Wednesday 18 November 2015

በውጭ ሃገር ያሉ ኢትዮጵያውያን የተራቡ ኢትዮጵያውያንን እንዳይረዱ የኢትዮጵያ ኢምባሲዎች በየሃገራቱ መግለጫ እያወጡ ነው (ይዘናቸዋል)

(ዘ-ሐበሻ) 15 ሚልዮን ሕዝብን ለረሃብ የዳረገው የድርቅ አደጋ በየቀኑ የሰው ሕይወትን እየቀጠፈ መሆኑን የተረዱ ኢትዮጵያውያን በረሃብ ለተጎዱ ወገኖች የሚያደርጉትን እንስቅቃሴ የኢትዮጵያ ኢምባሲዎች ሕገወጥ ነው በሚል መግለጫ በማውጣት ኢትዮጵያውያን ወገኖቻቸውን እንዳይረዱ በማከላከል ላይ እንደሚገኙ ታወቀ::

ዘ-ሐበሻ ከትናንት በስቲያ ባቀረበችው ሰበር መረጃ መሠረት መንግስት በድርቁና ረሃቡ የተነሳ መልካም ስሜ እየጠፋ ነው በሚል “ረሃብ አልተከሰተም… የሞተ ሰውም የለም” በሚል እያስተባበለ ይገኛል:: የመንግስት ሚዲያዎችና ኢምባሲዎች እንዲሁም ከፍተኛ ባለስልጣናት ከጠ/ሚ/ር ጽሕፈት ቤት; የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እና የመንግስት ኮምዩኒኬሽን መስሪያ ቤት በተላለፈላቸው ት ዕዛዝ መሰረት ይህንኑ ረሃብ የለም የሞተም የለም ዘገባ በሰፊው እያሰራጩት ይገኛሉ::

ኢምባሲዎች በሚገኙበት ሃገራት ኢትዮጵያውያን ማንኛውንም የገንዘብ ማሰባሰብ እንዳያደረጉ በማከላከል ሥራ ላይ እንዲሰማሩ በወረደላቸው ት ዕዛዝ መሰረት “ሕዝቡ ገንዘብ እንዳያዋጣና ረሃብም አልተከሰተም; መንግስት ጉዳዩን ተቆጣጥሮታል” በሚል ደብዳቤ እየበተኑ ይገኛሉ::

በሳዑዲ አረቢያ; በዱባይ; በአቡዳቢ የሚገኙ ቆንስላዎች እና ኢምባሲዎች በረሃቡ ስም ሕዝቡ ገንዘብ እንዳያዋጣ ቢያከላክሉም ሕዝቡ ግን ገንዘቡን ለመንግስት ባንሰጥም በውጭ ድርጅቶች በኩል ለሕዝቡ እንዲደርስ እናደርጋለን በሚል በከፍተኛ ሁኔታ ገንዘብ እየሰበሰበ ይገኛል:: መንግስት በውጭ ሃገር የሚደረጉ የገንዘብ ማሰባሰቦች “ገጽታዬን” ያበላሸዋል በሚል ረሃቡን ለመደበቅ የማይፈነቅለው ድንጋይ እንደማይኖር የነገሩን የዘ-ሐበሻ ዲፕሎማቲክ ምንጮች ይህ ረሃብ ስርዓቱን በወዳጆቹ ሃገራት ፊት እንዲዋረድ አድርጎታል ብለውናል::

ዘ-ሐበሻ ቀድማ በዘገበችው መሠረት በቢቢሲ ላይ ቀርባ ልጇ በርሃብ እንደሞተባት የገለጸችው ብርቱካን በደህነቶች አስገዳጅነት ልጄ የሞተው በበሽታ ነው ብላ እንድትናገርና በቲቭ እንድትቀርብ የተደረገውም ይኸው ገጽታን በማስተካከል ሰበብ ነው ተብሏል::
የኢትዮጵያ ኢምባሲዎች ከበተኗቸው ደብዳቤዎች መካከል የተወሰኑትን እነሆ::



0 comments:

Post a Comment