Saturday 29 November 2014

የእስክንድር ነጋ ያገባኛል ባይነት!

በላይ ማናዬ
 
‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል!››

ይህን ያለው ትንታጉ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ እስክንድር ነጋ ነው፡፡ እስክንድር ነጋን ካወኩት ወዲህ እንደዛሬ በኃይለ ቃል ሲናገር ሰምቼው አላውቅም፤ ወይም ትዝ አይለኝም፡፡ ዛሬ (ህዳር 19/2007 ዓ.ም) እኩለ ቀን ላይ እስክንድርን ልጠይቀው ቃሊቲ ተገኝቼ ነበር፡፡ ሆኖም ሁኔታው ሁሉ እንደማንኛውም ቀን አልነበረም፡፡ በር ላይ ስደርስ በርከት ያሉ የአንድነት ፓርቲ አባላት ሰሞኑን እያካሄዱት ያለውን የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ በማስመልከት እስክንድር ነጋን፣ አንዱዓለም አራጌን እና ሌሎችንም ሊጠይቁ በቦታው ተገኝተው ነበር፡፡

በጠዋት ቂሊንጦ የሚገኙ ወዳጆቼን ጠይቄ አብረውኝ ከነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ጋር ነበር ወደ ቃሊቲ ያመራሁት፡፡ ቃሊቲ የተገኘው ሰው ሁሉ መጠየቅ የሚፈልገውን ሰው እና ሙሉ አድራሻውን እያስመዘገበ ሳለ በመሐል እኔም እስክንድርን መጠየቅ እንደምፈልግ ነግሬ ተመዘገብኩ፡፡ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ግን ስማችሁ ከዚህ ቀደም ያልተመዘገባችሁ አሁን መግባት አትችሉም መባሉን መዝጋቢ ፖሊሱ አረዳን፡፡ እኔ እና ትንሽ ሰዎች መግባት ስንችል አብዛኛው ሰው ግን መግባት እንደማይችል ተነገረን፡፡

በዚህ ሁኔታ እስክንድር ጋር ደርሰን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ አንድ የአንድነት ፓርቲ አባል ሰሞኑን ፓርቲያቸው እስረኞችን በተመለከተ በማህበራዊ ድረ ገጽ ላይ እየተሰራ ያለውን ስራ ለእስክንድር ያብራራለት ጀመር፡፡ እስክንድር በተለመደ ጥሞናው ሲያዳምጠው ቆይቶ፣ በግሉ የተሰማውን እና መሆን ቢችል ያለውን ነጥብ ተናገረ፡፡ በመሐል ወጣቱ የአንድነት አባል ወደ እስክንድር ጠጋ ብሎ ሌሎች ተጨማሪ ጉዳዮችን ሲነግረው ድንገት አንድ የፖሊስ አዛዥ ጨዋታቸውን እንዲያቆሙና እስክንድር ወደ እስር ቤቱ እንዲገባ፣ ወጣቱ የአንድነት አባል ደግሞ ወደ ውጪ እንዲወጣ በትዕዛዝ ማጣደፍ ያዘ፡፡

ይህኔ እስክንድር ለስለስ ባለ አነጋገር ምንም እንዳላጠፋን በመግለጽ ፖሊሱ መረጋጋት እንዳለበት አስረዳ፡፡ የፖሊስ አዛዡ ግን ጭራሽ ብሶበት ወጣቱ በቶሎ እንዲወጣ አደረገ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ‹ፖለቲካ ማውራት አቁሙ› የሚል ሆነ፡፡ ይህን ተከትሎ እስክንድር ድንገት በኃይለ ቃል ተናገረ፡፡ ‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል! የማወራው ስለ ሰላማዊ ትግል፣ ስለህጋዊ ትግል ነው!›› አለ እስክንድር በስሜት ውስጥ ሆኖ፡፡

በግሌ እስክንድር እንዲረጋጋ፣ ሁኔታው ግን ያልተገባ እንደሆነ ገለጽኩ፡፡ ፖሊሱ ግን ሊረጋጋ አልቻለም፡፡ እስክንድርን ይዞት ሄደ፡፡ ‹‹በርቱ! እንቅስቃሴያችሁ ህጋዊና ሰላማዊ ይሁን እንጂ ትግላችሁን ቀጥሉ!›› ሲል እስክንድር ወደ እስር ቤቱ እየገባ ተናገረ፡፡ የፖሊስ አዛዡም ከእስክንድር ጋር የነበረንን ቆይታ ሰዓቱ ሳይደርስ ገታው፡፡ የእስክንድር ያገባኛል ባይነት አስደመመኝ፡፡ እስር ቤት ሆኖም፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖም እስክንድር ስለ ሀገሩ እንደሚያገባው በስሜት ተናገረ፡፡ መብቱን መቼም ቢሆን አሳልፎ እንደማይሰጥ አስረገጠ፡፡

ስለ ያገባኛል ባይነት ሳስብ በጠዋት ቂሊንጦ ያገኘኋቸውን የዞን 9 ጦማሪዎች አስታወስኩ፡፡ ‹ስለሚያገባን እንጦምራለን!› ይላሉ ወጣቶቹ ጦማሪያን፡፡ ከአብርሃ ደስታ ጋር አብረው ያገኘኋቸው እነ በፍቃዱ ኃይሉ እና አጥናፍ ብርሃኔ ብዙ ጉዳዮችን እያነሱ አወጉኝ፡፡ ‹‹ህወሓት አንድ ወይም ሁለት ነባር የህወሓት ባለስልጣናትን በሽብር ከከሰሰ ስርዓቱ እንዳበቃለት እቆጥራለሁ፡፡ ምክንያቱም ሽብር ማታለያ መሆኑ ይቀራል›› አለኝ በፍቃዱ ኃይሉ፡፡ አብርሃ ደስታ ቀበል አድርጎ ‹‹እናት አልጋነሽ በሽብር ስትከሰስ በጣም ብዙ ሰው ተቃውሞ ነበር›› አለ፡፡ አጥናፍ በበኩሉ ‹‹ቄስና ሸህ ሽብርተኛ እየተባለ አይደለም እንዴ›› በማለት ጠየቀ፡፡

አብርሃ ደስታ አንድ ነገር በኃይል እንደሚቆጨው ተናገረ፡፡ ምን እንደሆነ ጠየቅሁት፡፡ ‹‹ብዙ የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ሳላደርግ መታሰሬ ይቆጨኛል!›› አለ፡፡ በፍቃዱ በበኩሉ፣ ‹‹እኔም የገባኝ ነገር ያለውን የሰላማዊና ህጋዊ የመስሪያ ልክ አለመስራታችን ነው፡፡ አሁን ላይ ሆኜ ሳስበው እንዲህ ለሚያስሩን ስንት ህጋዊና ሰላማዊ እንቅስቃሴዎችን እንኳ ሳናደርግ በትንሽ ነገር በርግገው እዚህ ሲያስገቡን ይቆጨኛል›› በማለት ሀሳቡን ቀጠለ፡፡ ‹‹በእርግጥ አንድ ሰው አሁን መጠንቀቅ ያለበት የሚሰራው ስራ ህጋዊ መሆን አለመሆኑን እንጂ፣ ይህን ካደረኩማ ያስሩኛል የሚለውን መሆን የለበትም፡፡ እነሱ ከፈለጉ ያስሩሃል፤ ስለዚህ መብትህን ተጠቅመህ መታሰሩ ይሻላል እንዲሁ ምንም ሳይሰሩ ከመግባት›› ሲል አብርሃ ሀሳቡን አካፈለ፡፡

ቂሊንጦ ከእነ በፍቃዱ ጋር ስንጨዋወት ስለእስክንድር ነጋ ትሁትነት፣ አስተዋይነት፣ ሰላማዊነት እያነሱ ሰላምታ እንዳደርስላቸው ጠየቁኝ፡፡ እኔም እስክንድር ነጋን ሳውቀው በትሁትነቱ፣ በአስተዋይነቱና በሰላማዊነቱ ነው፡፡ ዛሬ በነበረው ሁኔታ ግን ክፉኛ ተበሳጭቶ ነበር የተመለከትኩት፡፡ ያ ፈገግታው ከፊቱ ብን ብሎ ጠፍቶ ‹‹ያገባኛል!›› ሲልበት የነበረውን ስሜት ግር አለኝ፡፡ ካልነኩት የማይነካ ሰው ሲነኩት ትንታግ ነው፡፡ እስክንድር እዛ ስሜት ውስጥ የገባው ተገድዶ ነበር፡፡ ሊጠይቁት የመጡትን ሰዎች አብዛኞቹን አላስገባም ማለታቸው ሳያንስ ከገቡትም መካከል የምታወራውን እኔ ልምረጥልህ በሚል ግብዝነት አባርረዋል፡፡ እስክንድር ይህን አይቶ ዝም ማለት አልቻለም፡፡ ስለሆነም እንዲህ አለ፤

‹‹…እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል! የማወራው ስለ ሰላማዊ ትግል፣ ስለህጋዊ ትግል ነው! ስለሀገሬ ያገባኛል!››



Thursday 27 November 2014

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ የወጣቶች ክፍል አዘጋጅነት ታላቅ ሰላማዊሰልፍ በኖርዌይ ኦስሎ ተካሄደ!!!

 Democratic Change in Ethiopia Support Organization Norway - D.C.E.S.O.N's photo.
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ የወጣቶች ክፍል አዘጋጅነት በዛሬው እለት ሀሙስ (November 27,2014) በኖርዌ ኦስሎ በእንግሊዝ ኢንባሲ ፊት በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከሩቅም ከቅርብም በአንድነት በመሰባሰብ ከቀኑ 13፡30 እስከ 15፡00 ስዓት ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ አካሄዱ።

የሰልፉ ዋና አላማ የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሃፊና የሰባዊ መብት ተቆርቋሪ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በአንምባ ገነኑ የወያኔ ቡድን በህገ ወጥ መንገድ ታፍነውና ፍትህ ተነፍገው በእስር ቤት መታሰራቸውን ለመቃወም ሲሆን በሰልፉ ስፍራ የተገኙ ሰዎች ሁሉ አቶ አንዳርጋቸው ለዲሞክራሲ እና ሰብአዊ መብት መከበር ከወጣትነት ጀምሮ የታገለ ታላቅ የሰላም ምሳሌ፣ የፍትህ ተምሳሌት፣ የነጻነት በር ከፋች እንዲሁም አገራዊ ስሜት የተላበሰ አርበኛ እንጂ እስር፣ ድብደባና መሰቃየት የሚገባው ሰው አልነበረም በማለት ለእንግሊዝ መንግስት በኢንባሲው አማካኝነት ዜጋዋን ከአረመኔና ጨካኝ መዳፍ እንድትታደግና ፍትህ እንዲያገኝ በከፍተኛ ድምጽ አሳስበዋል። 

ወጣቶች እጃቸውን በሰንሰለት በማሰር እኛም እንደ አርበኛው አንዳርጋቸው ጽጌና በእስር ቤት የሚሰቃዩ ኢትዮጵያውን የቁም እስረኞች ነን የሚል ጥልቅ መልእክት አስተላልፈዋል። ብዙ መስራትና መጻፍ የሚችሉ እጆች፣ መናገር የሚችል አንደበት፣ የእውቀት ባለቤት የሆነ አእምሮ ታስረዋልና እኛም ወጣቶች እስረኞች ነን በሚል ውስጣዊ ስሜት ለስዓታት የኖርዌ ብርድና ቁር ሳይበግራቸው እጃቸውን በሰንሰለት በማሰር ድምጻቸውን ከፍ አድርገው አሰምተዋል።




Democratic Change in Ethiopia Support Organization Norway - D.C.E.S.O.N's photo.
Democratic Change in Ethiopia Support Organization Norway - D.C.E.S.O.N's photo.
Democratic Change in Ethiopia Support Organization Norway - D.C.E.S.O.N's photo.

Wednesday 26 November 2014

Ethiopia is one of the ‘world’s least connected country’

Ethiopia is one of the 'world’s least connected country'Denmark has been named the world’s “most connected” country based on mobile phone and internet use.
Scandinavia dominated this year’s rankings, with Sweden in third place, followed by Iceland in fourth, Norway sixth and Finland eighth. Britain came fifth.



They were compiled as part of a report by the International Telecommunication Union – the Information and Communication Technology Development Index (IDI), which rates 166 countries according to their level of access to, use of and skills in using information and communication technology.
Hong Kong was the ninth most connected country, coming in ahead of Japan in 11th place, while Luxembourg completed the top 10.
Other countries in the top 30 included the US (which ranked 14th), Australia, Switzerland, Singapore, Germany, France, New Zealand, Estonia and Macau, as well the principalities of Andorra and Monaco.

The 10 least connected countries were all in Africa, with the Central African Republic being the worst, followed by Niger, Chad, Eritrea and Ethiopia.

All countries were shown to have improved their IDI values in the last year, while the nations with the “most dynamic” improvement in ranking included the United Arab Emirates, Fiji, Cape Verde, Thailand, Oman, Qatar, Belarus, Bosnia & Herzegovina and Georgia. Improvements were said to have been driven mostly by better wireless broadband connection.

Europe proved to be the most connected region, scooping up eight of the top 10 rankings, while Africa had the lowest regional ranking. The continent, however, did show a mobile broadband growth rate of more than 40 per cent in 2014 on last year.

Nearly three billion people globally will be using the internet by the end of this year, up by nearly 40 per cent on last year. But 450 million people still don’t live within reach of a mobile signal, while 4.3 billion people are not connected to the internet – with 90 per cent of those living in developing countries, the report said.

Earlier this year, Telegraph Travel’s technology expert Donald Strachan outlined the “world’s Wi-Fi-friendliest cities”, featuring various countries from the top 40 of this year’s IDI report.
Connecting in the Finnish capital of Helsinki is password-free and easy thanks to a network of hotspots in public buildings, civic squares and even on some buses and trams around the city.

Hong Kong, “one of the world’s most futuristic cities”, was said to be generous with free internet access in public areas. There are several free Wi-Fi networks, the key ones being GovWiFi (at parks, libraries, public buildings, ferry terminals and more) and MTR WiFi, which provides 15 minutes of free Wi-Fi per device up to five times every day at MTR stations.

Taipei offers 30 days of free access to a national, government-backed network of over 5,000 hotpsots. Hundreds of these free iTaiwan hotspots are available throughout the Taiwanese capital.

Macau was noted for its WiFiGo service which offers free internet for visitors every day between 8am and 1am. The network has around 150 hotspots, meaning there’s usually Wi-Fi close by, including at ports, museums and tourist information centres.

Other major cities with free public Wi-Fi access include New York, Paris and Perth, Australia, as well as Florence and Tel Aviv, which has eighty hotspots dotted around its centre.

Access to free Wi-Fi has been an increasingly important factor for travellers around the world, especially when booking a hotel. Britain’s hotels were found to be among the worst in Europe for free Wi-Fi access, while the two best performing cities were both Swedish – Malmö and Gothenburg, where 98 per cent and 96 per cent of hotels were found to offer free Wi-Fi, a survey by the travel search engine KAYAK earlier this year revealed.

A new website aiming to help travellers in the search for free and fast wireless internet access was introduced earlier this year. Hotewifitest.com lets hotel guests test the speed of their internet connection, and then stores the results for others to view. It also records whether the Wi-Fi is free or comes at a price.

