Saturday, 29 November 2014

የእስክንድር ነጋ ያገባኛል ባይነት!

በላይ ማናዬ   ‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል!›› ይህን ያለው ትንታጉ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ እስክንድር ነጋ ነው፡፡ እስክንድር ነጋን ካወኩት ወዲህ እንደዛሬ በኃይለ ቃል ሲናገር ሰምቼው አላውቅም፤ ወይም ትዝ አይለኝም፡፡ ዛሬ (ህዳር 19/2007 ዓ.ም) እኩለ ቀን ላይ እስክንድርን ልጠይቀው ቃሊቲ ተገኝቼ ነበር፡፡ ሆኖም ሁኔታው ሁሉ እንደማንኛውም ቀን አልነበረም፡፡ በር ላይ ስደርስ በርከት ያሉ የአንድነት ፓርቲ...

Thursday, 27 November 2014

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ የወጣቶች ክፍል አዘጋጅነት ታላቅ ሰላማዊሰልፍ በኖርዌይ ኦስሎ ተካሄደ!!!

  የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ የወጣቶች ክፍል አዘጋጅነት በዛሬው እለት ሀሙስ (November 27,2014) በኖርዌ ኦስሎ በእንግሊዝ ኢንባሲ ፊት በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከሩቅም ከቅርብም በአንድነት በመሰባሰብ ከቀኑ 13፡30 እስከ 15፡00 ስዓት ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ አካሄዱ። የሰልፉ ዋና አላማ የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሃፊና የሰባዊ መብት ተቆርቋሪ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በአንምባ ገነኑ የወያኔ ቡድን በህገ ወጥ መንገድ ታፍነውና ፍትህ ተነፍገው በእስር ቤት መታሰራቸውን ለመቃወም ሲሆን በሰልፉ ስፍራ የተገኙ ሰዎች ሁሉ አቶ አንዳርጋቸው ለዲሞክራሲ እና ሰብአዊ መብት መከበር ከወጣትነት ጀምሮ የታገለ ታላቅ...

Wednesday, 26 November 2014

Ethiopia is one of the ‘world’s least connected country’

Denmark has been named the world’s “most connected” country based on mobile phone and internet use. Scandinavia dominated this year’s rankings, with Sweden in third place, followed by Iceland in fourth, Norway sixth and Finland eighth. Britain came fifth. They were compiled as part of a report by the International Telecommunication Union – the Information and Communication Technology Development Index (IDI), which rates 166 countries according...

አንድነትና መድረክ ተለያዩ

ላለፉት ስድስት ዓመታት ገደማ ያህል በጋራ ለመሥራት ተስማምተው የተቃውሞ ጐራው ላይ በጋራ ሲሠሩ የነበሩት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) እና አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የነበራቸውን አብሮ የመሥራት ስምምነት አቋርጠው ተለያዩ፡፡ ሁለቱ ፓርቲዎች የቀድሞው የአንድነት ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው ሰጥተውታል በተባለው አስተያየት የተነሳ እሰጥ አገባ ውስጥ መግባታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ አስተያየቱን አንድነት ያስተባብል በሚል ከመድረክ የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ለፓርቲዎቹ መለያየት ከፍተኛውን ድርሻ መውሰዱን የሁለቱ ፓርቲዎች ባለድርሻ አካላት መግለጻቸውን መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡ ከሁለት ሳምንታት በፊት ዳግም የመድረክ...

ርዮት አረንጓዴ፣ ቢጫ ቀይ ሰንድቅ አላማ በላይዋ ላይ ለብሳ በክብር ከቃሊቲ ትወጣለች – ግርማ ካሳ

በሃይ ስኩል የእንግሊዘኛ አስተማሪ ነበረች። በሕገ መንግስቱ ላይ የተደነገገዉን መብት በመጠቀም፣ በተለያዩ አገር ውስጥ በሚታተሙ ሜዲያዎች ትጽፋለች። «እነርሱ እንዲጻፍ ከሚፈልጉት ዉጭ እንዲጻፍ የማይፈልጉ ባለስልጣናት፣ የሃሰት ክስ መሰርተዉ፣ ዳኛ ለተብዬዎች መመሪያ ሰጠዉ፣ መሰረተ ልማቶችን ለማፍረስ አሴራለች፣ ሽብርተኛ ናት» ብለዉ ፈረዱባት። ይች እህት ርዮት አለሙ ትባላለች። ጡቷ አካባቢ ችግር ስላለበት ክትትል እንደሚያሰልጋት እየታወቅም ክትትል እንድታገኝ አልተደረገም። ወደ ሶስት አመት ገደማ ባላጠፋችዉ ጥፋት፣ ኢሕአዴግን ስለተቃወመች ብቻ፣ እየማቀቀች ነዉ። የርዮት ወንጀል አገሯ፣ ሕዝቧን መዉደዷ ነዉ። ርዮት አለሙ፣ ከጋዜጣኛ ነብዩ ሃይሉ ጋር በአዲስ ፕሬስ፣ ከጋዜጣኛ ስለሺ ሃጎስ ጋር...

