Sunday 30 July 2017

የፓርላማ አባላት በድንገት ከዕረፍት ተጠሩ

ዋዜማ ራዲዮ- የሙስና  ተጠርጣሪዎች ቁጥር በየዕለቱ እያሻቀበ ባለበት በአሁኑ ወቅት ለእረፍት የተበተኑ የፓርላማ አባላት በሚቀጥለው ሳምንት መጀመርያ ወደ መዲናው ገብተው ሪፖርት እንዲያደርጉ በምክትል አፈጉባኤዋ መታዘዛቸው ታውቋል፡፡
ፓርላማው በዚህ ጥድፊያ ለምን እንደተጠራ ባይታወቅም ምናልባት ከሰሞኑ ያለመከሰስ መብቱ የሚነሳ ባለሥልጣን ይኖር ይሆን የሚለውን ግምት አጠናክሮታል፡፡ በሰኔ መጨረሻ የተበተነው ፓርላማ ለመጨረሻ ጊዜ የተመለከተው ጉዳይ ሰኔ 22 ኦሮሚያ ክልል ከአዲስ አበባ ይገባኛል የሚለውን ልዩ ጥቅም በተመለከተ ሲሆን ‹‹በቂ የመወያያ ጊዜ ያስፈልጋል›› በሚል ጉዳዩን ወደ 2010 ማዛወሩ ይታወሳል፡፡

ፓርላማው በመጪው ዓመት የመጀመርያ ወር የመጨረሻ ሳምንት ሥራውን እንደሚጀምር ቢታወቅም አሁን በፍጥነት እንዲሰበሰብ ጥሪ መደረጉ በርካታ መላምቶች እንዲፈጠሩ ምክንያት ሆኗል፡፡ በተለምዶ አብዛኛዎቹ የፓርላማ አባላት በእረፍት ጊዜያቸው ወደመረጣቸው ሕዝብ ተመልሰው ይሄዳሉ ቢባልም ይህ ተግባር በኢህአዴግ አባላትና አጋር ድርጅቶች በተሞላው ሸንጎ እምብዛምም የተለመደ አይደለም፡፡ ይልቁንም ክረምቱን አብዛኛዎቹ የምክር ቤቱ አባላት በገርጂና በፒኮክ በሚገኙ አፓርትመንቶቻቸው ሻይ ቡና እያሉ የሚያሳልፉት ቁጥር ከፍተኛ ነው፡፡


በምን ጉዳይ ለመምከር ምክር ቤቱ በዚህ ጥድፊያ ጥሪ ሊያስተላልፍ ይችላል በሚል በዋዜማ የተጠየቁ አንድ የቀድሞ የምክር ቤት አባል ምናልባት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በተመለከተ ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን ሰጥተዋል፡፡ 4 ወራት የተራዘመው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚያበቃው እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በኦገስት 9 2017 መሆኑ ይታወቃል፡፡

Saturday 29 July 2017

H. Res. 128, Supporting respect for human rights and encouraging inclusive governance in Ethiopia

On July 27, 2017, the full House Foreign Affairs Committee voted to advance a resolution, authored by Rep. Chris Smith (R-NJ), highlighting the human rights violations of the Ethiopian government, and offering a blueprint to create a government better designed to serve the interests of the Ethiopian people.

