Thursday 19 February 2015

“ዘመቻው በከፊል ተሳክቷል፤ ከጋዜጠኛ ተመስገን ጋር ተገናኝተናል”


ጋዜጠኛ ተመስገን የኢህአዴግን አሰራር በመቃወም ሃሳቡን ስለገለጸ “አሸባሪ” ተብሎ አሁን በእስር ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል። ነገሮችን የበለጠ ያከፋው ደግሞ ከቅርብ ግዜ ወዲህ፤ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በቤተሰቡም ሆነ በጓደኞቹ እንዳይጎበኝ መደረጉ ነበር። ከአንድ ወር በፊት ስንቅ ሊያቀብል የሄደው ወንድሙን ደብድበው፤ ምግቡን መሬት ላይ ደፍተው ገንዘቡን ጭምር ወስደው ከቃሊቲ እስር ቤት ያባረሩት መሆኑ የሚዘነጋ አይደለም።

ጋዜጠኛውን በፈጠራ ወንጀል ማሰር ሳያንስ እንዲህ ያለ ግፍ መፈጸም ኢሰብአዊነት መሆኑን በመግለጽ በርካታ ውትወታዎች ተደርገው ነበር። በቅርቡም የህገ መንግስቱ አንቀጽ 21 እንዲከበር እና የእስረኛ ሰብአዊ መብት እንዲከበር የሚጠይቅ የበይነ መረብ ዘመቻ ተካሂዷል። ይህ ዘመቻ በከፊልም ቢሆን ውጤት ያሳየ ይመስላል። ለመጀመሪያ ግዜ የተመስገን ወንድም እስር ቤት ሄዶ እንዲጎበኝ ተፈቅዶለታል። ሆኖም ጋዜጠኛ ተመስገን አሁንም በከፍተኛ የህመም ዝቃይ ውስጥ ነው። ህክምና እንዳያገኝ ተደርጓል። ይህም ሁኔታ የበይነ መረቡ ዘመቻ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመላካች ነው። ለማንኛውም የዘመቻው አስተባባሪዎች የሰጡትን አጭር መግለጫ ከዚህ ቀጥሎ አቅርበናል።

በቅድሚያ ያለፈውን ሳምንት አብራችሁን ለነበራችሁ የበይነ-መረብ ዘማቾችና ወዳጆች ምስጋና ይድረስ፡፡
በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ የምግብ የህክምናና የጎብኚ እግድ የተጣለው ከአንድ ወር በፊት ነበር፡፡ በዚህ የተቆጡ ቤተሰብና ወዳጆች ይህን መንግስታዊ ወንጀል ለማስቆም ይበጃል ያሉትን ሙከራ አድርገዋል፡፡ ለአምስት ተከታታይ ቀናት በበይነ-መረብና በተቋማት ቢሮዎች ላይ የተደረገው አስጨናቂ ህግን የማስከበር ውትወታ የመጀመሪያውን ውጤት አይቷል፡፡ ተመስገንንም በአካል ለማየት ተችሏል፡፡
የሰብአዊ መብት ኮሚሽን መርማሪዎችና በርከት ያሉ አጃቢ ወታደሮች ባሉበት፣ ከወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ ጋር ዛሬ የተገናኘው ጋዜጠኛ ተመስገን ጤንነቱ አደጋ ላይ እንዳለ መረዳት ተችሏል፡፡ ከዚህ ቀደም የነበረው የጀርባ ህመም አላስተኛ ወዳለው እብጠት መቀየሩንና የግራ ጆሮውም መስማት ወደማይችልበት ደረጃ መድረሱ ታውቋል፡፡ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኝ ለዝዋይ ማረሚያ ቤት ያቀረበው ጥያቄም እስካሁን ምላሽ እንዳላገኘ በቦታው ለነበረው ወንድሙ ገልጾለታል፡፡ አያይዞም ያለቀናት በቆየው ያላቋረጠ ዘመቻ ልባዊ ወዳጅነትን፣ ስስትንና ወንድማዊነትን ላሳያችሁ ወገኖች ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ምስጋና አቅርቧል፡፡
መጎብኘት እንደተፈቀደላቸው ከኮሚሽኑ መርማሪዎች በስልክ ማረጋገጫ ያገኙት ወንድሙና አንድ ወዳጁ ቢሆንም ሁለቱም ለመግባት የሚያስፈልገውን ምዝገባ ካሟሉ በኋላ የተመስገን ወዳጅ ተከልክሎ ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ እንዲገባ መደረጉ ለማወቅ ተችሏል፡፡

1 comment:


  1. A few versions were released offered in both steel and gold cases and either on a rolex replica uk matching diamond or leather band. There were even two movement options including a fake rolex sale basic COSC Chronometer 3-hand automatic and a world-timer. At 39mm wide it was considered large for its time, and in addition it has a unique style (not to mention diamond) that you simply can't find in anything else. You should also know that the Streamerica watches were designed by Switzerland fake rolex sale watch designer Jorg Hysek. The Tiffany & Company Streamerica was one of the first watches I ever wrote about on aBlogtoWatch back in 2007. I recently love the aesthetic and overall design. I've had the fake rolex sale pleasure of seeing a few in real life, but today they are chanel replica sale very rare even though they pop up from time to time at auction. I find myself that the Streamerica concept is one that Tiffany & Company. should come back to and that a timepiece similar to this may have been a bit ahead of its time, as back in the 1990s tastes were still rather conservative.

    ReplyDelete