Monday, 24 November 2014

ለስብሰባ ሲቀሰቅሱ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ተጨማሪ 7 ቀናት ተቀጠረባቸው

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ጠርቶት ለነበረው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ አርብ ህዳር 5/2007 ዓ.ም በቅስቀሳ ላይ እንደነበሩ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ 7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባቸው፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ም/ሰብሳቢና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ማቲያስ መኩሪያ እና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ሳምሶን ግዛቸው በቅስቀሳ ወቅት ተይዘው አራዳ ፖሊስ መምሪያ የታሰሩ ሲሆን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ችሎት ቀርበው የ7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ወጣቶቹ ‹‹ሽብር በማነሳሳት›› የሚል ‹ክስ› የተመሰረተባቸው ሲሆን ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ ሌሊት ደህንነቶች በተደጋጋሚ በኃይልና በዛቻ እንደሚመረምሯቸው...

Saturday, 22 November 2014

30 ደቂቃዎችን በዝዋይ እስር ቤት (ግዞት) ‹‹በብርቱ ታምሜያለሁ›› አበበ ቀስቶ

  ዝዋይ የሚገኙ የፖለቲካና የህሊና እስረኞችን በቦታው ተገኝቼ ለመጠየቅ እቅድ ከያዝኩ ረዘም ያሉ ቀናት አልፈዋል፡፡ እንዲያውም ጉዞው ከወዳጆቼ ጋር ሰብሰብ ብለን ቢሆን እንደሚመረጥ ተነጋግረንበት ነበር፡፡ ሆኖም ግን የዕለት ከዕለት ሩጫችን አላወላዳ ብሎን ባቀድነው ጊዜ ወደ ዝዋይ መጓዝ ሳንችል ቆይተናል፡፡ አርብ ህዳር 12/2007 ዓ.ም ግን እንዳሰብነው ሰብሰብ ብለንም ባይሆን በመጨረሻ አብሮኝ ከተጓዘው የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ባልደረባ ወጣት ፍቅረማርያም አስማማው ጋር ከአዲስ አበባ በጠዋት ተነስተን ወደ ዝዋይ አምርተን ለ30 ደቂቃዎች ያህል የናፈቅናቸውንና የናፈቁንን እስረኞች ልንጎበኝ በቅተናል፡፡ ዝዋይ ለመድረስ ከ2 ሰዓት በላይ ጉዞ ማድረግ ነበረብን፤ በጠዋት...

ፕሮፌሰር በየነ ጼጥሮስ ዲያስፖራውን ወቀሱ

ከአንድ ዓመት ላላነሰ ጊዜ በአሜሪካን ሀገር በቺካጎ ከተማ በሚገኝ አንድ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሲያስተምሩ ቆይተው በቅርቡ ወደሀገር ቤት መመለሳቸውን የተናገሩት የወቅቱ የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ዲያስፖራውን ወቅሰዋል። ፕሮፌሰሩ በዛሬው ዕለት ለንባብ ከበቃው መንግስታዊው ዘመን መጽሄት የጥቅምት 2007 ዕትም ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ “ዲያስፖራው ተስፋ የቆረጠና የተናደደ ነው፡፡ ተስፋ ስለቆረጠና ስለተናደደ ገዥው ፓርቲ የሚሰራው ሥራ ሁሉ ጥፋት ነው ብሎ ራሱን አሳምኖ ቁጭ ያለ ነው፡፡ በዚህም የሚናደድና የሚንቦገቦግ ነው፡፡ እናም ከእነዚህ ጋር ውይይት ማድረግ አይቻልም፡፡» ብለዋል። ፕሮፌሰር በየነ በዚሁ ቃለምልልሳቸው “ዲያስፖራውን ለመምከር እንሞክራለን» ካሉ በኃላ በአሜሪካ ቆይታቸው...

