Wednesday 11 November 2015

በኢትዮጵያ ድርቅ ባስከተለው ረሃብ የተነሳ በቆቦ ወረዳ አንድ ትንሽ መንደር ውስጥ ብቻ በየቀኑ 2 ህፃናት ይሞታሉ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኢትዮጵያ በተከሰተው ከባድ ድርቅ የተነሳ 15 ሚሊዮን ህዝብ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልገው አስታወቀ:: ድርጅቱ ባወጣው መግለጫውም በሃገሪቱ ሰሜናማው ክፍል ለዘገባ በተመረጠ ቦታ ብቻ በረሃብ የተነሳ (በቆቦ ወረዳ አንድ ትንሽ መንደር ውስጥ ብቻ) በቀን 2 ህፃናት ሕይወታቸው እንደሚያልፍ አስታውቋል::

ዝናብ ባለመዝነቡ የተነሳ ሰብል ማምረት እንዳልተቻለ ያስታወቀው የተባበሩት መንግስታት የሚጠበቀውን ያህል ማምረት እንዳልተቻለ ጠቅሷል:: በዚህም መሠረት የተባበሩት መንግስታት በድርቁ የተነሳ የተጎዱትን ለመርዳት ከ330 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ እንደሚያስፈልግ አስታውቋል::

ጠቅላይ ሚኒስተር ኃይለማርያምም ሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በቅርቡ በሰጧቸው ቃለምልልሶች በዚህ ረሃብ የሞተ ሰው የለም ሲሉ መናገራቸው የሚታወስ ሲሆን ይህ የቢቢሲ ዘገባ ሁለቱንም ሚኒስተሮች እርቃናቸውን ያስቀረ እንደሆነ የፖለቲካ ተንታኞች ይናገራሉ::

በ2016 መግቢያ ላይ ይህን ያህል ገንዘብ ኢትዮጵያውያኑን ለመመገብ እንደሚያስፈልግ የተባበሩት መንግስታት ሲያስቀምጥ ቢቢሲ በሰሜን ኢትዮጵያ በቆቦ አካባቢ ተዘዋውሮ ድርቁን እንደሚከተለው ዘግቦታል::



የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኢትዮጵያ በተከሰተው ከባድ ድርቅ የተነሳ 15 ሚሊዮን ህዝብ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልገው አስታወቀ:: ድርጅቱ ባወጣው መግለጫውም በሃገሪቱ ሰሜናማው ክፍል ለዘገባ በተመረጠ ቦታ ብቻ በረሃብ የተነሳ (በቆቦ ወረዳ አንድ ትንሽ መንደር ውስጥ ብቻ) በቀን 2 ህፃናት ሕይወታቸው እንደሚያልፍ አስታውቋል::
ዝናብ ባለመዝነቡ የተነሳ ሰብል ማምረት እንዳልተቻለ ያስታወቀው የተባበሩት መንግስታት የሚጠበቀውን ያህል ማምረት እንዳልተቻለ ጠቅሷል:: በዚህም መሠረት የተባበሩት መንግስታት በድርቁ የተነሳ የተጎዱትን ለመርዳት ከ330 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ እንደሚያስፈልግ አስታውቋል::
ጠቅላይ ሚኒስተር ኃይለማርያምም ሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በቅርቡ በሰጧቸው ቃለምልልሶች በዚህ ረሃብ የሞተ ሰው የለም ሲሉ መናገራቸው የሚታወስ ሲሆን ይህ የቢቢሲ ዘገባ ሁለቱንም ሚኒስተሮች እርቃናቸውን ያስቀረ እንደሆነ የፖለቲካ ተንታኞች ይናገራሉ::
በ2016 መግቢያ ላይ ይህን ያህል ገንዘብ ኢትዮጵያውያኑን ለመመገብ እንደሚያስፈልግ የተባበሩት መንግስታት ሲያስቀምጥ ቢቢሲ በሰሜን ኢትዮጵያ በቆቦ አካባቢ ተዘዋውሮ ድርቁን እንደሚከተለው ዘግቦታል::
- See more at: http://www.satenaw.com/amharic/archives/10946#sthash.wuoHPf1Q.dpuf

0 comments:

Post a Comment