The resolution, which passed without objection, also calls on the U.S. government to implement Magnitsky Act sanctions, targeting the individuals within the Ethiopian government who are the cause of the horrific abuses.
The State Department’s current human rights report on Ethiopia notes, “[t]he most significant human rights problems were security forces’ use of excessive force and arbitrary arrest in response to the protests, politically motivated prosecutions, and continued restrictions on activities of civil society and NGOs.”
H. Res. 128, is like a mirror held up to the Government of Ethiopia on how others see them, and it is intended to encourage them to move on the reforms they agree they need to enact,” said Smith, Chair of the House panel on Africa. “For the past 12 years, my staff and I have visited Ethiopia, spoken with Ethiopian officials, talked to a wide variety of members of the Ethiopia Diaspora and discussed the situation in Ethiopia with advocates and victims of government human rights violations.  Our efforts are not a response merely to government critics, but rather a realistic assessment of the urgent need to end very damaging and in some cases inexcusable actions by the government or those who act as their agents.”
H. Res. 128, entitled “Supporting respect for human rights and encouraging inclusive governance in Ethiopia,” condemns the human rights abuses of Ethiopia and calls on the Ethiopian government to:
  • lift the state of emergency;
  • end the use of excessive force by security forces;
  • investigate the killings and excessive use of force that took place as a result of protests in the Oromia and Amhara regions;
  • release dissidents, activists, and journalists who have been imprisoned for exercising constitutional rights;
  • respect the right to peaceful assembly and guarantee freedom of the press;
  • engage in open consultations with citizens regarding its development strategy;
  • allow a United Nations rapporteur to conduct an independent examination of the state of human rights in Ethiopia;
  • address the grievances brought forward by representatives of registered opposition parties;
  • hold accountable those responsible for killing, torturing and detaining innocent civilians who exercised their constitutional rights; and
  • investigate and report on the circumstances surrounding the September 3, 2016, shootings and fire at Qilinto Prison, the deaths of persons in attendance at the annual Irreecha festivities at Lake Hora near Bishoftu on October 2, 2016, and the ongoing killings of civilians over several years in the Somali Regional State by police.
It is important to note that this resolution does not call for sanctions on the Government of Ethiopia, but it does call for the use of existing mechanisms to sanction individuals who torture or otherwise deny their countrymen their human and civil rights,” said Smith.
Smith has chaired three hearings on Ethiopia, the most recent of which looked into the deterioration of the human rights situation in Ethiopia and was titled “Ethiopia After Meles: The Future of Democracy and Human Rights.”

የአቶ አባይ ጸሐዬ ሚስት ወ/ሮ ሳሌም ከበደ በሙስና ተጠርጥረው ታሰሩ (ዘ-ሐበሻ)


አቶ አባይ ፀሐዬ የተለያዩ ጀኔራሎች ጋር በመደወልከዚህ ጉድ አድኑኝእያሉና ጫና ለማድረግ እየሞከሩ እንደሆነ ውስጥ አዋቂዎች ተናግረዋል። እንደ እነሱ አገላለፅ፣ የሙስና ወንጀሉ አጣሪዎቹ አባይ ፀሃዬ በህግ እንዲጠየቅ የወሰኑ ቢሆንም የፓርላማ አባል በመሆኑና ያለመከሰስ መብቱ እስኪነሳ እየተጠበቀ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

የቤት ብርበራ ትእዛዝ የወጣበት ቢሆንም የፓርላማ አባል ነኝ ብሎ ለጊዜው አስቁሟልበማለት ውስጥ አዋቂዎቹ ተናግረዋል፡፡ ጉዳዮ እስኪጣራ አቆየሁት እንጂ የውስጥ አዋቂዎቹ የአባይ ፀሐዬ ባለቤት / ሣሌም ከበደ መታሰሯን የጠቆሙኝ በትላንትናው ዕለት ነበር፡፡ ይህን ሲሉኝ የሪፖርተር ጋዜጣ የወ/ ሳሌም ከበደ ስምን አልተካተተም ነበር፡፡

ከተወሰነ መዘግየት፥ ማዘግየት በኋላ ግን በድህረገፁ ላይ አካትቷል፡፡

ሪፖርተር በሙስና ታሰሩ ብሎ ስማቸውን የዘረዘራቸው ሰዎች የሚከተሉት ናቸው

1.1 ቢሊዮን ብር በላይ ጉዳት በማድረስ የተጠረጠሩ ባለሥልጣናትና ነጋዴዎች ስም ዝርዝር

በታምሩ ጽጌ

ማክሰኞ ሐምሌ 18 ቀን 2009 .. መንግሥት እምነት በማጉደልና ሥልጣንን ያላግባብ በመገልገል በአገር ላይ 1.15 ቢሊዮን ብር በላይ ጉዳት አድርሰዋል ያላቸው ተጠርጣሪዎች ስም ዝርዝር ከዚህ እንደሚከተለው ነው፡፡

የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን

ኢንጂነር ፍቃዱ ኃይሌ
ኢንጂነር ዋሲሁን
ኢንጂነር አህመዲን
ሚስተር ሚናሽ ሌቪ (ትህዳር ኮንስትራክሽን ኩባንያ)
(198 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት በማድረስ)

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን

አቶ አብዶ መሐመድ
አቶ በቀለ ንጉሤ
አቶ ገላና ቦሪ
አቶ የኔነህ አሰፋ
አቶ በቀለ ባልቻ
አቶ ገብረ አናንያ ፃዲቅ
(646 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት በማድረስ)

መተሐራ ስኳር ፋብሪካ

አቶ እንዳልካቸው ግርማ
/ ሰናይት ወርቁ
አቶ አየነው አሰፋ
አቶ በለጠ ዘለለው
(13 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት በማድረስ)

ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር

አቶ ሙሳ መሐመድ
አቶ መስፍን ወርቅነህ
አቶ ዋሲሁን አባተ
አቶ ሥዩም ጎበና
አቶ ታምራት አማረ
አቶ አክሎግ ደምሴ
አቶ ጌታቸው ነገራ
/ ወርቁ አብነት (የሚኒስቴሩ ባልደረባ ያልሆኑ)
አቶ ታመነ ደባልቄ (የሚኒስቴሩ ባልደረባ ያልሆኑ)
አቶ ዮናስ መርአዊ (የሚኒስቴሩ ባልደረባ ያልሆኑ)
(2.2 ሚሊዮን ዶላር ወይም 51.2 ሚሊዮን ብር ጉዳት በማድረስ)

ተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ

አቶ አበበ ተስፋዬ
አቶ ቢልልኝ ጣሰው
(31 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት በማድረስ)

አቶ አበበ ተስፋዬ
አቶ የማነ ግርማይ (ጂዋይቢ ኮንስትራክሽን ኩባንያ)
አቶ ዳንኤል አበበ
(20 ሚሊዮን በላይ ጉዳት በማድረስ)

አቶ ፈለቀ ታደሰ
አቶ ኤፍሬም ታደሰ
(10 ሚሊዮን በላይ ጉዳት በማድረስ)

ኦሞ ኩራዝ ስኳር ቁጥር 5 ፋብሪካ

አቶ መስፍን መልካሙ
አቶ ሰለሞን ከበደ
ሚስተር ሊዮ (የቻይና ጁጂአይሺኢ ኩባንያ ሥራ አስኪያጅ)
አቶ ፀጋዬ ገብረ እግዚአብሔር ብርሃነ
/ ሳሌም ከበደ

(184 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት በማድረስ)