እኔም ሃና ነኝ ( ሄኖክ የሺጥላ )

  ሀና ላይ በተፈጠረው ነገር እጅግ አዝኛለሁ ፣ ሃና ላይ የደረሰው ነገር ሀገሬ ላይ እየደረሰ ያለውን ነገር እንዳስታውስ ነው ያረገኝ ። ሃናስ ታክሲ ውስጥ ነው የተደፈረችው ፣ ሀገሬ ግን በየጎዳናው ፣ ህገ ወጥ በሆነ የመሬት ንግድ ፣ ህገ ወጥ በሆነ እስር ፣ ህገ ወጥ በሆኑ ሕጋዊ ሌቦች ፣  ህገ ወጥ በሆነ ዶዘር ፣ ህገ ወጥ በሆነ ዱርዬ ቡድን እዚም እዛም ( ጭኑዋም ተረከዙዋም ፣ እጁዋም ወገቡዋም  ተደፍሮዋል ) ።   እንድ ነገር ለማከል ብዙ ሰዎች ” እኔም ሀና ነኝ ” ማለት ጀምረዋል ፣ ያዝልቅላችሁ ፣ ታዲያ በነካ እኔነታችሁ ” እኔም ራሴ እኔ ነኝ !” በሉኝ ።  ክርስቶስ...

Friday, 21 November 2014

ሰበር ዜና - የአ.አ አስተዳደር ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ሲባል በሰማያዊ ፓርቲ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ አለ

የአ.አ አስተዳደር ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ሲባል በሰማያዊ ፓርቲ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ አለ • ‹‹ማስጠንቀቂያውን እንደ ቁም ነገር አንቆጥረውም›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት • ‹‹ስርዓቱ ምን ያህል ዝቅጠት ውስጥ እንደገባ ያሳያል›› አቶ ግርማ በቀለ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ሰማያዊ ፓርቲ ያስተባበረው የ9ኙ ፓርቲዎች የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ፀረ ህገ መንግስት በመሆኑና ነዋሪዎችን ሰላምና ፀጥታ በማወኩ በቀጣይ ተመሳሳይ እንቅስቃሴ ካደረገ ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ሲባል እርምጃ እወስዳለሁ ሲል አስጠነቀቀ፡፡ አስተዳደሩ ትናንት ህዳር 11/2007 ዓ.ም በጻፈው ደብዳቤ፤ ህዳር 6 ቀን ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል በሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት...

በመርጫ “ለመሳተፍ” ጋዜጣዊ መግለጫ ለምን ? (ከይድነቃቸው ከበደ)

“አንደነት ፓርቲ” እንዲሁም ሌሎች የጉዳዩ ባለቤት የሆኑት አብዛኛው የተቃዋሚ ፓርቲዎች ከዚህ ቀደም ‹‹የፖለቲካ ምህዳሩ ጠቧል›› ከሚለው አልፈው ‹‹ ተዘግቷል›› ወደሚል ድምዳሜ መሸጋገራቸውን በተጨባጭ ማስረጃ ሲያጋልጡ እና ሲያረጋግጡ ከርመዋል፡፡እዚህ ደረጃ ላይ መድረሳችሁንም በተለያየ ወቅት በጋዜጣዊ መግለጫቸው ለሕዝብ አሳውቀዋል፡፡ “የፖለቲካ ምህዳር” ምርጫንም የሚያካትት ነው፡፡ ደካማ የመንግስት አስተዳደር ለመለወጥ ምርጫ ያስፈልጋል፡፡ይሁን እንጂ ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ ማካሄድ አይቻልም፡፡ የገዢው የወያኔ መንግስት ጉዳይ ፈጻሚው በሆነው፣ በምርጫ ቦርድ በኩል በተለመደው መንገድ፣ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ምርጫ ቢካሄድ የወያኔ መንግስት አሸናፊ ሆኖ የሚወጣበት እድሉ የሰፋ ነው፡፡...

Thursday, 20 November 2014

ምርጫ ሲባል አማራጭ ሳያሳጡ መሆን ይኖርበታል!!!

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ በሀገራችን ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ጊዜ ሀገራዊ ምርጫ እንደሚደረግ በመንግስት በኩል በከፍተኛ ደረጃ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል፡፡ ነገር ግን ከዚህ በፊት የተከናወኑት አራት ምርጫዎች ያየን እንደሆነ በሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ወደፊት ሊወስዱ እንዳልቻሉ እሙን ነው፡፡ ይህም ሆኖ የኢትዮጵያ ህዝብ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ፍላጎት በተለያየ መንገድ ሲገልፅ ቆይቷል፡፡ በተቃራኒው መንግስትና ገዢው ፓርቲ በፍፁም መለየት በሚያስቸግር ሁኔታ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ ሆነው ተቀናጅተው ለአንድ ለአውራ ፓርቲ ግንባታ እየሰሩ እንደሆነ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ይህ የመንግሥትና የገዢው...

Journey in the dark Oromo’s untold story in Eritrea

 The aim of this bulletin is not in any way to black mail any organization, but only to share my own ordeal and also send a message to my fellow Oromo youths. It is better to identify myself to all readers than to deeply tell my past back ground. Few years ago, I was a student at Jima University. While in university, I actively participated and contributed my share of expectation to the cause of Oromo students’ movement protesting...