Several airports around the world also offer free Wi-Fi services, with Dallas-Forth Worth in Texas being among the best, providing free Wi-Fi in all five of its terminals since 2012. Since upgrading its former paid network, the number of daily Wi-Fi connections has risen from 2,000 to 55,000. Helsinki Airport, Singapore’s Changi Airport, Seoul’s Incheon Airport and Amsterdam Schiphol complete the world’s top five for airport Wi-Fi quality.
Earlier this year, Britain’s biggest airports have been criticised for failing to provide passengers with unlimited Wi-Fi access.

None of Britain’s six busiest airports – Heathrow, Gatwick, Manchester, Stansted, Edinburgh and Luton – offer unlimited free internet access, according to a study by Skyscanner, the flight comparison website.

Source: Telegraph

አንድነትና መድረክ ተለያዩ


ላለፉት ስድስት ዓመታት ገደማ ያህል በጋራ ለመሥራት ተስማምተው የተቃውሞ ጐራው ላይ በጋራ ሲሠሩ የነበሩት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) እና አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የነበራቸውን አብሮ የመሥራት ስምምነት አቋርጠው ተለያዩ፡፡

ሁለቱ ፓርቲዎች የቀድሞው የአንድነት ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው ሰጥተውታል በተባለው አስተያየት የተነሳ እሰጥ አገባ ውስጥ መግባታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ አስተያየቱን አንድነት ያስተባብል በሚል ከመድረክ የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ለፓርቲዎቹ መለያየት ከፍተኛውን ድርሻ መውሰዱን የሁለቱ ፓርቲዎች ባለድርሻ አካላት መግለጻቸውን መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡

ከሁለት ሳምንታት በፊት ዳግም የመድረክ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ለአንድነት እስከ ኅዳር 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ድረስ ገደብ መስጠታቸውን መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡
 በዚህም መሠረት አንድነት ለመድረክ ኅዳር 11 ቀን 2007 ዓ.ም. በጻፈው የመልስ ደብዳቤ፣ ከመድረክ አባልነት መውጣቱን ገልጾ መጻፉን የመድረክ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጥላሁን እንደሻው ለሪፖርተር አረጋግጠዋል፡፡

የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ አበበ አካሉ በበኩላቸው፣ ‹‹ከመድረክ ጋር በይፋ ተለያይተናል፤ ፊርማችንን ቀደናል፤›› በማለት ከመድረክ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት ማቋረጣቸውን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

ለሁለቱም የፓርቲ አመራሮች ምርጫ በተቃረበበት ወቅት እንዲህ ዓይነት ውሳኔ መውሰድ አጠቃላይ ሰላማዊ ትግሉን አይጐዳውም ወይ የሚል ጥያቄ ሪፖርተር አቅርቦ ነበር፡፡ የሁለቱም ፓርቲ አመራሮች ጉዳት ማስከተሉን ተቀብለው ነገር ግን ከአቅም በላይ በመሆኑ መለያየት መፍትሔ እንደሆነ አስረግጠው ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

በዚህ ረገድም ‹‹ይሄ እኮ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ የተቃውሞ ፓርቲዎች የጋራ ትብብር አለመኖር፤ ውህደት አለመኖር የኢትዮጵያን ሕዝብ ትግል ይጐዳዋል፡፡ ይህንን እናውቀዋለን፡፡ ነገር ግን ትግሉን እየጐዳው ቢሆንም አብሮ የማይሄድና የማይሆን ነገር ሲታይ አብረህ መቀጠል አትችልም፡፡ መለያየት አለብህ፤›› በማለት ልዩነቱ በመስፋቱ መለያየቱ የግድ እንደሆነ አቶ አበበ ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡

‹‹እንዲህ ዓይነት ውሳኔዎች ትግሉን እንደሚጐዳ ይታወቃል፤›› በማለት የገለጹት አቶ ጥላሁን በበኩላቸው፣ ‹‹የተቃውሞ ጐራውን ለመጉዳት የተነሱና የተመኙ ሰዎች የሠሩት ሥራ ጠቅላላ አንድነትና መድረክን ወደ መለያየት ወስዷል፤›› በማለት ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የሁለቱም ፓርቲ አመራሮች ወደፊት ስለሚያደርጉት የትግል አቅጣጫ የየራሳቸውን ዕቅድ ማዘጋጀታቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ‹‹እኛ ቀድሞውኑ በአፍራሽ መልኩ የመጣውን እንዴት እንደምንቋቋምና እንዴት ትግላችንን በዚህ ጉዳት ምክንያት ሳይዳከም ሊቀጥል እንደሚችል የራሳችንን ሥራ ስንሠራ ስለቆየን ይህን ጉዳይ አሁን እንደ አዲስ አናየውም፡፡ በእኛ በኩል የራሳችንን ትግል በተጠናከረ ሁኔታ እንቀጥልበታለን፤›› በማለት አቶ ጥላሁን ቀጣይ ሥራቸውን ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ አቶ አበበ በበኩላቸው፣ ‹‹መድረክ አንካሳ ነው ያደረገን፡፡ ነገር ግን አንካሳ ሆነን ከምንቀጥል ባለን ነገር ሮጠን ምርጫውን እኛ ባለን መዋቅር ብንጋፈጠው የተሻለ ውጤት እናገኛለን፤›› በማለት ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

 ሪፖርተር

ርዮት አረንጓዴ፣ ቢጫ ቀይ ሰንድቅ አላማ በላይዋ ላይ ለብሳ በክብር ከቃሊቲ ትወጣለች – ግርማ ካሳ

index
በሃይ ስኩል የእንግሊዘኛ አስተማሪ ነበረች። በሕገ መንግስቱ ላይ የተደነገገዉን መብት በመጠቀም፣ በተለያዩ አገር ውስጥ በሚታተሙ ሜዲያዎች ትጽፋለች። «እነርሱ እንዲጻፍ ከሚፈልጉት ዉጭ እንዲጻፍ የማይፈልጉ ባለስልጣናት፣ የሃሰት ክስ መሰርተዉ፣ ዳኛ ለተብዬዎች መመሪያ ሰጠዉ፣ መሰረተ ልማቶችን ለማፍረስ አሴራለች፣ ሽብርተኛ ናት» ብለዉ ፈረዱባት።
ይች እህት ርዮት አለሙ ትባላለች። ጡቷ አካባቢ ችግር ስላለበት ክትትል እንደሚያሰልጋት እየታወቅም ክትትል እንድታገኝ አልተደረገም። ወደ ሶስት አመት ገደማ ባላጠፋችዉ ጥፋት፣ ኢሕአዴግን ስለተቃወመች ብቻ፣ እየማቀቀች ነዉ። የርዮት ወንጀል አገሯ፣ ሕዝቧን መዉደዷ ነዉ።

ርዮት አለሙ፣ ከጋዜጣኛ ነብዩ ሃይሉ ጋር በአዲስ ፕሬስ፣ ከጋዜጣኛ ስለሺ ሃጎስ ጋር በ ቼንጅ መጽሄት ላይ ሰርታለች። ነብዩና ስለሺ፣ በአንድነት ራዲዮ አንድ ወቅት ስለርዮት አለሙ፣ ከሚያወቁት ያጋሩንን ጥቂቱን ላካፍላችሁ።
ያዉ በአገራችን ባለዉ የዘር ፖለቲካ ምክንያት «የትግራይ ልማት ማህበር»፣ «የአማራ ልማት ማህበር» የሚባሉ አሉ። እነዚህ ማህበራት በየቦታዉ ለልማት ሥራ በሚል ገንዘብ ያሰባስባሉ። የአማራዉ ልማት አማራ የሚላቸዉን ነዉ የሚያነጋግረዉ፣ የትግሬዉ ደግሞ ትግሬዎችን።

አንድ ጊዜ የትግራይ ልማት ማሕበር፣ ርዮት በምታስትምረበት ትምህርት ቤት የገንዘብ ማሰባሰቢያ ትኬቶችን ይሸጣል። አንዱ ትኬት 30 ብር ነበር። በትግራይ፣ መቀመጫ አጥተዉ በመሬት ላይ ተቀምጠዉ የሚማሩ ተማሪዎችን የሚያሳይ ቪዲዮ አሳዩ። እነርሱ ትግሬ፣ አማራ. ኦሮሞ ይላሉ። እርስዎ ግን ሁሉንም ዘር ሳትለይ “ወንድሞቼ፣ እህቶቼ” ትላቸዋለች” ። «ይሄማ መሆን የለበትም» ብላ በቪዴዎ የታዩ ተማሪዎችን ለመርዳት ወሰነች። እርሷ ብቻ 300 ብር አውጥታ አሥር ትኬቶች ገዛች። ሌሎች ጓደኞቿም እንዲገዙ ግፊት አደረገች። ምንም እንኳን ትግሬ ባትሆንም፣ የትግራይ ልማት ማህበሩ ያነጣጠረው ትግሬዎች ላይ የነበረም ቢሆን፣ እርሷ ግን ያየቸው የተማሪዎችን ዘር ሳይሆን፣ ስብእናቸዉን እና ኢትዮጵያዊነታቸውን ነበር።
ርዮትን ያሰሩ ሰዎች፣ «መሰረተ ልማትን ለማፍረስ ፣ በሰዎች ላዩ ጉዳት ለማድረግ የምትፈልግ ፣ አሸባሪ ናት» ነዉ የሚሉን። እንግዲህ በትግራይ ያሉ ተማሪዎች ይመስክሩ።

በአገራችን ትልቅ የኢኮኖሚ ችግር እንዳለ የሚታወቅ ነዉ። ጥቂቶች እላይ ሲመጠቁ፣ አብዛኛዉ ኑሮ ከብዶት፣ በቀን አንዴ እየተመገበ ነዉ የሚኖረዉ። ርዮት አስተማሪ እንደመሆኗ በተማሪዎቿ አካባቢ ያለዉን ችግር ታዉቃለች። ብዙ ጊዜ በጠኔ ሲወድቁ አይታለች። ብዙዎችም እንደ ታላቅ እህት ችግራቸውን ያጫዉቷታል። አቅሟ በፈቀደ መጠን ከማስተማር በተጨማሪ ተማሪዎቿን የምትረዳ ፣ የተከበረችና የተወደደች ምህሩ ነበረች። በጣም ችግረኛ ለሆኑ፣ አሥራ ሁለት ተማሪዎች፣ የሚለብሱት ዩኒፎርም በየአመቱ የምታሰፋ ነበረች።

ርዮትን ያሰሩ ሰዎች፣ «መሰረተ ልማትን ለማፍረስ ፣ በሰዎች ላዩ ጉዳት ለማድረግ የምትፈልግ አሸባሪ ናት » ነዉ የሚሉን። እንግዲህ በአዲስ አበባ ያሉ፣ ርዮት እንደ ታልቅ እህት የረዳቸቸዉና የደገፈቻቸው ተማሪዎች ይመስክሩ።

አንድ ጊዜ ደግሞ እንዲህ ሆነ። አንድ በጣም ጎበዝ የሆነ፣ ተማሪዎ፣ የማትሪክ ዉጤት እንደጠበቀዉ አልመጣለትም። የመንግስት ተቋማት መመደብ አልቻለም። በዚህም ምክንያት በጣም ተስፋ ቆርጦ እራሱን ወደ ማጥፋት ደረጃ ደረሰ። ይሄንን ስትሰማ ቤተሰቦቹን አነጋገረች። ያለዉን ነገር አስረዷት። በጣም ድሃዎች እንደመሆናቸው፣ ልጃቸውን የግል ትምህርት ቤት ከፍለው ሊያስተምሩት እንደማይችሉ ነገሯት። ይህን ወጣት፣ ወጭዉን በሙሉ ሸፍና፣ ዩኒቲ ኮሌጅ ገብቶ እንዲማር አደረግቸው።
እንግዲህ አስቡት ወገኖቼ፣ እንደ ርዮት አለሙ አይነት የተከበሩ፣ አገር ወዳድ፣ ለሰው የሚያዝኑ ኢትዮጵያዉያንን ነዉ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ሽብርተኞች እያለ ወደ ቃሊቲ የሚወረወረው። ዜጎች መልካም በሰሩ፣ የአገርንና የወገንን ጥቅም ባስቀደሙ፣ ለሕዝብ ክብርና ነጻነት በቆሙ፣ ፍትህን በሰበኩ፣ የአገሪቷ ባለስልጣናት የሚሰሩትን ስህተቶችን በደሎች ባጋለጡ ለምንድን ነዉ የሚታሰሩት ? ኢትዮጵያስ እስከምቼ ለልጆቿ ሲኦል ትሆናለች ?

አንዳንድ ሰዎች በጣም ክፉ ከመሆናቸው የተነሳ ሌሎች ሲሰቃዩ የሚደስቱ አሉ። እነዚህ በዉስጣቸው ያለው የሕሊና ድምጽ የማይቃጭልባቸዉ ፣ ርህራሄና ሃዘኔታ የሚባል ነገር የሌላቸው፣ ለስብእና ክብር የማይሰጡ ናቸው። ኢሕአዴግ እየተመራ ያለ በእንደነዚህ አይነት ሰዎች ነዉ። እነዚህ ሰዎች የራሳቸዉን የጥላቻ እርካታ ለማጥገብ ሲሉ በሚሰሩት ግፍ፣ ኢሕአዴግን ወደ ገደል እየወሰዱት ነዉ።

የርዮት አለሙ መታሰር እንደ ፓርቲ ኢሕአዴግ ለሚያደርጋቸው የልማት እንቅስቃሴዎች ምንም አይጠቅምም። በፖለቲካም የበለጠ እንዲጠላ ነዉ እያደረገው ያለዉ። የኢሕአዴግ አባላትና ደጋፊዎች የሚመሯቸውን አክራሪዎች ገፍተዉ እንዲያስወጡ እመክራቸዋለሁ። በአስቸኳይ ርዮት አለሙ እንዲሁም ሌሎች የሕሊና እስረኞችን መፍታት አለባቸው። ቀናት እየጨመሩ በሄዱ ቁጥር ነገሮች እየተወሳሰቡ ነዉ የሚመጡት። ኢሕአዴግ እየመነመነ፣ እነርዮት አለሙ ደግሞ ተወዳችነታቸው እየጨመረ ነዉ የሚመጣዉ።

ርዮት አለሙ፣ አሁን ብትታሰርም፣ ሚሊዮኖች የርዮት አፍ ሆነዉ ድምጻቸዉን ያስተጋባሉ። የሚሊዮኖች የፍትህ ድምጽ የአራት ኪሎ ቤተ መንግስት ግድግዳን እያለፈ፣ ባለስልጣናቱ በተኙበት ይሰሙታል። ያለ ምንም ጥርጥር ርዮት አለሙ፣ እንደ ደራርቱ ቱሉ የኢትዮጵያን አረንጓዴ፣ ቢጫ ቀይ ሰንድቅ አላማ በላይዋ ላይ ለብሳ በክብር ከቃሊቲ ትወጣለች።

Monday 24 November 2014

ለስብሰባ ሲቀሰቅሱ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ተጨማሪ 7 ቀናት ተቀጠረባቸው


የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ጠርቶት ለነበረው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ አርብ ህዳር 5/2007 ዓ.ም በቅስቀሳ ላይ እንደነበሩ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ 7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባቸው፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ም/ሰብሳቢና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ማቲያስ መኩሪያ እና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ሳምሶን ግዛቸው በቅስቀሳ ወቅት ተይዘው አራዳ ፖሊስ መምሪያ የታሰሩ ሲሆን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ችሎት ቀርበው የ7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ወጣቶቹ ‹‹ሽብር በማነሳሳት›› የሚል ‹ክስ› የተመሰረተባቸው ሲሆን ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ ሌሊት ደህንነቶች በተደጋጋሚ በኃይልና በዛቻ እንደሚመረምሯቸው መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡
 
ባለፈው የፍርድ ውሎ ታሳሪዎቹ ህጋዊ እውቅና ለተሰጠው ስብሰባ የቀሰቀሱ መሆኑን ጠቅሰው መታሰራቸው ህገ ወጥ በመሆኑ እንዲፈለቀቁ ቢከራከሩም፤ ፖሊስ ‹‹ሌሎች ግብረ አበሮቻቸው ስላልተያዙ መያዝ አለብን፡፡ እነሱም ከተለቀቁ መረጃ ያጠፉብናል›› በሚል የ7 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተቀባይት አግኝቷል ለዛሬ በቀጠሯቸው መሰረት ፍርድ ቤት ቢቀርቡም ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ አንድ ሳምንት ጊዜ ለፖሊስ ፈቅዶለታል፡፡ በአንጻሩ ታሳዎቹ የቀረቧቸው ቅሬታዎችና መከራከሪያዎች ተቀባይነት ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ጠርቶት ለነበረው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ አርብ ህዳር 5/2007 ዓ.ም በቅስቀሳ ላይ እንደነበሩ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ 7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባቸው፡፡የአዲስ አበባ ከተማ ም/ሰብሳቢና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ማቲያስ መኩሪያ እና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ሳምሶን ግዛቸው በቅስቀሳ ወቅት ተይዘው አራዳ ፖሊስ መምሪያ የታሰሩ ሲሆን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ችሎት ቀርበው የ7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ወጣቶቹ ‹‹ሽብር በማነሳሳት›› የሚል ‹ክስ› የተመሰረተባቸው ሲሆን ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ ሌሊት ደህንነቶች በተደጋጋሚ በኃይልና በዛቻ እንደሚመረምሯቸው መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡ ባለፈው የፍርድ ውሎ ታሳሪዎቹ ህጋዊ እውቅና ለተሰጠው ስብሰባ የቀሰቀሱ መሆኑን ጠቅሰው መታሰራቸው ህገ ወጥ በመሆኑ እንዲፈለቀቁ ቢከራከሩም፤ ፖሊስ ‹‹ሌሎች ግብረ አበሮቻቸው ስላልተያዙ መያዝ አለብን፡፡ እነሱም ከተለቀቁ መረጃ ያጠፉብናል›› በሚል የ7 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተቀባይት አግኝቷል ለዛሬ በቀጠሯቸው መሰረት ፍርድ ቤት ቢቀርቡም ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ አንድ ሳምንት ጊዜ ለፖሊስ ፈቅዶለታል፡፡ በአንጻሩ ታሳዎቹ የቀረቧቸው ቅሬታዎችና መከራከሪያዎች ተቀባይነት ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡
Photo: ለስብሰባ ሲቀሰቅሱ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ተጨማሪ 7 ቀናት ተቀጠረባቸው</p><br />
<p>የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ጠርቶት ለነበረው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ አርብ ህዳር 5/2007 ዓ.ም በቅስቀሳ ላይ እንደነበሩ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ 7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባቸው፡፡ </p><br />
<p>የአዲስ አበባ ከተማ ም/ሰብሳቢና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ማቲያስ መኩሪያ እና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ሳምሶን ግዛቸው በቅስቀሳ ወቅት ተይዘው አራዳ ፖሊስ መምሪያ የታሰሩ ሲሆን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ችሎት ቀርበው የ7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ወጣቶቹ ‹‹ሽብር በማነሳሳት›› የሚል ‹ክስ› የተመሰረተባቸው ሲሆን ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ ሌሊት ደህንነቶች በተደጋጋሚ በኃይልና በዛቻ እንደሚመረምሯቸው መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡</p><br />
<p>ባለፈው የፍርድ ውሎ ታሳሪዎቹ ህጋዊ እውቅና ለተሰጠው ስብሰባ የቀሰቀሱ መሆኑን ጠቅሰው መታሰራቸው ህገ ወጥ በመሆኑ እንዲፈለቀቁ ቢከራከሩም፤ ፖሊስ ‹‹ሌሎች ግብረ አበሮቻቸው ስላልተያዙ መያዝ አለብን፡፡ እነሱም ከተለቀቁ መረጃ ያጠፉብናል›› በሚል የ7 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተቀባይት አግኝቷል ለዛሬ በቀጠሯቸው መሰረት ፍርድ ቤት ቢቀርቡም ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ አንድ ሳምንት ጊዜ ለፖሊስ ፈቅዶለታል፡፡ በአንጻሩ ታሳዎቹ የቀረቧቸው ቅሬታዎችና መከራከሪያዎች ተቀባይነት ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡
- See more at: http://satenaw.com/amharic/?p=2649#sthash.I1JEIjlN.dpuf
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ጠርቶት ለነበረው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ አርብ ህዳር 5/2007 ዓ.ም በቅስቀሳ ላይ እንደነበሩ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ 7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባቸው፡፡የአዲስ አበባ ከተማ ም/ሰብሳቢና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ማቲያስ መኩሪያ እና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ሳምሶን ግዛቸው በቅስቀሳ ወቅት ተይዘው አራዳ ፖሊስ መምሪያ የታሰሩ ሲሆን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ችሎት ቀርበው የ7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ወጣቶቹ ‹‹ሽብር በማነሳሳት›› የሚል ‹ክስ› የተመሰረተባቸው ሲሆን ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ ሌሊት ደህንነቶች በተደጋጋሚ በኃይልና በዛቻ እንደሚመረምሯቸው መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡ ባለፈው የፍርድ ውሎ ታሳሪዎቹ ህጋዊ እውቅና ለተሰጠው ስብሰባ የቀሰቀሱ መሆኑን ጠቅሰው መታሰራቸው ህገ ወጥ በመሆኑ እንዲፈለቀቁ ቢከራከሩም፤ ፖሊስ ‹‹ሌሎች ግብረ አበሮቻቸው ስላልተያዙ መያዝ አለብን፡፡ እነሱም ከተለቀቁ መረጃ ያጠፉብናል›› በሚል የ7 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተቀባይት አግኝቷል ለዛሬ በቀጠሯቸው መሰረት ፍርድ ቤት ቢቀርቡም ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ አንድ ሳምንት ጊዜ ለፖሊስ ፈቅዶለታል፡፡ በአንጻሩ ታሳዎቹ የቀረቧቸው ቅሬታዎችና መከራከሪያዎች ተቀባይነት ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡
Photo: ለስብሰባ ሲቀሰቅሱ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ተጨማሪ 7 ቀናት ተቀጠረባቸው</p><br />
<p>የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ጠርቶት ለነበረው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ አርብ ህዳር 5/2007 ዓ.ም በቅስቀሳ ላይ እንደነበሩ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ 7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባቸው፡፡ </p><br />
<p>የአዲስ አበባ ከተማ ም/ሰብሳቢና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ማቲያስ መኩሪያ እና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ሳምሶን ግዛቸው በቅስቀሳ ወቅት ተይዘው አራዳ ፖሊስ መምሪያ የታሰሩ ሲሆን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ችሎት ቀርበው የ7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ወጣቶቹ ‹‹ሽብር በማነሳሳት›› የሚል ‹ክስ› የተመሰረተባቸው ሲሆን ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ ሌሊት ደህንነቶች በተደጋጋሚ በኃይልና በዛቻ እንደሚመረምሯቸው መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡</p><br />
<p>ባለፈው የፍርድ ውሎ ታሳሪዎቹ ህጋዊ እውቅና ለተሰጠው ስብሰባ የቀሰቀሱ መሆኑን ጠቅሰው መታሰራቸው ህገ ወጥ በመሆኑ እንዲፈለቀቁ ቢከራከሩም፤ ፖሊስ ‹‹ሌሎች ግብረ አበሮቻቸው ስላልተያዙ መያዝ አለብን፡፡ እነሱም ከተለቀቁ መረጃ ያጠፉብናል›› በሚል የ7 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተቀባይት አግኝቷል ለዛሬ በቀጠሯቸው መሰረት ፍርድ ቤት ቢቀርቡም ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ አንድ ሳምንት ጊዜ ለፖሊስ ፈቅዶለታል፡፡ በአንጻሩ ታሳዎቹ የቀረቧቸው ቅሬታዎችና መከራከሪያዎች ተቀባይነት ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡
- See more at: http://satenaw.com/amharic/?p=2649#sthash.I1JEIjlN.dpuf

Saturday 22 November 2014

30 ደቂቃዎችን በዝዋይ እስር ቤት (ግዞት) ‹‹በብርቱ ታምሜያለሁ›› አበበ ቀስቶ



ዝዋይ የሚገኙ የፖለቲካና የህሊና እስረኞችን በቦታው ተገኝቼ ለመጠየቅ እቅድ ከያዝኩ ረዘም ያሉ ቀናት አልፈዋል፡፡ እንዲያውም ጉዞው ከወዳጆቼ ጋር ሰብሰብ ብለን ቢሆን እንደሚመረጥ ተነጋግረንበት ነበር፡፡ ሆኖም ግን የዕለት ከዕለት ሩጫችን አላወላዳ ብሎን ባቀድነው ጊዜ ወደ ዝዋይ መጓዝ ሳንችል ቆይተናል፡፡ አርብ ህዳር 12/2007 ዓ.ም ግን እንዳሰብነው ሰብሰብ ብለንም ባይሆን በመጨረሻ አብሮኝ ከተጓዘው የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ባልደረባ ወጣት ፍቅረማርያም አስማማው ጋር ከአዲስ አበባ በጠዋት ተነስተን ወደ ዝዋይ አምርተን ለ30 ደቂቃዎች ያህል የናፈቅናቸውንና የናፈቁንን እስረኞች ልንጎበኝ በቅተናል፡፡

ዝዋይ ለመድረስ ከ2 ሰዓት በላይ ጉዞ ማድረግ ነበረብን፤ በጠዋት ቃሊቲ መነሐሪያ በመገኘት የዝዋይን ትራንስፖርት ለመያዝ ስንገኝ መልካም አጋጣሚ ተከሰተ፡፡ አጋጣሚው እኛ ወደምንሄድበት ዝዋይ እስር ቤት ሊሄዱ የተሰናዱትን የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወንድም እና ሌላ የስራ ባልደረባውን ያገናኘ ነበር፡፡ ቁጥራችን መጨመሩ ለእኛም ለምንጠይቃቸው እስረኞችም መልካም ነበር፡፡
ከተማዋ እንደደረስን ወደ አንድ አብረውኝ የተጓዙት ወዳጆቼ የሚያውቁት ቤት አመራን፤ ቡና በፔርሙስ ለመያዝ፡፡ ‹‹ተመስገን ደሳለኝ በእጅጉ ቡና ይወዳል አለኝ›› ታናሽ ወንድሙ፡፡ ቡናውን አስቀድተን ከከተማዋ ትንሽ ወጣ ብሎ ወደሚገኘው እስር ቤት አመራን፡፡ ጉዞው ደግሞ በጋሪ ነበር፡፡ ወደእስር ቤት የሚወስደው መንገድ እጅግ አቧራማ በመሆኑ ተጓዦች አቧራውን መልበሳቸው እሙን ነው፡፡ በእግር ለመጓዝ የፈቀደ ካለ ድልህ ቲባን በጫማዎቹ ልክ ይዋኝበታል፡፡ የእኛ ጉዞ በጋሪ ቢሆንም ከአቧራው ማምለጥ ግን አይቻልም፡፡

እስር ቤቱ በር ደርሰን ከጋሪ እንደወረድን ወደጥበቃዎቹ ቀርበን የምንጠይቃቸውን እስረኞች ስም ሰጥተን የእኛን ሙሉ አድራሻ አስመዘገብን፡፡ የምንጠይቃቸውን እስረኞች ስናስመዘግብ ‹‹ምኑ ነህ?›› የሚለው ጥያቄ ይነሳል፡፡ ጓደኛ፣ ወንድም፣ ዘመድ…እያልን አስሞላን፡፡ መዝጋቢ ፖሊሶቹ ቀና እያሉ በጥያቄ ያዩናል፡፡ ኢትዮጵያውያን ወገኖች ‹ጓደኛ፣ ወንድም፣ ዘመድ…› ተብለው እንጂ ሌላ በምን ይገለጻሉ ታዲያ! በዚህ መሰረት የአራት እስረኞችን ስም አስመዘገብን፤ እነሱም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ብ/ጄ አሳምነው ፅጌ፣ ፖለቲከኞቹ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ ናቸው፡፡ ጥብቅ ፍተሻውን አልፈን ልናያቸው የጓጓንላቸውን እስረኞች ወደምንገናኝበት ቦታ አመራን፡፡

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ቦታው ላይ ስንደርስ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በሶስት ፖሊሶች ተከብቦ ቀድመውን ከደረሱ ወዳጆቹ ጋር እያወራ ነበር፡፡ ከአጥር ወዲህ እና ወዲያ ማዶ ሆነን ግማሽ አካል ተቃቅፈን ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ ደስ አለን፤ ተመስገንም ደስታው በመላ ፊቱ ሲበራ ተመለከትን፡፡ በደስታው ድጋሜ ደስ ተሰኘን፡፡ በእኛ በኩል ትንሽ ስለ ጤንነቱ፣ በእሱ በኩል ስለቤተሰብ እና ስለእኛ ደህንነት ተጠያየቅን፡፡ በመካከላችን ትንሽ ዝምታ ሰፈነ፡፡ እኛም ተመስገንም ቀና ብለን ፖሊሶችን ተመለከትን፡፡ ከዚያም ተመስገን ጥያቄ ወረወረ፡፡

‹‹ውጭ ያለው እንዴት ነው? አንድነትና ሰማያዊ….›› ተሜ የጀመረውን ሳይጨርስ ሁለቱ ፖሊሶች አንባረቁብን፡፡
‹‹ፖለቲካ አታውራ! እናንተ ፖለቲካ አታውሩ! ዝም ብላችሁ ሌላ ሌላ አውሩ!…›› አሉን ፖሊሶች አንዴ እኛን አንዴ ከአጥር ማዶ የተቀመጠውን ተመስጋንን እየተመለከቱ፡፡ የፖለቲካ ድርጅቶችን ስም መጥራት ፖለቲካ ማውራት ሆኖ ተሰማቸው፣ እዚያ ለነበሩ ፖሊሶች፡፡ የአንድነትን እና የሰማያዊን ስም ጠርቶ ተሜ ምን ሊያወራ እንደፈለገ እንኳ ለመስማት አልተዘጋጁም፡፡ በየዕለቱ መረጃ የሚያነፈንፍ፣ ያገኘውን መረጃ ደግሞ ወደህዝብ የሚያደርስ ሙያ ላይ እንደነበር ለእነሱ አልገባቸውም፡፡ አዎ መረጃ ምን ያህል እንደሚርብ ለፖሊሶቹ የተገለጸላቸው አልመሰለኝም፤ ለዚያውም ለጋዜጠኛ፡፡
ተሜ ጋር ልናወራ ያሰብነው ብዙ አብይ ጉዳዮች ቢኖሩም ክልከላው የሚያወላዳ አልሆነም፡፡ በበኩሌ በኋላ ተመስገን ላይ ሊያደርሱበት የሚችሉት ጫና ይኖራል ከሚል ርዕሱን መቀየሩን መርጬ ነበር፡፡ ተመስገን ግን ‹‹እናውራበት›› በሚል ትንሽ ከፖሊሶቹ ጋር ተከራከረ፡፡ ተሜ ድፍረቱ በብዕሩ ብቻ አይደለም፡፡ መብቱን ለማስከበር ወደኋላ የማይል ብርቱ ሰው መሆኑን ከሁኔታው አነበብኩ፡፡