Wednesday 26 July 2017

“ተቃዋሚዎች ራሳችንን ማታለል የለብንም” ሌንጮ ለታ ከህብር ሬዲዮ-ሃብታሙ አሰፋ ጋር

<...ተቃዋሚዎች ራሳችንን ማታለል የለብንም። በአስቸኳይ ከኢህአዴግ ተቃራኒ የሆነ ሀይል መፍጠር አለብን። እነሱ ስልጣን ላይ ሲወጡ ሁለት ስትራቴጂ ነድፈው ነው። ከቻሉ ኢትዮጵያን መግዛት ካልቻሉ እስር በእርስ አጋጭተው አገሪቱን በትነው ወደ መጡበት መሄድ ነው። በአስቸኳይ አማራውም ሌላውም ብሄር የተወከለበት ...ሁል ጊዜ ከወያኔ የሚመጣ ነገር መጠራጠር አለብን። እነሱ በሚሰጡን አጀንዳ መነታረክ የለብንም የአዲስ አበባም ጉዳይ ቢሆን እነሱ አማራና ኦሮሞውን ለማጣላት ያመጡት ነው። ባይሆን እና የተሻለ ነገር ቢያስቡ ኖሮ ከተማዋን ...>
አቶ ሌንጮ ለታ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር(ኦዴግ) ሊቀመንበርና የኢትዮጵአ አገራዊ  ንቅናቄ ከፍተኛ አመራር ከህብር ሬዲዮ ጋር ካደረጉት ቃለ መጠይቅ የተወሰደ (ሙሉውን ያድምጡት)



Friday 14 July 2017

‹‹ለ12 ቀናት ቀዝቃዛ ባዶ ሲሚንቶ ወለል ላይ እንድተኛ ተደርጌያለሁ›› የኦፌኮ አመራር አቶ ደስታ ዲንቃ

ስም፡ደስታ ዲንቃ ጎሴ
ዕድሜ፡- 42 አመት
አድራሻ፡- ኦሮሚያ ክልል አዲስ አበባ ዙሪያ ዞን ሱሉልታ ወሰርቢ ቀበሌ
አሁን በእስር የምገኝበት ቦታ፡- ቂሊንጦ እስር ቤት

ለእስር የተዳረግሁበት ምክንያት፡- በሽብር ተከስሼ (በኦሮሚያ ክልል ተቀስቅሶ በነበረው ህዝባዊ የመብት ጥያቄ ወቅት አመጽ አነሳስተሃል፣ አደራጅተሃል በሚል)
በይፋ የተመሰረተብኝ የክስ አይነት፡- 25/09/08 . በፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ቀርቦብኝ ጉዳየን እየተከታተልሁ ነው፡፡ አቃቤ ህግ የጸረ-ሽብር አዋጁን አንቀጽ 4 እና 3(1)/3(2)/3(4) እና 3(6) በመተላለፍ ክስ አቅርቦብኛል፡፡ በዚህም፣ በሌላ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ከቀረበባቸው እነ ጉርሜሳ አያኖ ጋር በመሆን ኦፌኮን እንደሽፋን በመጠቀም ከኦነግ ጋር በህቡህ ግንኙነት በመፍጠር ሁከትና አመጽ በማስነሳት በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት በማድረስ ነው የከሰሱኝ፡፡ ጉዳዩን የሚያየው የፌደራሉ ከፍተኛ /ቤት ልደታ ምድብ 19 ወንጀል ችሎት ነው፡፡

በእስር በምገኝበት ወቅት የሚከተሉት የመብት ጥሰቶች ተፈጽመውብኛል፡፡

1. በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ በቆየሁበት ጊዜ በታሰርሁ በመጀመሪያዎቹ ሳምንታት ጠያቂ ተከልክያለሁ፡፡
2. በተጠረጠርሁበት የሽብር ወንጀል፣ የጸረ-ሽብር አዋጁ ከሚፈቅደው የምርመራ ጊዜ በተጻራሪ ከአምስት ወራት በላይ በምርመራ ላይ ቆይቻለሁ፡፡
3. በቂ የጸሐይ ብርሃንና ንጹህ አየር እንዳላገኝ ተደርጌያለሁ፡፡
4. 2008 . መጨረሻ በታሰርሁበት ቂሊንጦ እስር ቤት ተከስቶ የነበረውን የእሳት ቃጠሎ ተከትሎ በነበረው ጊዜ ቃጠሎውን ተከትሎ ወደሌሎች እስር ቤቶች እንዲዛወሩ ከተደረጉት መካከል ስሆን፣ ወደዝዋይ የፌደራል /ቤት ተወስጄ 12 ቀናት ባዶ ሲሚንቶ ላይ እንድተኛ ተገድጃለሁ፡፡
5. ዝዋይ እያለሁ እጆቼ ከአንድ እስረኛ ጋር ተጣምረው ታስሬ ነበር የምውለውና የማድረው፡፡
6. አንድ ቀን የታሰርሁበት ሰንሰለት በራሱ ጊዜ ተፈትቶ፣ስለምን ፈታኸው!› ተብዬ ከፍተኛ ድብደባ ተፈጽሞብኛል፡፡
7. ጠያቂ ተከልክየ ቤተሰቦቼን ሳላይ እንዳሳልፍ ተደርጌያለሁ፡፡

