Friday 31 January 2014

አትውረድ

ዳንኤል ክብረት


አንድ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር በዋናው በር በኩል ወደ አውራ ጎዳናው ይወጣል፡፡ ጥቂት እንደተጓዘ ደግሞ እዚያ አካባቢ ቆመው አላፊ አግዳሚውን ከሚላከፉ ጎረምሶች ጋር ይጨቃጨቃል፡፡ ጭቅጭቁ በምን እንደተጀመረ ማናችንም አላወቅንም፡፡ እነዚያ ጎረምሶች ግን በመምህሩ ላይ ‹ሙድ› ይዘውበታል፡፡ ‹እሺ - - ሊቁ› እያሉ በስድብ ጠረባ ይረፈርፉታል፡፡ እርሱ ደግሞ ስድቡን አልቻለበትም፡፡ ‹‹ያልተማራችሁ፣ ማይሞች፣ ከስድብ በቀር ሌላ የማታውቁ፣ ደደቦች›› ይላል ሥሩ እስኪገታተር ድረስ በቁጣ፡፡ በትከሻው ያንጠለጠለው ቦርሳ ይወዘወዛል፣ መነጽሩም ልውደቅ ልውደቅ ይላል፡፡
‹‹እሺ ሊቁ፣ ለምን ላፕቶፕሺን ከፍተሺ ዕውቀት አትጭኝብንም›› እያሉ ጎረምሶቹ ይሳሳቁበታል፡፡እርሱ ይበግናል፡፡ ‹ኤፍ ብቻ ነው እንዴ ቦርሳሽ ውስጥ የያዝሺው፤ በናትሺ አንድ አምስት ኤ የለሽም›› ይሉታል፡፡ እርሱ ይንዘፈዘፋል፡፡ ‹‹አንድ ሁለት ኤ ብትሰጭን ቸብ አርገን በርጫ እንገዛበት ነበር›› ይሉታል፡፡ ሰው እየተሰበሰበ፣ እየከበበው ይሄድና የጎረምሶቹን ስድብ እንደመዝናኛ ቆጥሮት አብሯቸው ይሳሳቃል፡፡ እርሱን ኮሜዲ ፊልም እንደሚሠራ ተዋናይ ቆጥረውት በነጻ ይኮመኩማሉ፡፡ ጎረምሶቹ አንድ ተረብ በወረወሩ ቁጥር ከብቦ የተሰበሰበው ‹አስገቡለት› እያለ እንደ ጎጃም ልቅሶ ያጅባቸዋል፡፡ 
 እየቆየ ከበባው እየሰፋ፣ ሳቁ እየደራ፣ የመምህሩ ንዴት ወደ እሳተ ገሞራነት እየተቀየረ ሄደ፡፡ መምህሩ ከዚያ ከበባ ልውጣ ቢል እንኳን ሰው በጎረምሶቹ ተረብ ስለተዝናና በቀላሉ የሚያስወጡት አይመስልም፡፡ የተከፈለው አዝማሪ መስሏል፡፡ የሚያውቃቸው ስድቦች አልቀውበት አሁን ጣቱን ማውጣትና ‹‹አሳይሃለሁ›› እያለ መዛት ጀምሯል፡፡ የአንዳንድ የእንግሊዝኛ ስድቦችን ሲሳደብም
የኛ ሙሽራ ኩሪባቸው
በእንግሊዝ አናግሪያቸው›› ብለው ሳቁበት፡፡ በልቡ አንዳች የፖሊስ ኃይል መጥቶ እንዲገላግለው እየተመኘ ነበር፡፡ ወደ ስድቡ ሜዳ አስቦ ስላልገባ አስቦ ሊወጣ አልቻለም፡፡
በዚህ መካከል በግራ እጃቸው ጋዜጣ አጣጥፈው የያዙ አንድ አዛውንት ሁላችንንም እየገፈተሩ፣ እንደ ሙሴ የሕዝቡን ባሕር ለሁለት እየከፈሉ ወደ መካከል መጡና ያንን መምህር እጁን ይዘው በዝምታ ጎትተው ከከበባው አወጡት፤ ጎረምሶቹም ‹ሼባው ልቀቀው እንጂ›› እያሉ ተረቧቸው፡፡ እርሳቸው ቀናም አላሉ፣ መልስም አልሰጡ፡፡ እየሰነጠቁ እንደገቡ፣ እየሰነጠቁ ወጡ፡፡