በመሐል ላይ ሌሎች እስረኞችን እንዲጠሩልን ስም ዝርዝር ሰጥተን ስለነበር ሲዘገዩ ጊዜ ‹‹እነ ክንፈሚካኤልና አሳምነውን ጥሩልን እንጂ!›› አልናቸው፡፡ አንደኛው ፖሊስ ቆጣ ብሎ ‹‹ቆይ እሱ ጋር ጨርሱ!›› አለን፡፡ ከተመስገን ጋር ያለንን ቆይታ ማለቱ ነበር፡፡ እኛም እስኪመጡ እንደምንጨርስ በመጥቀስ አስጠሩልን አልናቸው፡፡ በዚህ መሐል ትንሽ ጭቅጭቅ ድጋሜ ተፈጠረ፡፡ ‹‹እንዲያውም ስማቸውን በትክክል አልጻፋችሁም፤ ስለዚህ አንጠራላችሁም አሉን፡፡›› እኛም የሰጠናቸውን የስም ዝርዝር የጻፉት የራሳቸው ባልደረቦች እንጂ እኛ አለመሆናችንን ጠቅሰን ነገርናቸው፡፡

ካፈርኩ አይመልሰኝ በሚመስል መልኩ አንጠራላችሁም አሉን፡፡ ‹‹በቃ አምጣው እንደገና አስተካክለው እንዲጽፉ አድርገን እናምጣው!›› አልናቸው፡፡ በእርግጥ ትክክለኛ ምክንያታቸው የስም ስህተት እንዳልሆነ እናውቅ ነበር፡፡ ሲጀመር አሳምነው ፅጌን ከእኛ ከወጣቶች ይልቅ እነሱ ከበረሃ ጀምረው ጠንቅቀው ያውቁታል፡፡ ስለሆነም ‹‹እገሌ የሚባል ሰው የለም፤ እዚሁ ተወለደ ካላላችሁን›› እያሉ ሲናገሩ በውስጤ እየሳቅሁ ነበር፡፡ እንዲያውም፣ ‹‹አዲስ ታሰረ ካላላችሁ በቀር አዲስ እንደማይወለድ ታውቃላችሁ፤ ሴትና ወንድ የት ይገናኛሉና ነው!›› አልኩ፡፡ የግዳቸውን ፈገግ አሉ፡፡

በዚህ መሰል ጭቅጭቅ ከተመስገን ጋር ያለንን ጊዜ ተሻሙብን፡፡ ይህ የገባው ተመስገን ደሳለኝ በጭቅጭቁ ጣልቃ ገብቶ፣ ‹‹ሰዎቹ ከአዲስ አበባ ነው የመጡት፡፡ ስለሆነም ከሩቅ ቦታ መጥተው ሳያገኟቸው ቢመለሱ ደስ አይልም›› አላቸው፡፡ ወዲያው አንደኛው ወደ እኛ ዞሮ ‹‹ናትናኤል መኮንንን የት ነው የምታውቀው?›› አለኝ፡፡ ጥያቄውን ወደጓደኛየም ወሰደው፡፡ ‹‹ይህን ጥያቄ ምን አመጣው›› ብዬ ጥያቄውን በጥያቄ ከመመለሴ፣ ጋዜጠኛ ተመስገን ቀበል አድርጎ ‹‹ኢትዮጵያዊ ወገኑን ሳያውቀውም ቢሆን መጠየቅ ይችላል!›› አለ፡፡ ተመስገን ተቆርቋሪነቱ ደስ ይላል፡፡ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ እስረኞቹ ሊጠሩልን ስምምነት ላይ ደረስን፡፡ እስኪመጡ ድረስም ከተመስገን ደሳለኝ ጋር ‹‹ከፖለቲካ ውጭ›› ባለ ድባብ ጨዋታችንን ቀጠልን፡፡

ተሜ ስለሚዲያ አብዝቶ ጠየቀኝ፡፡ ያለው ሁኔታ ከሚያውቀው እውነታ እንዳልተለወጠ ገለጽኩለት፡፡ ከዚያም ወደወንድሙ ዞሮ ስለቤተሰባዊ ጉዳዮች ሲያወራ ዓይኖቼን ወዳስጠራናቸው እስረኞች መምጫ አማትር ያዝኩ፡፡ ብ/ጄ አሳምነው ፅጌ፣ ፖለቲከኞቹ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ ከርቀት አንድ ላይ ሆነው ሲመጡ ተመለከትኩ፡፡ ከፖሊሶች ጋር ባለው እሰጣ ገባ ስሜቴ ተረብሾ ነበር፡፡ ይህ ስሜቴ ግን ድንገት ሶስቱ ሰዎች ከርቀት በፈገግታ ታጅበው ወደ እኛ ሲመጡ ሳይ በንኖ ጠፋ፡፡

ሞገደኛው አበበ ቀስቶ እና የተጓደለው ጤናው ጉዳይ

ብ/ጄ አሳምነው ፅጌ፣ ፖለቲከኞቹ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ (አበበ ቀስቶ) ካለንበት ስፍራ ደርሰው ተቃቅፈን ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ አቤት እንዴት ደስ እንዳላቸው! ሙሉ ፊታቸው ያበራል፡፡ ‹‹እኛን ልትጠይቁ መጣችሁ?›› እያሉ በደስታ ተቁነጠነጡ፡፡ እውነት ለመናገር ደስታው የእነሱ ሳይሆን የእኛ ነበር፡፡ በበኩሌ በእስር ላይ ያሉ ወንድም እህቶቼን መጠየቅ ምን አይነት የህሊና እረፍትና ደስታ እንደሚሰጠኝ የማውቀው እኔው ነኝ፡፡

ይህ ደስታችን ታዲያ ተመስገን ደሳለኝ ጋር በነበረው መልኩ ድንገት ደፈረሰ፡፡ ፖሊሶቹ አሁንም እሳት ለበሱ፡፡ ከውጭ ያለውን ነገር የተራቡት እነ ክንፈሚካኤል እነዚያን የፓርቲ ስሞች ጠቅሰው ጥያቄ ሰነዘሩ፡፡ ‹‹አንድነትና ሰማያዊ…›› ካፋቸው ቀልበው ፖሊሶቹ አንባረቁ፡፡ ‹‹አንተ ፖለቲካ አታውራ!›› በማለት ያዙኝ ልቀቁኝ አሉ፡፡ እንዲያውም ምንም ሳናወራ ተነሱና ግቡ አሏቸው፡፡ በዚህ ጊዜ አበበ ቀስቶ በኃይለ ቃል መልሶ ፖሊሶቹ ላይ አፈጠጠ፡፡ ፖሊሶቹ ትንሽ ድንግጥ በማለት ‹‹ሌላ ሌላ አውሩ በቃ!›› አሉን፡፡
ዝዋይ እስር ቤት ካሉ እስረኞች ጋር የሚገናኝ ጠያቂ ‹‹ደህና ነህ፣ እንዴት ነህ…›› ብቻ ብሎ እንዲመለስ ነው የሚፈለገው፡፡ ከሁሉም ጋር ያለውን ማህበራዊና የጤና ሁኔታ አንስተን ስንጨዋወት አበበ ቀስቶ ወደእኔ አንገቱን ሰገግ አድርጎ ‹‹አሞኛል፣ በብርቱ ከታመምኩ ቆይቻለሁ›› አለኝ፡፡ ከዚህ ቀደም በጤናው ላይ እከል እንደገጠመው አውቅ ነበር፡፡ የአሁኑ ህመሙ ምን ይሆን በሚል የበለጠ እንዲነግረኝ እኔም አንገቴን ሰገግ አድርጌ ጆሮዎቼን ሰጠሁት፡፡

‹‹የሚያመኝ ይሄን የጆሮየን አካባቢ ነው፡፡ በብርቱ ታምሜያለሁ፡፡ አብሮኝ የሚተኛው ናትናኤል መኮንን ባይሆን ኑሮ ምን እንደሚውጠኝ አላውቅም፡፡ ቁስል አበጅቶ መጥፎ ጠረንም ፈጥሯል›› አለኝ፡፡ እኔም የህመሙ ምክንያት ምን እንደሆነ ጠየቅኩት፡፡
‹‹ያኔ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ እያለሁ የደረሰብኝ ድብደባ ነው ዛሬም የሚያሰቃየኝ›› አለኝና ከዚያ ወዲህ እንዴት እየተሰቃየ እንዳለ አስከትሎ አስረዳኝ፡፡ እኔም ‹‹ህክምና…›› ሳልጨርሰው ተቀበለኝ፡፡ ‹‹ህክምና የሚባለውን ተወው፡፡ ይሄው ስንት ጊዜ እንዲያሳክሙኝ የምጮኸው! ሰበቡ አያልቅባቸውም! ምንም በቂ ህክምና አላገኘሁም፡፡ መቼስ….›› ብሎ ያ ከደቂቃዎች በፊት በሳቅ፣ ከዚያም በንዴት ውስጥ የነበረው ቆፍጣናውና ቀጭኑ ፖለቲከኛ በትካዜ አንገቱን ደፋ፡፡ ውስጤ በማላውቀው ስሜት ተላወሰ፡፡ አበበ ቀስቶ በስካርቭ ጨርቅ ሙሉ ጆሮ ግንዱን ጠምጥሞ የመጣበት ምክንያት ገባኝ፡፡ ቁስሉን ለመሸፈን ነው፡፡
ከአበበ ጋር ይህን ስናወራ ሌሎች ወዳጆቼ ከእነ አሳምነው እና ናትናኤል ጋር ስለተለያዩ ጉዳዮች (‹ከፖለቲካ ውጭ›) እያወሩ ነበር፡፡ ‹‹እስኪ ደግሞ ከእነሱ ጋር አውራ፣ ጊዜህን እኔ ብቻ ወሰድኩብህ›› አለኝ አበበ ቀስቶ ወደ ናትናኤልና አሳምነው እየተመለከተ፡፡ እኔም በአለችው ትንሽ ደቂቃ ከሌሎቹ ጋር ጨዋታ ያዝኩ፡፡ በዚህ መሐል ግን ቀልቤ የአበበ ቀስቶ ጤንነት ላይ ነበር፡፡ እንዴት ሰው አካሉ እንዲያ ቆስሎ ህክምና አይሰጠውም?

ስንብት

በፖሊሶች ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ ለሰላሳ ደቂቃዎች ብቻ የነበረን ቆይታ ማብቃቱን ስንረዳ 30 ደቂቃ ምን ያህል አጭር እንደሆነ ተገነዘብን፡፡ ስድስት ሰዓት ደርሶም ስለነበር መለያየታችን ግድ ሆነ፡፡ ስንገናኝ እንዳደረግነው ሁሉ እንደገና ለስንብትም ተቃቀፍን፡፡ በእቅፎቻችን መካከል የተሰነቀረው አጥር ደግሞ የመለያየታችን ደንቃራነት ማሳያ ነበር፡፡
ከእነ አበበ ቀስቶ ጋር ያለኝን ስንብት ጨርሼ ወደ ተመስገን ደሳለኝ ስጠጋ በእጆቹ አንገቴን ሳብ አድርጎ ወደ ጆሮዬ ጠጋ በማለት ‹‹ስርዓት ሲፈርስ የሚያደርገውን ያጣል፡፡ ስርዓቱ እየፈረሰ ነው›› አለኝ፡፡ ምንም አልመለስኩለትም፡፡ በእጆቼ ትከሻውን መታ መታ በማድረግ የተናገረውን መስማቴን አረጋገጥኩለት፡፡

Source: ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia

ፕሮፌሰር በየነ ጼጥሮስ ዲያስፖራውን ወቀሱ


ከአንድ ዓመት ላላነሰ ጊዜ በአሜሪካን ሀገር በቺካጎ ከተማ በሚገኝ አንድ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሲያስተምሩ ቆይተው በቅርቡ ወደሀገር ቤት መመለሳቸውን የተናገሩት የወቅቱ የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ዲያስፖራውን ወቅሰዋል።

ፕሮፌሰሩ በዛሬው ዕለት ለንባብ ከበቃው መንግስታዊው ዘመን መጽሄት የጥቅምት 2007 ዕትም ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ “ዲያስፖራው ተስፋ የቆረጠና የተናደደ ነው፡፡ ተስፋ ስለቆረጠና ስለተናደደ ገዥው ፓርቲ የሚሰራው ሥራ ሁሉ ጥፋት ነው ብሎ ራሱን አሳምኖ ቁጭ ያለ ነው፡፡ በዚህም የሚናደድና የሚንቦገቦግ ነው፡፡ እናም ከእነዚህ ጋር ውይይት ማድረግ አይቻልም፡፡» ብለዋል። ፕሮፌሰር በየነ በዚሁ ቃለምልልሳቸው “ዲያስፖራውን ለመምከር እንሞክራለን» ካሉ በኃላ በአሜሪካ ቆይታቸው ወቅት እርሳቸው ንግግር እንዲያደርጉ የተጋበዙ ሰዎች እንዲበተኑ እንደተደረገ ተናግረዋል።

መጽሄቱ በእሳቸው ላይ ይህ ለምን እንደተደረገ ጠይቆአቸው በሰጡት ምላሽ “እኔ እውነቱን ስለማወጣ ነው» የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

ኢህአዴግ በአንድ በኩል እኛን ትክክል ባልሆነ ምስል ያስቀምጠናል ያሉት የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ዲያስፖራው ደግሞ የባሰ በመሆኑ መቸገራቸውን ተናግረዋል፡፡

Source:: Ethsat

እኔም ሃና ነኝ ( ሄኖክ የሺጥላ )


unnamed 
ሀና ላይ በተፈጠረው ነገር እጅግ አዝኛለሁ ፣ ሃና ላይ የደረሰው ነገር ሀገሬ ላይ እየደረሰ ያለውን ነገር እንዳስታውስ ነው ያረገኝ ። ሃናስ ታክሲ ውስጥ ነው የተደፈረችው ፣ ሀገሬ ግን በየጎዳናው ፣ ህገ ወጥ በሆነ የመሬት ንግድ ፣ ህገ ወጥ በሆነ እስር ፣ ህገ ወጥ በሆኑ ሕጋዊ ሌቦች ፣  ህገ ወጥ በሆነ ዶዘር ፣ ህገ ወጥ በሆነ ዱርዬ ቡድን እዚም እዛም ( ጭኑዋም ተረከዙዋም ፣ እጁዋም ወገቡዋም  ተደፍሮዋል ) ።
 