ባለትዳርና የቤተሰብ ኃላፊ ነኝ፤ ልጆች አሉኝ፡፡ የምወዳቸው እናቴ በእስር ቤት ሆኜ አርፈዋል፤ አልቅሼ መቅበር አልቻልሁም፡፡

በሙያዬ ደግሞ የህግ ባለሙያ ነኝ፡፡ በኦፌኮ ፓርቲ ውስጥ የህግ ክፍሉ እንዲጠናከር አስተዋጽኦ አድርጌያለሁ፡፡ 2006 . በአዲስ አበባና የኦሮሚያ ክልል ፊንፊኔ ዙሪያ ዞን ሊተገበር የታቀደውንማስተር ፕላንበመቃወም በአምቦና በወለጋ አካባቢዎች ተማሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ በማድረጋቸው ለእስር ሲዳረጉ የህግ ድጋፍ እሰጥ ነበር፡፡ በሀገር ውስጥ በህጋዊነት እውቅና አግኝተው ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል በሚያደርጉት የኦፌኮ እና ኦፌኮ አባል በሆነበት መድረክ ፓርቲዎች ውስጥ በተለያዩ የአመራር ቦታዎች ላይ ተሳትፎ አደርጋለሁ፡፡ በተለይም በወጣቶች ጉዳይ ኃላፊነትና በኦዲትና ኢንስፔክሽን በጸሐፊነት ሰርቻለሁ፡፡


የአቶ በቀለ ገርባ የሽብር ክስ ዉድቅ ተደረገ

በኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀ-መንበር በአቶ በቀለ ገርባ ላይ ከሽብር ጋር ተያይዞ የቀረበባቸዉ ክስ ውድቅ ተደረገ። ዛሬ ያስቻለው አራተኛ ወንጀል ችሎት ልደታ ምድብ አቶ በቀለ የተከሰሱበት ጉዳይ በመደበኛ የወንጀል ክስ እንዲታይ መበየኑን ጠበቃ አመኃ መኮንን ለዶይቼ ቬለ ገልፀዋል።


በፀረ-ሽብር አዋጁ አንቀፅ 3 የሽብር ድርጊት ፈፅመዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት አቶ ጉርሜሳ አያኖ፤ አቶ ደጀኔ ጣፋና አቶ አዲሱ ቡላላም ክሳቸው በሽብርተኛ ቡድን ውስጥ መሳተፍ ወደሚል ተቀይሮ ተከላከሉ ተብለዋል። ከነዚህ ሌላ አምስት ተከሳሾች ሰባተኛ ዘጠነኛ አስረኛ አስራ ሦስተኛ 22ተኛ ተከሳሾች ምንም መከላከል ሳያስፈልጋቸዉ በነፃ እንዲሰናበቱ የሚል ዉሳኔ ተላልፎአል። 

ቀሪ ተከሳሾች ከፀረ ሽብር ድርጅቶች ግንኙነት በማድረግና በመሳተፍ የሚል ሲሆን ይህንን የሚያስረዳ መረጃ በመኖሩ በዚሁ በቀረበባቸዉ ክስ እንዲከላከሉ መወሰኑን ችሎቱን የተከታተለዉ ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ገልጾልናል። ከችሎቱ በኋላ የአዲስ አበባዉን ወኪላችንን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔርን እና ጠበቃ አመኃ መኮንን በስልክ አነጋግረናል።

