችም በፍጥነት አዱስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ሄደው ሲጠይቁ ማሙሸት እነሱ ጋረ መግባቱን አና አስረኛ መሆኑን በመግለፅ ምግብ እና ልብስ አምጡለት እንደተባሉ ገልፀዋል ሚያዝያ 12/2007 ዓም ድንጋይ አስወርውረሀል የሚል ሌላ ክሰ እንደተፈበረከለትም ጭምር ሠምተናል ታስሮበት የነበረው ክስ ሚያዚያ 14/2007 ዓም መንግስት የጠራውን ሰልፍ ወጣቶችን አደራጅተህ አመፅ እንዲነሳ አቀነባብረሀል የሚል ነበር ተከላከል ተብሎ መከላከያ አሰምቶ ነበር ከሰው ማስረጃ ሌላ በተከሰሰበት ቀንና ሰአት ልደታ ፍረድ ቤት ችሎት ላይ እንደነበረ ከፍረድ ቤት ያቀረበው ሠነድ አላፈናፍን ስላላቸው እንደገና ወደ 12/2007 አውርደው መክሰሳቸወ ነው ነገ ጠዋት ግንቦት 26/2007 ዓም በ3:00 አራዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እንደሚቀርብ ታውቋል ፡፡

0 comments:

Post a Comment