እንድ ነገር ለማከል ብዙ ሰዎች ” እኔም ሀና ነኝ ” ማለት ጀምረዋል ፣ ያዝልቅላችሁ ፣ ታዲያ በነካ እኔነታችሁ ” እኔም ራሴ እኔ ነኝ !” በሉኝ ።  ክርስቶስ  ተመልሶ ቢመጣ ” ሰው ራሱን ሳይሆን ሌላ ሰው መሆን እንደምን ይቻለው ይሆን ?” ብሎ ያስተምር ነበር ። ለነገሩ ድጋሚ ክርስቶስ መጥቶ ለኛ ቢሰቀል፣ ለምን ተሰቀለ ብለን ከስቅለቱ እና ከደሙ ተምሳሌተ ትምህርት በመውሰድ ፈንታ ” እኔም ክርስቶስ ነኝ !” የምንል ይመስለኛል ። ከቻልን ያልሆነውን  አንሁን ፣ ወይ ደሞ ነን ስንል ሆነን  ብቻ ከሆነ ይሁን ።
 
አንድ ጥያቄ አለኝ ።  የሃና ጉዳይ ያገባኛል ያሉ ድህረ ገጾች ” የሀገሬ ጉዳይ ያገባኛል ማለት እንዴት ተሳናቸው ?” በሃና ስቃይ የተቆጡ እና ያነቡ አይኖች እንዴት ስለ  ህጻን ነብዩ ለመናገር ፈሩ ?  ሀና ፍትህ ያስፈልጋታል ያሉ አንደበቶች  እንዴት የሽብሬ ወይም የ በቀለ ገርባ ወይም የእስክንድር መታሰር  ብሎም የእስሩ ኢ ፍትሃዊነት አልታይ አላቸው ? ከሀናነት በፊት እንዴት ራሳቸው ፍትህ እንደሚያስፈልጋቸው መጠየቅ አቃታቸው ። ሃናን ነኝ ስንልስ ምን ማለታችን ነው ? ሃና ላይ የደረሰው እኔ ላይ እንደደረሰ ያህል ነው ማለት መሰለኝ ? ይደለም ? ከሆነ ዘንዳ ታዲያ  “ታላቁ” ( በትምህርተ ጥቅስ ውስጥ ይሁን ታላቁ  የሚለው ቃል )  አዎ ታላቁ  የገነት ሰይጣን ክርስቶስን ” እስኪ ይሄን ድንጋይ ዳቦ አድርገው?” ሲለው ክስቶስ ” ሰው በእሕል ብቻ እንደማይኖር ! ” ያስረዳዋል ! እኔ ከክርቶስ የተማርኩት ይህንን ነው፣  ነጻነት እኔም አከሌን  ነኝ  በማለት አይገኝም ፣ በመሆን ብቻ !!! አንዳንድ ሰዎች ከክርስቶስ ተማርን ብለው የሚሉት ስለ ገነት ማሰብን ነው ። ሰው ሆይ አጠገብህ ያለውን ገሀነም የሙጥኝ ብለህ እንዴት ስለ ገነት ታወራልህ ? ሰው ሆይ ለኢትዮጵያም እንደ ሃና  እንጮኸላት ዘንድ ኢትዮጵያስ  ሀገርህ ታክሲ ውስጥ ትደፈር ወይ ? አደጋ የማያደርስብንን ነገር ብቻ እየመረጥን የነጻነት እና የመብት ተሙዋጋች መምሰል ማስመሰሉን እናቁም ። አዎ የሃና ቁስል ፣ በተደፈረችበት ሰዓት ያሰማችው ጩኸት ፣ የፈሰሰው ደሟ ሁሉም ያማል ፣ ያስቆጫል ፣ ያበሳጫል ። ግን ታዲያ እኮ  ፍትህ ላንድ ሰው ከተጉዋደለ ለሁሉም እንደተጉዋደለ ነው ። እኔ ሃናን ነኝ ስትል ” በእውነት ግን ነኝ ወይ  ብለህ ራስህን  ለመጠየቅ አንድ ሰከንድ ይኑርህ ” እኔ ክርስቲያን ነኝ ስትልም እንዲሁ ፣ እኔ ሙስሊም ነኝ ስትልም እንዲሁ ። እያሳሰበን ያለው የፍትህ መጉዋደል ሳይሆን የተጉዋደለው ፍትህ ለመጮህ ይመቻል ወይስ አይመችም የሚለው ስለመሰለኝ ነው ። አጠገብህ ያለውን ወንድምህን ሳትወድ እኔን ያላየከውን እንዴት ልትወድስ ትችላለህ ያለው አሁንም  ክርስቶስ ነው ! በ ፌስ ቡክ ገጾቻችን ላይ የለጠፍናት ሃና አሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ ያለበትን የ ሞራል ውድቀት እና የስርዓቱን ዋልጌነት ያሳያል ብላችሁ መቼም ተሯሩጣችሁ እንደማታነሱት ነው፣ የሃና ደም የስርዓቱ ጭፍግግ የሞራል ድቀት ያፈሰሰው ድንግልና ነው፣ ሃና የተደፈረችው ሳትወለድ ነው ፣ ሃና የተደፈርችው የዛሬ 23 ዓመት ነው ፣ ሃና ክብሩዋ የተዋረደው ፣ ጭኑዋ በጉልበት የተፈለቀቀው ዛሬ አይደለም ፣ ትናንት ነው ፣ አጉራ ዘለል ፣ ጥራዝ ነጠቅ ፣ እና ቦዘኔ ስርዓት እና መሪ ኢትዮጵያን መምራት የጀመሩ ቀን ነው ፣ የሃና ቀሚስ የላላው ። የሃና እናት መቀነት የተፈታው ፣ በ ሬዲዮና በቴሌቪዥን ሕዝቡን የሚሳደብ መሪ የተፈጠረ ለት ነው ፣ ሃና ከተደፈረች ቆይታለች ። ሃናን የሚደፍር ስብእና ያለው ትውልድ ሲፈጠር ፣ እንደዛ አይነት ትውልድ ኮትኩቶ ያሳደገ ስርዓት ሲፈጠር ሃና ተደፍራለች ።  ዛሬ ብዙ ሀናዎች ታስረዋል ፣ ብዙ ሃናዎች ተገድለዋል ፣ ብዙ ሃናዎች ገና ይታሰራሉ። ወይንሸት ማን መሰለች ሃና እኮ ነች ፣ ርዮት ማን መሰለች ሃና ራሷ ነች ። እና ሃና  ነን ስንል   የሚያሳስር እና የማያሳስር እየመረጥን ሳይሆን የሆነውን እና የሆ—ነውን መሆን አለበት ። ነጻነታችንን ካላስመለስን ሀገር ሃና ትሆናለች መርዎቹዋ ደፍሪዎቹዋ !!!!
 
አትርሱት  ሕዝብ በቁጥርም በመንፈስም ከመንግስት ይበልጣል ስለዚህ   ሕዝብ ከቆረጠ  ያሸንፋል ። ጊዜ የመከራ መለኪያ ቁና ቢሆን እንጂ ያለመቻላችን መገለጫ አይሆንም ! እንበርታ !!!! ከ ጨቁዋኞቹ ሳይሆን ከተጨቁዋኞቹ ጎን መቆም ነው ሃናነት ፣ ሀናነት ትግል ነው ፣ እምቢ ማለት ነው ፣ ውስጡ ሞት ቢኖርበትም !  እኔ ሃናን ነኝ ስንል ፣ በሞት ጥላ ስር እንኩዋ ብሄድ ሞትን አልፈራም ብሎ ማለት ነው ።  አንድ ወዳጄ እንዳለው ”  ኢትዮጵያና ህዝቦቿ ተደፍሯል! ዴሞክራስ፣ መልካም አሥተዳደር፣ ፍትህ፣ ነፃ ምርጭ እና የህግ የበላይነት ያልተከበረበት አገር አገርቷም ህዝቧም በግዳጅ የተደፍሩ ናቸው።”

Friday 21 November 2014

ሰበር ዜና - የአ.አ አስተዳደር ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ሲባል በሰማያዊ ፓርቲ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ አለ

የአ.አ አስተዳደር ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ሲባል በሰማያዊ ፓርቲ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ አለ

• ‹‹ማስጠንቀቂያውን እንደ ቁም ነገር አንቆጥረውም›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት
• ‹‹ስርዓቱ ምን ያህል ዝቅጠት ውስጥ እንደገባ ያሳያል›› አቶ ግርማ በቀለ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ሰማያዊ ፓርቲ ያስተባበረው የ9ኙ ፓርቲዎች የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ፀረ ህገ መንግስት በመሆኑና ነዋሪዎችን ሰላምና ፀጥታ በማወኩ በቀጣይ ተመሳሳይ እንቅስቃሴ ካደረገ ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ሲባል እርምጃ እወስዳለሁ ሲል አስጠነቀቀ፡፡

አስተዳደሩ ትናንት ህዳር 11/2007 ዓ.ም በጻፈው ደብዳቤ፤ ህዳር 6 ቀን ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል በሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ለህዝብ የተሰራጨው በራሪ ወረቀት ህገ ወጥ መሆኑን፣ ህዳር 7/2007 ዓ.ም በኢንጅነር ይልቃል ጌትነት መሪነት ሊደረግ የነበረው አደባባይ ስብሰባ ህገ ወጥ እንደነበርና በወቅቱ የስብሰባው ተሳታፊዎች ከፖሊስ ጋር ግብ ግብ ከመግጠማቸውም በተጨማሪ የአካባቢውን ህዝብ ሰላምና ፀጥታ አውከዋል ሲል ከሷል፡፡ አስተዳደሩ አክሎም ፓርቲው የአደባባይ ብጥብጥና ሁከት በመፍጠሩ እርምጃ እወስዳሉ ሲል ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ልኳል፡፡

በሌላ በኩል ሰማያዊ ፓርቲ በቀን 5/3/2007 ዓ.ም ለአስተዳደሩ የእውቅና ደብዳቤ ያስገባ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን የሰማያዊ ፓርቲና የትብብሩ አመራሮች አስተዳደሩ የላከው ደብዳቤ ከገዥው ፓርቲ ፍርሃት የመነጨ በመሆኑ ከእንቅስቃሴያቸው እንደማይገታቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብርና የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ደብዳቤው ስርዓቱ የደረሰበትን መጠነ ሰፊ የፍርሃት ደረጃና ትግሉን ይበልጥ አጠናክረን መቀጠል እንዳለብን የሚያሳይ ነው ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ማስጠንቀቂው የደረሰው ሰማያዊ ፓርቲና የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ‹‹የረዥም ጊዜ የመንግስት ታሪክ ባላት አገር የከተማ አስተዳደር ነኝ ያለ አካል እንዲህ አይነት ደብዳቤ መጻፉ ኢትዮጵያ ምን ያህል ውድቀት እንደገጠማትና እኛም እንደ ህዝብ የውረደት ካባ መከናነባችን በግልጽ የሚያሳይ ነው፡፡ እንደ ሰማያዊ አሊያም የትብብሩ ሊቀመንበርነት ሳይሆን እንደ አንድ ይህን ያህል ውርደት እንደገጠማት አገር ዜጋ ሀፍረት ይሰማኛል፡፡›› ሲሉ አስተዳደሩ የላከው ደብዳቤ ላይ አስተያየታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ማስጠንቀቂያው በቀጣይ የፓርቲውም ሆነ የትብብሩ እንቅስቃሴ ላይ የሚያመጣው ችግር ካለ በሚል ለኢንጅነር ይልቃል ላነሳነላቸው ጥያቄም ‹‹ደብዳቤው የኢህአዴግ ፍርሃት ገደብ መልቀቁንና ትግሉም ይበልጥ መጠናከር እንዳለበት የሚያሳይ ነው፡፡ ኢህአዴግ ሰላማዊ ህዝባዊ እንቅስቃሴን ብቻ ሳይሆን የራሱን ጥላም አለማመን ደረጃ ላይ መድረሱን ያሳያል፡፡ እኛ ይህን የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንደቁም ነገር አንቆጥረውም፡፡ ይበልጡንም ለትግሉ በተጠናከረ መንገድ ንድንነሳሳ ይገፋፋናል›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በተመሳሳይ የትብብሩ ፀኃፊና የኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ግርማ በቀለ ‹‹ማስጠንቀቂያው ትብብሩ በየሳምንቱ ያቀዳቸውን መርሃ ግብሮች ለማደናቀፍ ያለመ ነው፡፡ ከአንድ የመንግስት መስሪያ ቤት እንዲህ አይነት አሳፋሪ ደብዳቤ መጻፉ ስርዓቱ ምን ያህል ዝግጠት ውስጥ እንደገባ ያሳያል፡፡ ሆኖም ማስጠንቀቂያው ከእንቅስቃሴያችን አይገታንም፡፡ እንዲያውም ለዚህ የስርዓቱ ዝቅጠት የሚመጥን ስልት ነድፈን በጋራ እንድንሰራ ያደርገናል፡፡›› ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በመርጫ “ለመሳተፍ” ጋዜጣዊ መግለጫ ለምን ? (ከይድነቃቸው ከበደ)


“አንደነት ፓርቲ” እንዲሁም ሌሎች የጉዳዩ ባለቤት የሆኑት አብዛኛው የተቃዋሚ ፓርቲዎች ከዚህ ቀደም ‹‹የፖለቲካ ምህዳሩ ጠቧል›› ከሚለው አልፈው ‹‹ ተዘግቷል›› ወደሚል ድምዳሜ መሸጋገራቸውን በተጨባጭ ማስረጃ ሲያጋልጡ እና ሲያረጋግጡ ከርመዋል፡፡እዚህ ደረጃ ላይ መድረሳችሁንም በተለያየ ወቅት በጋዜጣዊ መግለጫቸው ለሕዝብ አሳውቀዋል፡፡ “የፖለቲካ ምህዳር” ምርጫንም የሚያካትት ነው፡፡

ደካማ የመንግስት አስተዳደር ለመለወጥ ምርጫ ያስፈልጋል፡፡ይሁን እንጂ ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ ማካሄድ አይቻልም፡፡ የገዢው የወያኔ መንግስት ጉዳይ ፈጻሚው በሆነው፣ በምርጫ ቦርድ በኩል በተለመደው መንገድ፣ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ምርጫ ቢካሄድ የወያኔ መንግስት አሸናፊ ሆኖ የሚወጣበት እድሉ የሰፋ ነው፡፡ እንዲህ መሆኑን የተረዱ እውነተኛ የተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫ ሥም ማጭበርበር ይበቃ !በማለት ትብብር መስርተው፣ ዘጠኝ ፓርቲዎች “ ነፃነት ለፍትሃዊ ምርጫ” የሕዝባዊ ትግል ፕሮግራም ይፋ አድርገዋል፡፡ ለነጻ፣ፍትሃዊ፣ ተኣማኒና አሳታፊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ፣ እንዲካሄድ በሠላማዊ ትግል አዎንታዊ ተጽዕኖ ለማሳረፍ ደፋ ቀና እያሉ ይገኛሉ፡፡

ሆኖም ግን በምርጫ ቦርድ እና በመንግሰት ላይ በሰላማዊ ትግል አዎንታዊ ግፊት ለማድረግ፣ በተጀመረው ህዝባዊ እንቅስቃሴ አጋር እና ደጋፊ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረ ፓርቲ “እኔ በምርጫ እሳተፋለው” በማለት የይወቁልኝ እና የይድረሱልኝ ጥሪ ሳይገደድ በፍቃደኝነት ከወዲኹ ማስተላለፉ ምን የሚሉት ነገር ነው፡፡ወይስ የሚባለው ነገር እውነት ይሆን እንዴ ?
ለማንኛውም ነገሩን ግልፅ ለማድረግ ያህል ፤አንድ ፓርቲ በሕጋዊ መንገድ ሲቋቋም ስልጣን ሊይዝ የሚችለው በመርጫ እንደሆነ ይታወቃል፣ ይህ ማለት በምርጫ መሳተፍ የአንድ ፓርቲ መደበኛ ተግባሩ ነው፡፡ መደበኛ ተግባርን ለማከናወን የተለየ መግለጫ አያስፈልግም፡፡ከዚህ ይልቅ በምርጫ አልሳተፍም ማለተ የተሸለ የተለየ መግለጫ ያስፈልገዋል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የተሰጠ ተግባር ከማከናወን ይልቅ አለማከናወን በቂ ምክንያት የሚያስፈልገው በመሆኑ፡፡ለማንኛውም ይሄ በወፍ በረር ስለ ጉዳዮ ለምግለፅ ያህል ነው፣ወደፊት በሰፊው እመለስበታለው፡፡ እስከዚያው ቸር ወሬ ያሰማን !