ከዚያም ወደ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን መታጠፊያ ዘወር አደረጉትና ‹‹ለምን ልጄ፣ ለምን?›› አሉት፡፡
‹‹ከዩኒቨርሲቲ ስወጣ ለከፉኝ፣ እኔም መልስ ሰጠኋቸው››
‹‹ተማሪ ነህ?››
‹‹የዩኒቨርሲቲ መምህር ነኝ››
‹‹እና መምህር ሆነህ ነው ከእነርሱ ጋር ስድብ የገጠምከው፤ ጥፋተኛው አንተ ነህ›› አሉት፡፡ እኛ ትንሽ ራቅ ብለን የሚሉትን መስማት ጀመርን፡፡
‹‹ተመልከት እዚያ›› አሉት በአመልካች ጣታቸው ወደ አንበሳ ግቢ አቅጣጫ እያመለከቱ፡፡ ‹‹እዚያ ግቢ ውስጥ ምን አለ?›› አሉና ጠየቁት፡፡
‹‹አንበሳ ነዋ››
‹‹አንበሳ ግን መኖሪያው ግቢ ውስጥ ነው እንዴ?››
‹‹አንበሳማ የዱር እንስሳኮ ነው፤ ምን ዓይነት ጥያቄ ነው የሚጠይቁኝ፤ የዩኒቨርሲቲ መምህር ነኝ እያልኩዎ›› መምህሩ ተናደደና ጥሏቸው ሊሄድ ከጀለ፡፡ እርሳቸውም ከእናቱ ጋር መንገድ እንደሚሻገር ሕጻን እጁን አጥብቀው ያዙት፡፡ ‹‹ወዳጂ፣ ሰው በሁሉም ነገር ሊቅ አይሆንም፡፡ በአንዱ ሊቅ ሲሆን በሌላው ማይም ነው፤ በአንዱ መምህር ሲሆን በሌላው ተማሪ ነው፤ በአንዱ ጎበዝ የሆነ ለሌላው ሰነፍ ነው›› አሉት፡፡ ትንሽ ቀዝቀዝ አለ፡፡
‹‹አንበሳው በገዛ ጫካው ውስጥ ቢሆን ኖሮ ማን ይደፍረው ነበር? ማን ጀግና ነበር ሃምሳ ሳንቲም ከፍሎ በሃምሳ ሜትር ርቀት የሚያየው? ማን ጀግና ነበር ቀርቦ ፎቶ የሚያነሣው? ማን ጀግና ነበር ከአንበሳው ጋር ፎቶ ሲነሣ የሚውለውጫካው የእርሱ ክልል ነው፤ የእርሱ ሠገነት ነው፡፡ እዚያ የቀለበቱ ጌታ (Lord of the Ring) እርሱ ነው፡፡ ከተማው ግን የአንበሳ መደብ አይደለም፣ እርሱ ለከተማ አልተፈጠረም፣ ከተማውን አይችልበትም፤ በግቢ ውስጥ መኖር፣ በአጥር መከለል፣ ከአንበሳው ተፈጥሮ ውጭ ነው፡፡ ስለዚህ ከሚያውቀው ወደማያውቀው፣ ከሠገነቱ ወደ ባርነቱ፣ ከሚያሸንፍበት ወደሚሸነፍበት፣ ከሚችልበት ወደማይችልበት፣ አወደርነውና፤ በከተማ፣ ግቢ ውስጥ አሥረን እንደልባቸውን እንጫወትበታለን፡፡ አሁን የሚፈልገውን አድኖ ሳይሆን የምንሰጠውን ይበላል፣ በፈለገው ሰዓት ሳይሆን በሰጠነው ሰዓት ይመገባል፣ ወደፈለገው ቦታ ሳይሆን ወደፈለግነው ቦታ ይሄዳል፣ የፈለገውን ሳይሆን የፈቀድንለትን ብቻ ያያል፡፡ ለምን? ወደኛ ሜዳ አውርደንዋላ፣ ሜዳውን ትቶ መጥቷላ፤››