«ማእከላዊ ውስጥ ሴትነቴን ተመስርተው ጥቃት ፈጽመውብኛል» አክቲቪስት ንግስት ይርጋ

በይፋ የተመሰረተብኝ የክስ አይነት፡- የሽብር ክስ ሲሆን (‹‹ህዝባዊ አመጾችን››) በማደራጀትና በሰልፎቹም በመሳተፍ ‹‹የሽብር ቡድኖችን ተልዕኮ በመቀበል ለማስፈጽም መንቀሳቀስ›› የሚል ነው፡፡ የተጠቀሰው የህግ ክፍል ደግሞ የጸረ-ሽብር አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 3 4 እና 6 ላይ የተመለከቱትን ድርጊቶች በመተላለፍ ወንጀል ከሌሎች አምስት ሰዎች ጋር በአንደኛ ተከሳሽነት ነው የተከሰስሁት፡፡

የክስ ሂደቱን የሚያየው የፌደራል ከፍተኛ /ቤት ልድታ ምድብ 4 ወንጀል ችሎት ነው፡፡
በእስር በምገኝበት ወቅት የሚከተሉት የመብት ጥሰቶች ተፈጽመውብኛል፡፡

1. በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ እስር ቤት በቀዝቃዛና በጨለማ ክፍል ውስጥ ለረጅም ቀናት አስረውኛል፡፡
2. ያለማንም ጠያቂ፣ ያለሁበት ሁኔታ ሳይታወቅ ታፍኜ ለሳምታት እንድቆይ ተደርጌያለሁ፡፡
3. በማታ ለምርመራ በሚል ከታሰርሁበት ክፍል እያስወጡ ሰብዓዊ ክብሬን በሚያዋርዱ ተግባራትና ማሰቃየት ተፈጽሞብኛል፡፡
4. ክብሬን የሚነኩ፣ በማንነቴ ላይ የተመሰረቱ ስድቦች ተሰድቤያለሁ፡፡
5. ሴትነቴን ተመስርተው ጥቃት ፈጽመውብኛል፤ ሴት ሁኜ መፈጠሬን እንድትጠላ የሚያደርጉ ተግባራትን ፈጽመውብኛል፡፡
6. እርቃኔን አቁመው ተሳልቀውብኛል፡፡
7. የእግር ጥፍሮቼን መርማሪዎቼ ነቃቅለዋቸዋል፡፡ ጥፍሮቼን ከነቀሉ በኋላም ጥፍሮቼ የነበሩበትን ቦታ ቁስል እየነካኩ አሰቃይተውኛል፡፡
8. ጸጉሬን በመንቀልም የኢ-ሰብዓዊ ተግባር ሰለባ አድርገውኛል፡፡
9. ክስ ተመስርቶብኝ ቃሊቲ ከተዛወርሁም በኋላ የሰብዓዊ መብት ጥሰቱ አልቆመም፡፡ ጠያቂ ገደብ ተጥሎብኛል፡፡ እኔን መጠየቅ የሚችለው ቀድሞ ስም ዝርዝራቸው ለእስር ቤቱ አስተዳደር የታወቁ የቤተሰብ አባላት ብቻ ናቸው፡፡ ያም ሆኖ የቤተሰብ አባላትም ቢሆን ከምዝገባ ዝርዝሩ ውስጥ የተካተቱ ካልሆኑ መጠየቅ አይፈቀድም፡፡ በማነኛውም የስራ ሰዓት ሳይሆን ከስድስ ሰዓት እስከ ስድስት ሰዓት ተኩል ለሰላሳ ደቂቃ ብቻ ነው የምጠየቀው፡፡ ይህ ገደብ እንዲሻሻልልኝ ለፍርድ ቤት በተደጋጋሚ አቤት ብልም መሻሻል አልቻለም፡፡