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !!!

Thursday 20 November 2014

ምርጫ ሲባል አማራጭ ሳያሳጡ መሆን ይኖርበታል!!!


ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

በሀገራችን ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ጊዜ ሀገራዊ ምርጫ እንደሚደረግ በመንግስት በኩል በከፍተኛ ደረጃ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል፡፡ ነገር ግን ከዚህ በፊት የተከናወኑት አራት ምርጫዎች ያየን እንደሆነ በሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ወደፊት ሊወስዱ እንዳልቻሉ እሙን ነው፡፡ ይህም ሆኖ የኢትዮጵያ ህዝብ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ፍላጎት በተለያየ መንገድ ሲገልፅ ቆይቷል፡፡ በተቃራኒው መንግስትና ገዢው ፓርቲ በፍፁም መለየት በሚያስቸግር ሁኔታ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ ሆነው ተቀናጅተው ለአንድ ለአውራ ፓርቲ ግንባታ እየሰሩ እንደሆነ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ይህ የመንግሥትና የገዢው ፓርቲ ተግባር ምርጫን ያለ አማራጭ እንዲሆነ እያደረገው እንደሆነ ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡

በቅርቡ የአንድነት ፓርቲ አባላት ላይ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ዘመቻ በሚባል ደረጃ እየተካሄደ ያለው አፈናና እስር፤ ከዚህም ባሻገር ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከህዝብ ጋር እንዳይገናኙ ክልከላውና ወከባው ተጠናከሮ መቀጠሉ፤ ገዥው ቡድን የምር ተቃዋሚ ፓርቲ ናቸው ብሎ የሚያስባቸው ፓርቲዎች ለማዳከምና ከምርጫው ውድድር ውጪ ለማድረግ ያለው ቁርጥ አቋም የሚያሳይ ነው። ይህ የገዢው ቡድን አካሄድ በሀገራችን ዴሞክራሲያዊ የሆነ የመድበለ ፓርቲ ስርዓት እንዲመሰረት ፍላጎት እንደሌለው በደንብ የሚያረጋግጥ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃና ፍትሐዊ በሆነ ምርጫ የሚፈልገውን ፓርቲ እንዲመርጥ እድል ሊጠሰው ሲገባ በሥርዓቱ በእኩል ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ እንዳያካሄድ የተለያዩ ጫናዎች እየተደረጉበት የሚካሄዱት ምርጫዎች ሁሉ ትርጉም አልባ እየሆኑ ይገኛሉ፡፡ ይህ የገዢው ቡድን ሀላፊነት የጎደለው እንቅስቃሴ በተግባር የሚደግፈው ከሠላማዊ ትግል ይልቅ የኃይልና የአመፅ መንገድ እንደሚሆን የተረዳ አይመስልም፤ ይልቁንም በሠላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ያሉትን ፓርቲዎች ወደ አላስፈላጊ መስመር በመግፋት ሀገራችን ወደ ብጥብጥና ወደ እርስ በእርስ ጦርነት እንድትገባ የሚያደርግ ሁኔታ እየተከተለ ነው የሚገኘው። በሥልጣን ላይ ያሉት ወገኖች ይህ አሳሳቢ ሁኔታ በትክክል እንዳያዩ ጭፍን የሥልጣን ጥም ጋርዷቸዋል፡፡
በቀጣይ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. የሚደረገው ምርጫም በመንግስት በኩል የመድበለ ፓርቲን ስርዓት ለማጎልበት ምንም ዓይነት ምቹ ሁኔታ እንዳይፈጠር ከአሁኑ የተለያዩ እንቅፋቶችን በመደርደር ላይ ነው። የአንድነት አመራሮችና አባላት በግፍ በማሰር ፓርቲው በምርጫው እንዳይሳተፍ ከፍተኛ የሆነ ጫና እየተደረገ ቢሆንም አንድነት ፓርቲ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ሆኖ ህዝቡ እንዲሳተፍ በመቀስቀስና በማበረታታት የተዘጋውን የዴሞክራሲ በር በምርጫ ካርዱ ሊያስከፍት እንደሚችል ከፍተኛ እምነት አለው፡፡

ከሁሉም በላይ ደግሞ እንደከዚህ ቀደሙ ኢህአዴግ ደጋፊዎቼ የሚላቸውን ብቻ በመራጭነት አስመዝግቦ ምርጫ የሚያደርግበት ሁኔታ ማብቃት ይኖርበታል ብለን እናምናለን፡፡ ይህ ተግባራዊ እንዲሆን በእኛ በኩል ደጋፊዎቻችን በመራጭነት እንዲመዘገቡ ከማበረታት ጀምሮ የህዝብና የፓርቲ ታዛቢ በመሆን የምርጫ ሂደቱን በሙሉ በንቃት እንዲከታተል እንዲሳተፍ የበኩላችንን ጥረት በማድረግ የ2007 ሀገራዊ ምርጫ ከጅማሮው ህዝባዊ እንዲሆን ትግላችንን እንቀጥላለን፡፡ ይህ እርምጃም ህዝቡን የስልጣን ባለቤት ለማድረግ ወሳኝ እርምጃ ነው የሚል እምነት አለን፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ በገዥው ቡድን መልካም ፍቃድ ወይም በማንኛውም ውጫዊ ተፅዕኖ የፖለቲካ ምህዳሩን እንደማይሰፋ ሊገነዘብ ይገባል። ምህዳሩ የሚሰፋውና ትክክለኛ የሆነ ዴሞክራሲያዊ ለውጥ የሚኖረው ህዝቡ በጠቅላላ ከፍርሀት ቆፈን ተላቆ በሙሉ ልብ ለመብቱ ሲቆም፣ ለፓርቲዎች ተገቢው ድጋፍ ሲሰጥ፤ ከፍ ሲልም ወደ ትግሉ ሲቀላቀል መሆኑ መገንዘብ ያስፈልጋል።
በዚህ አጋጣሚ አንድነት ፓርቲ ከህዳር 14 እስከ 20 ቀን 2007 ዓ.ም. የሚቆይ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለህሊና እስረኞች” የሚል የሶሻል ሚዲያ ዘመቻ አዘጋጅቷል። በዚህ ዘመቻ ለመንግስት ባለስልጣናት፣ ለታዋቂ ግለሰቦች፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተቋማትና ለልዩ ልዩ የሚዲያ ድርጅቶች በኢንተርኔትና በሶሻል ሚዲያ በእኩል መልዕክት በመላክ በሀገራችን ያሉት የፖለቲካ እስረኞች ሁኔታና አያያዝ በተመለከተ መረጃ በመስጠት ተገቢ የሆነ አያያዝ እንዲኖራቸው፤ ከእስር እንዲፈቱ፣ በሰላማዊ መንገድ የሚታሉትን ማሰርና ማዋከብ እንዲቆም በመንግስት ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ ለመፍጠር ያለመ ነው። በዚህ ዘመቻ ላይ ሚሊዮኖች ለሚያውቁትና ተፅዕኖ ማሳደር ይችላል ለሚሉት ሰው ሁሉ መልዕክት በኢተርኔትና በሶሻል ሚዲያ በመላክ ድምፃቸውን ያሰሙ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)
ህዳር 11 ቀን 2007 ዓ.ም.
አዲስ አበባ


Journey in the dark Oromo’s untold story in Eritrea

OLF_Messianic_Expectation


 The aim of this bulletin is not in any way to black mail any organization, but only to share my own ordeal and also send a message to my fellow Oromo youths. It is better to identify myself to all readers than to deeply tell my past back ground. Few years ago, I was a student at Jima University. While in university, I actively participated and contributed my share of expectation to the cause of Oromo students’ movement protesting against the plunder and brutality of the Habesha regime. Starting from high school education, recruited to an Oromo liberation front (OLF) underground cell, I spent my school time as an activist fulfilling my responsibility of a generation. When I was at university I didn’t completely went to study, but also shared my time for the cause of the Oromo peoples’ struggle. I just couldn’t isolate myself from any movement that stands for justice and equality of the Oromo people.

I was grown up in a family brutalized by their political attitude. Since I was young my father spent most of his life in prison framed as an OLF member. Mercilessly and cruelly tortured by the tyrant government regime, my father became disabled and mentally unstable to look after his children. It was our mother, who fends for our survival while looking after our father in prison and bearing the responsibility of the whole family on her shoulder. Having this kind of deep human inflicted scar in my mind, I developed the wish and the ambition to join the OLF, the organization I yearn to be a member one day since my childhood. This is what I believe in, live for and die for, for OLF is a stamp on my body and a stream running in my blood. Limiting words to tell about myself let me take you with me on a journey to the ordeal I was through as a young Oromo student activist. As I said, while at university I was spotted by the regimes spies and marked as dangerous daily followed wherever I move. Later the twist turned to a fiasco. Oromo student activists were unjustly arrested and detained by the authoritarian government of Tigray. I was lucky enough to evade an arrest.

However, life was not going to be the same again. Failing to visit my family, I spent some few weeks in Addis Ababa hiding from the piranhas totally disconnected from friends. I also lost connection with the OLF and that made me unstable. Life started boring in Addis. I have to make decision soon or later. The soon the better I thought. I made my decision and cut a line to fully join OLF. It wasn’t like an adventure but a life risking start, but I set on a journey to find OLF and wholly submit myself to the cause of the struggle.Long way from Addis Ababa to Eritrea I don’t have any clue since when was OLF residing in Eritrea but the Tigrayan regimes media puts it as it was since the end of 1990s.

Nevertheless, it is a known secret that OLF is based in Eritrea. As a person evading arrest, I passed so many challenges on my way to Eritrea. But before making the final attempt to cross to Eritrea, I spent some few months in Humera, on the side of Ethiopia as a daily laborer; not to earn a living but taking my time to know how it should be done and reach successfully the other side of the border.

Fortunately I found a government military escapee person from south Showa who is also working as a daily laborer for coverage but tacitly he was engaged in human trafficking across the border. Knowing him very well I let the cat out of the bag by telling him the secret I was holding. At first he was skeptical of my decision, but at last he let it go and guide me to my final destiny. It was Thursday night. My reference was the information I got from the escapee. Though difficult and risky I Friday morning I was on the side of the other border on Eritrean soil on the hands’ of Eritrean soldiers.

Uncertain about tomorrow, but I was certain that I am not in the brutal hands of the Ethiopian regime.
The night mare ordeals soon I was in Eritrea No sooner I surrender to the Eritrean defense forces, I told them what I was looking for. I want to join the OLF, I cried. They told me I should rest a moment and I will be granted my wish. Even though my yearnings of many years is now about to burst as though I didn’t spent many passing times for this opportunity, I couldn’t hold my excitement of this time for another few moment. But here things are different. It was not as smooth as I wished it should be. Two weeks had gone, and I was under scrutiny. What went wrong? Was I suspected as an agent? I don’t know. Two weeks later a logistic car came and I was on board to Afabet, a small town where soldiers surrendered to Eritrea, escaping from Ethiopia are kept. Interrogated again my wish was one and only one. Joining the OLF! Forget the OLF! I was told, you better stop thinking about OLF and I suggest you join the Tigray people’s democratic movement (TPDM), groaned Eritrean military personnel.

I felt a cold blood flows in my body. It all felt like a night mare. I stood my ground. I repeatedly told the man that I will only participate in Oromo political cause and join only the OLF. I knew my request failed on a deaf ear only when I was taken to a place called Harena, where I saw myself in a big military barrack. Only Tigrinya is spoken here. It is a TPDM military camp. Before they left I asked the Eritrean defense force members who brought me to the camp, why should I be brought here against my will? Yet I want to join the OLF. They told me from now on it is the TPDM I should deal with and my case doesn’t concern the government of Eritrea. What a malevolent act! Is the OLF not in Eritrea? Is the government of Eritrea not sheltering OLF in a safe haven as it was claimed? Or OLF and TPDM are one organization I didn’t know yet? Life with tpdm Two days after in their camp, a TPDM leader came and asked me few questions.

I answered his questions honestly and told him my intention. He told me I should stop fooling myself and better think about my future. The mood between us was as uncomfortable as I expected. He came back again two days later. His face was uninviting and my decision was irreversible. What have you decided? He roared. I knew things are going to be bitter, but I told him I will never be his front’s member as long as I am conscious. No deal was struck between us. Removing my shoes I was straightly taken to a prison. Home sweet home; I laughed burningly. Escaping a prison to a prison I murmured. I wasn’t alone at least. There were some 16 Oromo youths handed over to the TPDM by the Eritrean government. Most of them spent more than six months and they are in a bad shape. One of them from western Oromia region, Dembi Dollo, was inhumanely beaten and lost one eye completely. It doesn’t need one to look for evidence to know these youths were tortured, for a foul smell coming from their maimed wound tells it all. Three month has gone. Torture, interrogations, malicious damages and mental degradation was the fate one is destined to achieve in this prison. We were told leave alone thinking joining OLF dreaming about the name by itself is a crime. What is this all about? My daily stay with the Oromo prisoners has an answer. TPDM is trying to make an organization like people’s democratic organizations incepted by the former Tigray people’s liberation front (TPLF.) a daughter learns from her mother is the case here. The 16 I was detained with strongly opposed TPDM’s dream of turning them in to a tool.

But TPDM’s attempt was not in vain. They created an Oromo wing organization like the TPLF did by creating the Oromo people’s democratic organization (OPDO). Their members were those Oromo youths who were coordinated by force, failing to stand the brute’s daily torture. As days were passing I reached on one undeniable fact. TPDM has succeeded in creating a PDO and I couldn’t help about it. So my only way out is to accept their offer and see what fortune has for me in its store. Staying in prison in a dessert far away from home in country like Eritrea is not a wise decision we concluded with my fellow prisoners. We knew what we decided and it was the right decision. We told the TPDM person, our ‘hero’ who daily come to us for beating the ‘hell’ out of us. I observed the excitement on his face. Our gate is open to you gentlemen; he victoriously told us. They let us free at last! We were taken to a farm land to work as daily servants on TPDM owned vast land.