ዝም አሉና ቀና ብለው አዩት፡፡ ቦርሳውን ወደ ላይ ገፋ ገፋ እያደረገ ይመለከታቸዋል፡፡ እኛም መጨረሻውን ለማወቅ ጓጉተን አፍጠን እናያቸዋለን፡፡ ስድብና ድብድብ ለማየት ተሰብስቦ የነበረው ሰውም ነገሩ ዕውቀትና ቁም ነገር ሲሆንበት ጊዜ ቀስ በቀስ ‹‹ሼባው ነገሩን ትምሮ አደረጉት›› እያለ ከአካባቢው ሸሸ፡፡ ‹‹የሚቧቀሱ መስሎኝ ነበር፤ ሼባው አበላሸው፡፡ ስድድቡ ተመችቶኝ ነበር ›› እያሉ በቁጭት ጥለዋቸው ሄዱ፡፡
‹‹አንተም እንደ አንበሳው ሆንክ›› አሉ ሽማግሌው፡፡ ወረድክ ከመደብህ፣ ከምትችለው የዕውቀት ክርክር ሜዳ፣ ከምታሸንፍበት የሃሳብ ክርክር ሜዳ፣ ከለመድከው የጥናት ክርክር ሜዳ፣ ወረድክላቸው፡፡ ጎበዞች ናቸው ደግሞ አድንቃቸው፡፡ አወረዱህና በሚችሉት ሜዳ ላይ በደንብ አድርገው ቀጠቀጡህ፡፡ አንተም ሞኝ ነህ በማታውቀው ሜዳ ላይ ትግል ገጠምክ፡፡
‹‹ሶምሶን ከፍልስጤማውያን ዐቅም በላይ ሲሆንባቸው፡፡ ፍልስጤማውያን ምን አደረጉ? በደሊላ በኩል ሶምሶን ወደማይችለው እነርሱ ግን ወደሚችሉት ሜዳ አወረዱት፡፡ በሚችሉት ሜዳ አውርደው ደኅና አድርገው ቀጥቅጠው ያንን ኃያል ሰው ወፍጮ ፈጭ አደረጉት፡፡
‹‹ብልጥ ከሆንክ አትውረድ፣ ጀግና ከሆንክ የወረዱትን አውጣቸው፡፡አሁን አሁን ብዙ ሰው በዚህ እየተሸነፈብን ነው፡፡ እስኪ ጋዜጣውን፣ መጽሔቱን፣ ፌስ ቡኩን፣ ሰልፉን፣ የፖለቲካ ክርክሩንም ተመልከተው፡፡ ብዙዎቹ ከሜዳቸው ወርደዋል፡፡ ብልጦቹ ከፍ ወዳለው ሃሳብ፣ ዕውቀት ወደሚጠይቀው ክርክር፣ በመረጃና በማስረጃ ወደሚደረገው ውይይት፣ ላቅ ወዳለ ትግል፣ ወደ ልዕልናና ወደ ሠለጠነ አስተሳሰብ ማደግ እንደማይችሉ ያውቁታል፡፡ በዕውቀትና በሃሳብ ክርክር፣ በሠለጠነና ደርዝ ባለው ትግል፤ ማንበብን፣ ማወቅን፣ መመራመርን፣ በሚጠይቅ መሥመር መጓዝ፣ ተጉዘውም ማሸነፍ እንደማይችሉ ያውቁታል፡፡ ስለዚህ አንተን መሰል ሰዎችን ወደ ሜዳቸው ‹ውረድ እንውረድ› ብለው ያወርዷችኋል፡፡ በእነርሱ አጀንዳ፣ በእነርሱ ዐቅም፣ በእነርሱ ተራ ነገር፣ በእነርሱ አሉባልታ፣ በእነርሱ ስድድብ፣ በእነርሱ ጠባብነትና ጎጠኝነት፣ በእነርሱ ወንዘኛነትና መንደርተኛነት፣ በእነርሱ ተረብ ይገጥሟችኋል፡፡ ከዚያም ያሸንፏችኋል፡፡ አሁንማኮ ሁላችንንም አወረዱን፣ እንደነርሱ እንድናስብ፣ እንደነርሱ እንድንጽፍ፣ እንደነርሱ እንድንደራጅ፣ እንደነርሱ እንድንናገር፣ እንደነርሱ እንድንዘፍን፣ እንደነርሱ እንድናምን፣ እንደነርሱ እንድንለብስ አደረጉንኮ፡፡

አትውረድ ልጄ፣ ዕውቀት ዋጋ ወደማታገኝበት፣ ሃሳብ ልዕልት ወደማትሆንበት፣ ችሎታ ወደሚያስቀጣበት አለማወቅ ወደሚያስከብርበት፣ ማይም አለቃ ወደሆነበት፣ ክርክር ተረብ ወደሆነበት፣ ውይይት እንደ ኮካ ኮላ ጠርሙስ አንድ ዓይነት ወደሆነበት፣ አላዋቂዎች ወደሠለጠኑበት፣ ከብት ካለው ይልቅ አፍ ያለው ወደተሾመበት ሜዳ አትውረድ፡፡ ከወረድክ ግን በማታውቀው ሜዳ፣ በማታውቀው ስልት፣ በወረደ ትግል ይደበድቡሃል፡፡ አትውረድ ልጄ፡፡ አትውረድ፡

Thursday 30 January 2014

Ethiopia - Land for Sale




As the economy thrives, we examine the plight of Ethiopians forced from their land to make way for foreign investors.


Just a few decades ago, Ethiopia was a country defined by its famines, particularly between 1983-1985 when in excess of half a million people starved to death as a consequence of drought, crop failure and a brutal civil war.

Against this backdrop, it is impressive that in recent years, Ethiopia has been experiencing stellar economic growth. The headline statistics are certainly remarkable: the country is creating millionaires faster than any other in Africa; output from farming, Ethiopia’s dominant industry, has tripled in a decade; the capital Addis Ababa is experiencing a massive construction boom; and the last six years have seen the nation’s GDP grow by a staggering 108 percent.

But it is not all positive news, because for all the good figures there are still plenty of bad ones.
Around 90 percent of the population of 87 million still suffers from numerous deprivations, ranging from insufficient access to education to inadequate health care; average incomes are still well below $1500 a year; and more than 30 million people still face chronic food shortages.

And while there are a number of positive and genuine reasons for the growth spurt - business and legislative reforms, more professional governance, the achievements of a thriving service sector - many critics say that the growth seen in agriculture, which accounts for almost half of Ethiopia’s economic activity and a great deal of its recent success, is actually being driven by an out of control ‘land grab', as  multinational companies and private speculators vie to lease millions of acres of the country’s most fertile territory from the government at bargain basement prices.

At the ministry of agriculture in Addis Ababa, this land-lease programme is often described as a "win-win" because it brings in new technologies and employment and, supposedly, makes it easier to improve health care, education and other services in rural areas. 
"Ethiopia needs to develop to fight poverty, increase food supplies and improve livelihoods and is doing so in a sustainable way," said one official.

But according to a host of NGO’s and policy advocates, including Oxfam, Human Rights Watch and the Oakland Institute, the true consequences of the land grabs are almost all negative. They say that in order to make such huge areas available for foreign investors to grow foodstuffs and bio-fuels for export - and in direct contravention of Ethiopia’s obligations under international law - the authorities are displacing hundreds of thousands of indigenous peoples, abusing their human rights, destroying their traditions, trashing the environment, and making them more dependent on food aid  than ever before.