TPDM is not creating an Oromo organization wing only, but also other nations and nationalities are on the making. There was a weekend nations and nationalities entertainment day, by Amharic language. Everybody is supposed to speak Amharic and has to avoid speaking his native language. In this kind of situation one day when at work an Oromo former prisoner working with us hit on a head a Tigre soldier guarding us and escaped successfully. The guard died on spot. It was a miracle the escapee survived the dessert challenges and reached Sudan, I learned later. But his escape made life terrible for those of us who remained behind. We were threatened to be retaliation targets. Another incident had happened again. A young Oromo former Ethiopian soldier from western oromia region, Ilu Aba Bor zone escaped. His was not a success to tale. He was captured and shot dead by firing squad. Here what I want my readers to know is that TPDM has a big number of soldiers in Eritrean dessert from the age of 8 to 80 shackled together by force against their will. Students, farmers, teachers, husband and wife, all were abducted by force and serving TPDM by the mouth of gun. When an opportunity presents itself everybody tries his/her luck to escape, whatever cost it takes to pay. After we start training 22 trainees out of 108 escaped within a period of one month.

Their cruelty is not only for us who were not Tigrayans, but their own members from Tigray also share the same challenge. While on expedition their fighters dessert in mass and their causalities are very high. Now they even stopped fighting because number of casualties and deserters. Through passing time I proofed my loyalty to TPDM and set myself free from their surveillance. All this time I was preparing for my escape and it has to be first and last successful one I thought. One day I collapsed in front of the TPDM leader. I spent some few minutes as though I am unconscious, and when wake up I told the leader who was standing with confused face that I was ill from diarrhea and lost too much fluid. I was treated fairly and that night frequented toilet more than ten times. For there is no a latrine we used the bushes and that night I was sure no one was following me when I was going out and went deep to the bush. The second night was my luckiest night ever. I escaped with ease and saw myself the next morning at the hands of the Sudanese defense force. Without any harsh treatment I was taken to shagarab refugee camp in Sudan.Not all days are bad.

After three weeks at the refugee camp I made every contact I could and finally made my way to Khartoum, to try to find OLF contact. I have never dreamed to lead a refugee life and I left my education, my beloved family and my country biasing for the Oromo people’s struggle. Therefore, there is no reason for me to remain at refugee camp and seek an asylum and then repatriated to third country as many refuges do. Arriving in Khartoum and finding OLF contact It took me only few days. I accessed all my old contacts and it was worth trying. Finally I succeeded in contacting a friend graduate of Jima University who guide me to another friend released from Ma’ikelaw (known for its torching Oromo activists) prison. This freed prisoner is my former class mate at Jima University. It all doesn’t feel real. Yet it was all real. Through this friend I was contacted by an OLF member residing in Khartoum. Though it is not the code of conduct to identify this person his approach, treatment, understanding and caring is a personality I couldn’t pass without mentioning. With him I got a sanction, and I also told him all I was dreaming, my ordeals, and the malicious damage the government of Eritrea is inflicting on our youths in a remote Eritrean dessert. He wasn’t surprised at all when I told him about Eritrean governments act and TPDM’s attempt of creating PDOs supported by Shabiya.

You draw in water unknowing its enmity was all he has to say. When I asked what he means by his word he told me he even couldn’t understand what he said. I knew he was raged in anger and I withdraw my question. But he collected his thoughts and started telling me a long story that touched me deep to my bones. I was a member of Oromo liberation army (OLA), he said; I have been to Asmara so many times before I said enough. I was listening attentively and he continued. Many people think Eritrea is a safe haven for the OLF leaders living there. But the truth is, it is a living hell for them. Leave OLF he hissed, Eritrea is not a country to live in even for its own people. Leaders from Eritrean government hated our movement and they are assigned in splitting us daily, making our struggle crawls on its knees. I was sad and at the same time felt retaliation surging in my body. Kamal Galchu (leader of OLF faction splinted from OLF in 2008) was hand made by this kind of leaders he said. Our leaders are doing all they could to save this struggle from collapse and I am also in this struggle at this old age he told me tears rolling in his face. I was feeling something. Something cannot be put in to words. Hell to Shabiya I shouted! What is the difference between them, they are all working against us for the dominance of habeshan hegemony. TPLF and EPLF are both sides of one coin. There is nothing for me in Sudan I thought though. From Khartoum I set to Nairobi via South Sudan and Uganda. The journey was hazardous and I don’t see it useful to mention, but I managed to reach Nairobi after three months. I could have said a lot about what I saw and experienced in Eritrea, but I reserved it for history and also feared for the safety of Oromo children still trapped in that malicious country. For me life will never be the same. Now I have the right contact with OLF and I will be looking forward. As I said I will never be a refugee in my life, Nairobi is also not going to be my final destiny. I have my own destiny and it is my hand, I know where I have to go and it is the right direction to take.

Before ending my story I will say to the government of Shabiya, take off your hands from Oromo struggle, stop harassing our children, stop handing over Oromo youths to TPDM and if you don’t want OLF existence in your country; tell the leaders to leave. For Oromo leaders who are struggling and keeping the flame burning in this kind of testing situation, my appreciation is sincere and I want to say may God reward you the fruit of your sweat.I will reiterate once again. Shabiya please take off your hands from our struggle. History will judge us!For Oromo youths wishing to join OLF, the road to Eritrea is not the road to liberty, don’t make the mistake I made. OLA is in Oromia and look for it just around you. This is my story and I know there are so many untold histories. But one day someone will live tell these untold stories. Pray for all those who are still languishing in Eritrean dessert.

Thank you for your precious time.Oromia shall be free!!
God bless Oromia!!
T.F/ AdamuNairobi Kenya
Source: SiiTube Ethiopian News Oromo News
Source:: satenaw
The aim of this bulletin is not in any way to black mail any organization, but only to share my own ordeal and also send a message to my fellow Oromo youths. It is better to identify myself to all readers than to deeply tell my past back ground. Few years ago, I was a student at Jima University. While in university, I actively participated and contributed my share of expectation to the cause of Oromo students’ movement protesting against the plunder and brutality of the Habesha regime. Starting from high school education, recruited to an Oromo liberation front (OLF) underground cell, I spent my school time as an activist fulfilling my responsibility of a generation. When I was at university I didn’t completely went to study, but also shared my time for the cause of the Oromo peoples’ struggle. I just couldn’t isolate myself from any movement that stands for justice and equality of the Oromo people.
I was grown up in a family brutalized by their political attitude. Since I was young my father spent most of his life in prison framed as an OLF member. Mercilessly and cruelly tortured by the tyrant government regime, my father became disabled and mentally unstable to look after his children. It was our mother, who fends for our survival while looking after our father in prison and bearing the responsibility of the whole family on her shoulder. Having this kind of deep human inflicted scar in my mind, I developed the wish and the ambition to join the OLF, the organization I yearn to be a member one day since my childhood. This is what I believe in, live for and die for, for OLF is a stamp on my body and a stream running in my blood. Limiting words to tell about myself let me take you with me on a journey to the ordeal I was through as a young Oromo student activist. As I said, while at university I was spotted by the regimes spies and marked as dangerous daily followed wherever I move. Later the twist turned to a fiasco. Oromo student activists were unjustly arrested and detained by the authoritarian government of Tigray. I was lucky enough to evade an arrest.
However, life was not going to be the same again. Failing to visit my family, I spent some few weeks in Addis Ababa hiding from the piranhas totally disconnected from friends. I also lost connection with the OLF and that made me unstable. Life started boring in Addis. I have to make decision soon or later. The soon the better I thought. I made my decision and cut a line to fully join OLF. It wasn’t like an adventure but a life risking start, but I set on a journey to find OLF and wholly submit myself to the cause of the struggle.Long way from Addis Ababa to Eritrea I don’t have any clue since when was OLF residing in Eritrea but the Tigrayan regimes media puts it as it was since the end of 1990s. Nevertheless, it is a known secret that OLF is based in Eritrea. As a person evading arrest, I passed so many challenges on my way to Eritrea. But before making the final attempt to cross to Eritrea, I spent some few months in Humera, on the side of Ethiopia as a daily laborer; not to earn a living but taking my time to know how it should be done and reach successfully the other side of the border. Fortunately I found a government military escapee person from south Showa who is also working as a daily laborer for coverage but tacitly he was engaged in human trafficking across the border. Knowing him very well I let the cat out of the bag by telling him the secret I was holding. At first he was skeptical of my decision, but at last he let it go and guide me to my final destiny. It was Thursday night. My reference was the information I got from the escapee. Though difficult and risky I Friday morning I was on the side of the other border on Eritrean soil on the hands’ of Eritrean soldiers. Uncertain about tomorrow, but I was certain that I am not in the brutal hands of the Ethiopian regime.
The night mare ordeals soon I was in Eritrea No sooner I surrender to the Eritrean defense forces, I told them what I was looking for. I want to join the OLF, I cried. They told me I should rest a moment and I will be granted my wish. Even though my yearnings of many years is now about to burst as though I didn’t spent many passing times for this opportunity, I couldn’t hold my excitement of this time for another few moment. But here things are different. It was not as smooth as I wished it should be. Two weeks had gone, and I was under scrutiny. What went wrong? Was I suspected as an agent? I don’t know. Two weeks later a logistic car came and I was on board to Afabet, a small town where soldiers surrendered to Eritrea, escaping from Ethiopia are kept. Interrogated again my wish was one and only one. Joining the OLF! Forget the OLF! I was told, you better stop thinking about OLF and I suggest you join the Tigray people’s democratic movement (TPDM), groaned Eritrean military personnel. I felt a cold blood flows in my body. It all felt like a night mare. I stood my ground. I repeatedly told the man that I will only participate in Oromo political cause and join only the OLF. I knew my request failed on a deaf ear only when I was taken to a place called Harena, where I saw myself in a big military barrack. Only Tigrinya is spoken here. It is a TPDM military camp. Before they left I asked the Eritrean defense force members who brought me to the camp, why should I be brought here against my will? Yet I want to join the OLF. They told me from now on it is the TPDM I should deal with and my case doesn’t concern the government of Eritrea. What a malevolent act! Is the OLF not in Eritrea? Is the government of Eritrea not sheltering OLF in a safe haven as it was claimed?
Or OLF and TPDM are one organization I didn’t know yet? Life with tpdm Two days after in their camp, a TPDM leader came and asked me few questions. I answered his questions honestly and told him my intention. He told me I should stop fooling myself and better think about my future. The mood between us was as uncomfortable us I expected. He came back again two days later. His face was uninviting and my decision was irreversible. What have you decided? He roared. I knew things are going to be bitter, but I told him I will never be his front’s member as long as I am conscious. No deal was struck between us. Removing my shoes I was straightly taken to a prison. Home sweet home; I laughed burningly. Escaping a prison to a prison I murmured. I wasn’t alone at least. There were some 16 Oromo youths handed over to the TPDM by the Eritrean government. Most of them spent more than six months and they are in a bad shape. One of them from western Oromia region, Dembi Dollo, was inhumanely beaten and lost one eye completely. It doesn’t need one to look for evidence to know these youths were tortured, for a foul smell coming from their maimed wound tells it all. Three month has gone. Torture, interrogations, malicious damages and mental degradation was the fate one is destined to achieve in this prison. We were told leave alone thinking joining OLF dreaming about the name by itself is a crime. What is this all about? My daily stay with the Oromo prisoners has an answer. TPDM is trying to make an organization like people’s democratic organizations incepted by the former Tigray people’s liberation front (TPLF.) a daughter learns from her mother is the case here. The 16 I was detained with strongly opposed TPDM’s dream of turning them in to a tool.
But TPDM’s attempt was not in vain. They created an Oromo wing organization like the TPLF did by creating the Oromo people’s democratic organization (OPDO). Their members were those Oromo youths who were coordinated by force, failing to stand the brute’s daily torture. As days were passing I reached on one undeniable fact. TPDM has succeeded in creating a PDO and I couldn’t help about it. So my only way out is to accept their offer and see what fortune has for me in its store. Staying in prison in a dessert far away from home in country like Eritrea is not a wise decision we concluded with my fellow prisoners. We knew what we decided and it was the right decision. We told the TPDM person, our ‘hero’ who daily come to us for beating the ‘hell’ out of us. I observed the excitement on his face. Our gate is open to you gentlemen; he victoriously told us. They let us free at last! We were taken to a farm land to work as daily servants on TPDM owned vast land. TPDM is not creating an Oromo organization wing only, but also other nations and nationalities are on the making. There was a weekend nations and nationalities entertainment day, by Amharic language. Everybody is supposed to speak Amharic and has to avoid speaking his native language. In this kind of situation one day when at work an Oromo former prisoner working with us hit on a head a Tigre soldier guarding us and escaped successfully. The guard died on spot. It was a miracle the escapee survived the dessert challengesand reached Sudan, I learned later. But his escape made life terrible for those of us who remained behind. We were threatened to be retaliation targets. Another incident had happened again. A young Oromo former Ethiopian soldier from western oromia region, Ilu Aba Bor zone escaped. His was not a success to tale. He was captured and shot dead by firing squad. Here what I want my readers to know is that TPDM has a big number of soldiers in Eritrean dessert from the age of 8 to 80 shackled together by force against their will. Students, farmers, teachers, husband and wife, all were abducted by force and serving TPDM by the mouth of gun. When an opportunity presents itself everybody tries his/her luck to escape, whatever cost it takes to pay. After we start training 22 trainees out of 108 escaped within a period of one month.
Their cruelty is not only for us who were not Tigrayans, but their own members from Tigray also share the same challenge. While on expedition their fighters dessert in mass and their causalities are very high. Now they even stopped fighting because number of casualties and deserters. Through passing time I proofed my loyalty to TPDM and set myself free from their surveillance. All this time I was preparing for my escape and it has to be first and last successful one I thought. One day I collapsed in front of the TPDM leader. I spent some few minutes as though I am unconscious, and when wake up I told the leader who was standing with confused face that I was ill from diarrhea and lost too much fluid. I was treated fairly and that night frequented toilet more than ten times. For there is no a latrine we used the bushes and that night I was sure no one was following me when I was going out and went deep to the bush. The second night was my luckiest night ever. I escaped with ease and saw myself the next morning at the hands of the Sudanese defense force. Without any harsh treatment I was taken to shagarab refugee camp in Sudan.Not all days are bad. After three weeks at the refugee camp I made every contact I could and finally made my way to Khartoum, to try to find OLF contact. I have never dreamed to lead a refugee life and I left my education, my beloved family and my country biasing for the Oromo people’s struggle. Therefore, there is no reason for me to remain at refugee camp and seek an asylum and then repatriated to third country as many refuges do. Arriving in Khartoum and finding OLF contact It took me only few days. I accessed all my old contacts and it was worth trying. Finally I succeeded in contacting a friend graduate of Jima University who guide me to another friend released from Ma’ikelaw (known for its torching Oromo activists) prison. This freed prisoner is my former class mate at Jima University. It all doesn’t feel real. Yet it was all real. Through this friend I was contacted by an OLF member residing in Khartoum. Though it is not the code of conduct to identify this person his approach, treatment, understanding and caring is a personality I couldn’t pass without mentioning. With him I got a sanction, and I also told him all I was dreaming, my ordeals, and the malicious damage the government of Eritrea is inflicting on our youths in a remote Eritrean dessert. He wasn’t surprised at all when I told him about Eritrean governments act and TPDM’s attempt of creating PDOs supported by Shabiya.
You draw in water unknowing its enmity was all he has to say. When I asked what he means by his word he told me he even couldn’t understand what he said. I knew he was raged in anger and I withdraw my question. But he collected his thoughts and started telling me a long story that touched me deep to my bones. I was a member of Oromo liberation army (OLA), he said; I have been to Asmara so many times before I said enough. I was listening attentively and he continued. Many people think Eritrea is a safe haven for the OLF leaders living there. But the truth is, it is a living hell for them. Leave OLF he hissed, Eritrea is not a country to live in even for its own people. Leaders from Eritrean government hated our movement and they are assigned in splitting us daily, making our struggle crawls on its knees. I was sad and at the same time felt retaliation surging in my body. Kamal Galchu (leader of OLF faction splinted from OLF in 2008) was hand made by this kind of leaders he said. Our leaders are doing all they could to save this struggle from collapse and I am also in this struggle at this old age he told me tears rolling in his face. I was feeling something. Something cannot be put in to words. Hell to Shabiya I shouted! What is the difference between them, they are all working against us for the dominance of habeshan hegemony. TPLF and EPLF are both sides of one coin. There is nothing for me in Sudan I thought though. From Khartoum I set to Nairobi via South Sudan and Uganda. The journey was hazardous and I don’t see it useful to mention, but I managed to reach Nairobi after three months. I could have said a lot about what I saw and experienced in Eritrea, but I reserved it for history and also feared for the safety of Oromo children still trapped in that malicious country. For me life will never be the same. Now I have the right contact with OLF and I will be looking forward. As I said I will never be a refugee in my life, Nairobi is also not going to be my final destiny. I have my own destiny and it is my hand, I know where I have to go and it is the right direction to take.
Before ending my story I will say to the government of Shabiya, take off your hands from Oromo struggle, stop harassing our children, stop handing over Oromo youths to TPDM and if you don’t want OLF existence in your country; tell the leaders to leave. For Oromo leaders who are struggling and keeping the flame burning in this kind of testing situation, my appreciation is sincere and I want to say may God reward you the fruit of your sweat.I will reiterate once again. Shabiya please take off your hands from our struggle. History will judge us!For Oromo youths wishing to join OLF, the road to Eritrea is not the road to liberty, don’t make the mistake I made. OLA is in Ormia and look for it just around you. This is my story and I know there are so many untold histories. But one day someone will live tell these untold stories. Pray for all those who are still languishing in Eritrean dessert.
Thank you for your precious time.Oromia shall be free!!
God bless Oromia!!
T.F/ AdamuNairobi Kenya
Source: SiiTube Ethiopian News Oromo News
- See more at: http://satenaw.com/journey-in-the-dark-oromos-untold-story-in-eritrea/#sthash.P1cyTm4P.dpuf