"The benefits for the local populations are very little," said renowned Ethiopian sociologist Dessalegn Rahmato. "They’ve taken away their land. They’ve taken away their natural resource, because these investors are clearing the land, destroying the forest, cutting down the trees. The government claims that one of the aims of this investment was to enable local areas to benefit by investing in infrastructure, social services … but these benefits are not included in the contract. It's only left up to the magnanimity of the investor."

And those investors, he continued, are simply not interested in anything other than serving their own needs: "They can grow any crop they want, when they want it, they can sell in any market they want, whether it’s a global market or a local market. In fact most of them are not interested in the local markets.” 
He cited as an example a massive Saudi-owned plantation in the fertile Gambella region of south west Ethiopia, a prime target area for investors: "They have 10,000 hectares and they are producing rice. This rice is going to be exported to the Middle East, to Saudi Arabia and other places. The local people in that area don’t eat rice."

But the most controversial element of the government’s programme is known as 'villagisation' - the displacement of people from land they have occupied for generations and their subsequent resettlement in artificial communities.

In Gambella, where two ethnic groups, the Anuaks and the Nuers, predominate, it has meant tens of thousands of people have been forced to abandon a traditional way of life. One such is Moot, an Anuak farmer who now lives in a government village far from his home.

"When investors showed up, we were told to pack up our things and to go to the village. If we had decided not to go, they would have destroyed our crops, our houses and our belongings. We couldn't even claim compensation because the government decided that those lands belonged to the investors. We were scared … if you get upset and say that someone stole your land, you are put in prison. If you complain about being arrested, they will kill you. It's not our land anymore; we have been deprived of our rights."

Despite growing internal opposition and international criticism, the Ethiopian government shows no sign of scaling the programme back. According to the Oakland Institute, since 2008, an area the size of France has already been handed over to foreign corporations. Over the next few years an area twice that size is thought to be earmarked for leasing to investors.

So what does all this mean for the people on the ground? In Ethiopia – Land for Sale, filmmakers Veronique Mauduy and Romain Pelleray try and find out.

source_Aljazeera

Wednesday 29 January 2014

ጎንደር በሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄዎች ተወጥራለች

ሰንደቅ-ጋዜጣ

በመጪው እሁድ ጥር 25 ቀን 2006 ዓ.ም በጎንደር ከተማ ሰማያዊ ፓርቲ በኢትዮ-ሱዳን ድንበር መካከለል ጉዳይ ለሕዝብ ግልፅ አለመሆኑን በመቃወም ሰልፍ የጠራ ሲሆን፤ በተመሳሳይ ቀን በጎንደር ዙሪያ የሚኖሩ የቅማንት ብሔረሰብ አባላት ማንነታችን አልተከበረም በሚል ሕገ-መንግስታዊ ጥያቄአቸውን ለማቅረብ የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ አቅርበዋል።

ለጎንደር ከተማ አስተዳደር ሁለቱም ወገኖች የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ቢያቀርቡም፤ ለሁለቱም ወገኖች ለሰላማዊ ሰልፉ መካሄድ ማረጋገጫ አለማግኘታቸውን እየተናገሩ ነው። ሰማያዊ ፓርቲ ሰልፉን ለማስተባበር ወደስፍራው የላከውን የፓርቲውን አመራር ጨምሮ ሌሎች የፓርቲው አስተባባሪዎች ታስረው መፈታታቸውን ገልጿል። ሆኖም ሰልፉን ለማካሄድና የማሳወቂያ ደብዳቤ ለከተማው አስተዳደር ቢያቀርቡም አስተዳደሩ ደብዳቤውን ባለመቀበሉ ጠረጴዛ ላይ ትተው መውጣታቸውን የፓርቲው ሕዝብ ግንኙነት አስታውቋል። እስካሁን የከተማው አስተዳደር ምንም አይነት ምላሽ ያልሰጠ በመሆኑ ሰላማዊ ሰልፉ እንደተፈቀደ በመቁጠር ሰልፉን ለማካሄድ በዛሬው ዕለት 12 የአመራር አባላት ያሉት ቡድን ወደ ጎንደር እንደሚሄድ አስታውቋል።

በሌላ በኩል በበርካታ ጊዜያት የቅማንት ብሔረሰብ የቋንቋ፣ የባህልና የማንነት መብቱ አልተጠበቀም የሚሉ ወገኖች በተመሳሳይ ቀን (ጥር 25 ቀን 2006 ዓ.ም) ጥያቄአቸውን በሰላማዊ ሰልፍ ለመጠየቅ ሰልፍ መጥራታቸውን የቅማንት ብሔረሰብ የማንነት የራስ አስተዳደር ጥያቄ አስተባባሪ ኮሚቴ ሊቀመንበር አቶ አበራ አለማየሁ ለሰንደቅ ጋዜጣ አስታውቀዋል።

የኮሚቴው ሊቀመንበር የጎንደር ከተማ በጉዳዩ ላይ ለማነጋገር ጥረት ማድረጋቸውን ገልፀዋል። አስተዳደሩም የእነሱ ጥያቄ ሕገ-መንግስታዊ እንጂ የፖለቲካ አይደለም። ነገር ግን እናንተ ጥያቄ ካቀረባችሁ በኋላ ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ጠይቋል በማለት አጀንዳችሁ ተመሳሳይ ነው የሚል ጥያቄ ቀርቦላቸው አጀንዳችን የተለያየ መሆኑን ብንገልጽም፤ “በጥይት ትመታላችሁ፣ መትረየስ ጠምደን እንፈጃችኋለን” እያሉ እያስፈራሩን ነው ብለዋል።

ከዚህ ቀደም ጥር 4 ቀን 2006 ዓ.ም በጅልጋ ወረዳ አይከል ከተማ ላይ ከ70 ሺህ በላይ ሕዝብ የተገኘበት ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸውን ያስታወሱት አቶ አበራ፤ በዚያን ጊዜም “በመትረየስ እንፈጃችኋለን” ቢሉንም ሕዝቡ ነቅሎ መውጣቱን ተናግረዋል። አሁንም በጎንደር ከተማ ከሰማያዊ ፓርቲ ቀድመው ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ቢዘጋጁም በየቀበሌው ሕዝቡን በስብሰባ በመጥራት ወደ ሰልፉ እንዳይወጡ ቅስቀሳ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም ያለውን ጫና ተቀቁመው ሰልፉን ለማካሄድ ወደኋላ እንደማይመለሱ ተናግረዋል።
እንደ አቶ አበራ ገለፃ፤ እነሱ የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘው በተመሳሳይ ቀን ሰማያዊ ፓርቲ በሌላ አጀንዳ ሰልፍ በመጥራቱ እኛም ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር አብረን እንደምንሰራ ተደርጎ ታይቶብናል ብለዋል። ይሁን እንጂ የእኛ ጥያቄ ሕገ-መንግስታዊ እንጂ የፖለቲካ ወይም የድንበር አይደለም ብለዋል።

የቅማንት ብሔረሰብ በአማራ ክልል በጎንደር የተለያዩ ወረዳዎች የሚኖር ሕዝብ መሆኑን የጠቀሱት አቶ አበራ፤ የሕዝብ ብዛቱም አንድ ሚሊዮን እንደሚሆን፣ የቋንቋው ተናጋሪዎችም ከ20 ሺህ በላይ እንደሚሆኑ ገልፀው፤ ሕዝቡ እራሱን በቻለ ዞን ለመተዳደር ተደጋጋሚ ጥያቄዎችን ሲያቀርብ ቆይቷል ብለዋል። በያዝነው ዓመት መስከረም ወር ጥያቄውን ለፌዴሬሽን ም/ቤት አቅርቦ ውሳኔ አለማግኘቱንም ተናግረዋል። የጎንደር ከተማ ከንቲባ አቶ ጌትነት አማረን በስልክ አግኝተን በዚሁ ጉዳይ ላይ የአስተዳደራቸውን አቋም እንዲያብራሩልን ያደረግነው ተደጋጋሚ ጥረት አልተሳካም።