  • 59
    Share
OLF_Messianic_ExpectationThe aim of this bulletin is not in any way to black mail any organization, but only to share my own ordeal and also send a message to my fellow Oromo youths. It is better to identify myself to all readers than to deeply tell my past back ground. Few years ago, I was a student at Jima University. While in university, I actively participated and contributed my share of expectation to the cause of Oromo students’ movement protesting against the plunder and brutality of the Habesha regime. Starting from high school education, recruited to an Oromo liberation front (OLF) underground cell, I spent my school time as an activist fulfilling my responsibility of a generation. When I was at university I didn’t completely went to study, but also shared my time for the cause of the Oromo peoples’ struggle. I just couldn’t isolate myself from any movement that stands for justice and equality of the Oromo people.
I was grown up in a family brutalized by their political attitude. Since I was young my father spent most of his life in prison framed as an OLF member. Mercilessly and cruelly tortured by the tyrant government regime, my father became disabled and mentally unstable to look after his children. It was our mother, who fends for our survival while looking after our father in prison and bearing the responsibility of the whole family on her shoulder. Having this kind of deep human inflicted scar in my mind, I developed the wish and the ambition to join the OLF, the organization I yearn to be a member one day since my childhood. This is what I believe in, live for and die for, for OLF is a stamp on my body and a stream running in my blood. Limiting words to tell about myself let me take you with me on a journey to the ordeal I was through as a young Oromo student activist. As I said, while at university I was spotted by the regimes spies and marked as dangerous daily followed wherever I move. Later the twist turned to a fiasco. Oromo student activists were unjustly arrested and detained by the authoritarian government of Tigray. I was lucky enough to evade an arrest.
However, life was not going to be the same again. Failing to visit my family, I spent some few weeks in Addis Ababa hiding from the piranhas totally disconnected from friends. I also lost connection with the OLF and that made me unstable. Life started boring in Addis. I have to make decision soon or later. The soon the better I thought. I made my decision and cut a line to fully join OLF. It wasn’t like an adventure but a life risking start, but I set on a journey to find OLF and wholly submit myself to the cause of the struggle.Long way from Addis Ababa to Eritrea I don’t have any clue since when was OLF residing in Eritrea but the Tigrayan regimes media puts it as it was since the end of 1990s. Nevertheless, it is a known secret that OLF is based in Eritrea. As a person evading arrest, I passed so many challenges on my way to Eritrea. But before making the final attempt to cross to Eritrea, I spent some few months in Humera, on the side of Ethiopia as a daily laborer; not to earn a living but taking my time to know how it should be done and reach successfully the other side of the border. Fortunately I found a government military escapee person from south Showa who is also working as a daily laborer for coverage but tacitly he was engaged in human trafficking across the border. Knowing him very well I let the cat out of the bag by telling him the secret I was holding. At first he was skeptical of my decision, but at last he let it go and guide me to my final destiny. It was Thursday night. My reference was the information I got from the escapee. Though difficult and risky I Friday morning I was on the side of the other border on Eritrean soil on the hands’ of Eritrean soldiers. Uncertain about tomorrow, but I was certain that I am not in the brutal hands of the Ethiopian regime.
The night mare ordeals soon I was in Eritrea No sooner I surrender to the Eritrean defense forces, I told them what I was looking for. I want to join the OLF, I cried. They told me I should rest a moment and I will be granted my wish. Even though my yearnings of many years is now about to burst as though I didn’t spent many passing times for this opportunity, I couldn’t hold my excitement of this time for another few moment. But here things are different. It was not as smooth as I wished it should be. Two weeks had gone, and I was under scrutiny. What went wrong? Was I suspected as an agent? I don’t know. Two weeks later a logistic car came and I was on board to Afabet, a small town where soldiers surrendered to Eritrea, escaping from Ethiopia are kept. Interrogated again my wish was one and only one. Joining the OLF! Forget the OLF! I was told, you better stop thinking about OLF and I suggest you join the Tigray people’s democratic movement (TPDM), groaned Eritrean military personnel. I felt a cold blood flows in my body. It all felt like a night mare. I stood my ground. I repeatedly told the man that I will only participate in Oromo political cause and join only the OLF. I knew my request failed on a deaf ear only when I was taken to a place called Harena, where I saw myself in a big military barrack. Only Tigrinya is spoken here. It is a TPDM military camp. Before they left I asked the Eritrean defense force members who brought me to the camp, why should I be brought here against my will? Yet I want to join the OLF. They told me from now on it is the TPDM I should deal with and my case doesn’t concern the government of Eritrea. What a malevolent act! Is the OLF not in Eritrea? Is the government of Eritrea not sheltering OLF in a safe haven as it was claimed?
Or OLF and TPDM are one organization I didn’t know yet? Life with tpdm Two days after in their camp, a TPDM leader came and asked me few questions. I answered his questions honestly and told him my intention. He told me I should stop fooling myself and better think about my future. The mood between us was as uncomfortable us I expected. He came back again two days later. His face was uninviting and my decision was irreversible. What have you decided? He roared. I knew things are going to be bitter, but I told him I will never be his front’s member as long as I am conscious. No deal was struck between us. Removing my shoes I was straightly taken to a prison. Home sweet home; I laughed burningly. Escaping a prison to a prison I murmured. I wasn’t alone at least. There were some 16 Oromo youths handed over to the TPDM by the Eritrean government. Most of them spent more than six months and they are in a bad shape. One of them from western Oromia region, Dembi Dollo, was inhumanely beaten and lost one eye completely. It doesn’t need one to look for evidence to know these youths were tortured, for a foul smell coming from their maimed wound tells it all. Three month has gone. Torture, interrogations, malicious damages and mental degradation was the fate one is destined to achieve in this prison. We were told leave alone thinking joining OLF dreaming about the name by itself is a crime. What is this all about? My daily stay with the Oromo prisoners has an answer. TPDM is trying to make an organization like people’s democratic organizations incepted by the former Tigray people’s liberation front (TPLF.) a daughter learns from her mother is the case here. The 16 I was detained with strongly opposed TPDM’s dream of turning them in to a tool.
But TPDM’s attempt was not in vain. They created an Oromo wing organization like the TPLF did by creating the Oromo people’s democratic organization (OPDO). Their members were those Oromo youths who were coordinated by force, failing to stand the brute’s daily torture. As days were passing I reached on one undeniable fact. TPDM has succeeded in creating a PDO and I couldn’t help about it. So my only way out is to accept their offer and see what fortune has for me in its store. Staying in prison in a dessert far away from home in country like Eritrea is not a wise decision we concluded with my fellow prisoners. We knew what we decided and it was the right decision. We told the TPDM person, our ‘hero’ who daily come to us for beating the ‘hell’ out of us. I observed the excitement on his face. Our gate is open to you gentlemen; he victoriously told us. They let us free at last! We were taken to a farm land to work as daily servants on TPDM owned vast land. TPDM is not creating an Oromo organization wing only, but also other nations and nationalities are on the making. There was a weekend nations and nationalities entertainment day, by Amharic language. Everybody is supposed to speak Amharic and has to avoid speaking his native language. In this kind of situation one day when at work an Oromo former prisoner working with us hit on a head a Tigre soldier guarding us and escaped successfully. The guard died on spot. It was a miracle the escapee survived the dessert challengesand reached Sudan, I learned later. But his escape made life terrible for those of us who remained behind. We were threatened to be retaliation targets. Another incident had happened again. A young Oromo former Ethiopian soldier from western oromia region, Ilu Aba Bor zone escaped. His was not a success to tale. He was captured and shot dead by firing squad. Here what I want my readers to know is that TPDM has a big number of soldiers in Eritrean dessert from the age of 8 to 80 shackled together by force against their will. Students, farmers, teachers, husband and wife, all were abducted by force and serving TPDM by the mouth of gun. When an opportunity presents itself everybody tries his/her luck to escape, whatever cost it takes to pay. After we start training 22 trainees out of 108 escaped within a period of one month.
Their cruelty is not only for us who were not Tigrayans, but their own members from Tigray also share the same challenge. While on expedition their fighters dessert in mass and their causalities are very high. Now they even stopped fighting because number of casualties and deserters. Through passing time I proofed my loyalty to TPDM and set myself free from their surveillance. All this time I was preparing for my escape and it has to be first and last successful one I thought. One day I collapsed in front of the TPDM leader. I spent some few minutes as though I am unconscious, and when wake up I told the leader who was standing with confused face that I was ill from diarrhea and lost too much fluid. I was treated fairly and that night frequented toilet more than ten times. For there is no a latrine we used the bushes and that night I was sure no one was following me when I was going out and went deep to the bush. The second night was my luckiest night ever. I escaped with ease and saw myself the next morning at the hands of the Sudanese defense force. Without any harsh treatment I was taken to shagarab refugee camp in Sudan.Not all days are bad. After three weeks at the refugee camp I made every contact I could and finally made my way to Khartoum, to try to find OLF contact. I have never dreamed to lead a refugee life and I left my education, my beloved family and my country biasing for the Oromo people’s struggle. Therefore, there is no reason for me to remain at refugee camp and seek an asylum and then repatriated to third country as many refuges do. Arriving in Khartoum and finding OLF contact It took me only few days. I accessed all my old contacts and it was worth trying. Finally I succeeded in contacting a friend graduate of Jima University who guide me to another friend released from Ma’ikelaw (known for its torching Oromo activists) prison. This freed prisoner is my former class mate at Jima University. It all doesn’t feel real. Yet it was all real. Through this friend I was contacted by an OLF member residing in Khartoum. Though it is not the code of conduct to identify this person his approach, treatment, understanding and caring is a personality I couldn’t pass without mentioning. With him I got a sanction, and I also told him all I was dreaming, my ordeals, and the malicious damage the government of Eritrea is inflicting on our youths in a remote Eritrean dessert. He wasn’t surprised at all when I told him about Eritrean governments act and TPDM’s attempt of creating PDOs supported by Shabiya.
You draw in water unknowing its enmity was all he has to say. When I asked what he means by his word he told me he even couldn’t understand what he said. I knew he was raged in anger and I withdraw my question. But he collected his thoughts and started telling me a long story that touched me deep to my bones. I was a member of Oromo liberation army (OLA), he said; I have been to Asmara so many times before I said enough. I was listening attentively and he continued. Many people think Eritrea is a safe haven for the OLF leaders living there. But the truth is, it is a living hell for them. Leave OLF he hissed, Eritrea is not a country to live in even for its own people. Leaders from Eritrean government hated our movement and they are assigned in splitting us daily, making our struggle crawls on its knees. I was sad and at the same time felt retaliation surging in my body. Kamal Galchu (leader of OLF faction splinted from OLF in 2008) was hand made by this kind of leaders he said. Our leaders are doing all they could to save this struggle from collapse and I am also in this struggle at this old age he told me tears rolling in his face. I was feeling something. Something cannot be put in to words. Hell to Shabiya I shouted! What is the difference between them, they are all working against us for the dominance of habeshan hegemony. TPLF and EPLF are both sides of one coin. There is nothing for me in Sudan I thought though. From Khartoum I set to Nairobi via South Sudan and Uganda. The journey was hazardous and I don’t see it useful to mention, but I managed to reach Nairobi after three months. I could have said a lot about what I saw and experienced in Eritrea, but I reserved it for history and also feared for the safety of Oromo children still trapped in that malicious country. For me life will never be the same. Now I have the right contact with OLF and I will be looking forward. As I said I will never be a refugee in my life, Nairobi is also not going to be my final destiny. I have my own destiny and it is my hand, I know where I have to go and it is the right direction to take.
Before ending my story I will say to the government of Shabiya, take off your hands from Oromo struggle, stop harassing our children, stop handing over Oromo youths to TPDM and if you don’t want OLF existence in your country; tell the leaders to leave. For Oromo leaders who are struggling and keeping the flame burning in this kind of testing situation, my appreciation is sincere and I want to say may God reward you the fruit of your sweat.I will reiterate once again. Shabiya please take off your hands from our struggle. History will judge us!For Oromo youths wishing to join OLF, the road to Eritrea is not the road to liberty, don’t make the mistake I made. OLA is in Ormia and look for it just around you. This is my story and I know there are so many untold histories. But one day someone will live tell these untold stories. Pray for all those who are still languishing in Eritrean dessert.
Thank you for your precious time.Oromia shall be free!!
God bless Oromia!!
T.F/ AdamuNairobi Kenya
Source: SiiTube Ethiopian News Oromo News
- See more at: http://satenaw.com/journey-in-the-dark-oromos-untold-story-in-eritrea/#sthash.P1cyTm4P.dpuf