Tuesday 28 January 2014

2014 Golden Pen of Freedom awarded to jailed Ethiopian journalist


Eskinder Nega, an Ethiopian publisher, journalist and blogger who is serving an 18-year jail sentence under anti-terror legislation, has been awarded the 2014 Golden Pen of Freedom, the annual press freedom prize of the World Association of Newspapers and News Publishers (WAN-IFRA).
Mr Nega was arrested on September 14, 2011 after publishing an article criticising his government’s use of the 2009 Anti-Terror Proclamation to jail and silence critics, including Ethiopian actor and activist Debebe Eshetu.  He was sentenced on 23 January 2012 and denounced as belonging to a terrorist organisation.

In making the award, the WAN-IFRA Board sent a message to the Ethiopian government that misusing anti-terror legislation to jail journalists and those critical of his government is unwarranted and against international protocols, including the Vienna Declaration on Terrorism, Media and the Law.

“This award recognises the courage of Eskinder Nega to speak out despite the risks that saw him jailed under his country’s draconian and overly broad anti-terror laws,” said WAN-IFRA President Tomas Brunegård, speaking on behalf of the Board.

“We call on the Ethiopian government to release Eskinder Nega and all journalists convicted under the sedition provisions, including Solomon Kebede, Wubset Taye, Reyot Alemu, and Yusuf Getachew”, said Mr Brunegård, who recently visited Ethiopia as part of an international mission that found that the country’s publishers and journalists practice journalism in a climate of fear.

The Golden Pen of Freedom is an annual award made by WAN-IFRA since 1961 to recognise the outstanding action, in writing or deed, of an individual, a group or an institution in the cause of press freedom. More on the Golden Pen can be found at http://www.wan-ifra.org/node/31099

The award will be presented on 9 June during the opening ceremonies of the World Newspaper Congress, World Editors Forum and World Advertising Forum, the global summit meetings of the world’s press, to be held in Torino, Italy.

In an opinion piece published in the New York Times, Mr Nega said of his imprisonment: “I’ve never conspired to overthrow the government; all I did was report on the Arab Spring and suggest that something similar might happen in Ethiopia if the authoritarian regime didn’t reform... I also dared to question the government’s ludicrous claim that jailed journalists were terrorists.”

WAN-IFRA has been vocal in their opposition to Ethiopia’s misuse of anti-terror legislation, writing to late Prime Minister H.E. Meles Zenawi in 2012 requesting the immediate release of Mr Nega and most recently demanding his release, along with four other imprisoned journalists, in a joint international press freedom mission to Ethiopia, conducted with the International Press Institute. The full report from the international press freedom mission can be found at http://www.wan-ifra.org/node/97172

Mr Nega opened his first newspaper, Ethiopis, in 1993, which was soon shut down by authorities due to its critical reporting. He then, along with his wife Serkalem Fasil, managed Serkalem Publishing House, responsible for newspapers such as Asqual, Satenaw and Menelik, all of which are currently banned in Ethiopia.  He has also had his journalist’s licence revoked since 2005, but continued to publish articles despite the ban.

Mr Nega is no stranger to being imprisoned due to his writings. He was detained at least seven times under Prime Minister Meles Zenawi.  This included a 17-month jail sentence, along with his wife, on treason charges for their critical reporting on the Meles government's violent response to peaceful protests that followed the disputed 2005 elections.

WAN-IFRA, based in Paris, France, and Darmstadt, Germany, with subsidiaries in Singapore and India, is the global organisation of the world’s newspapers and news publishers. It represents more than 18,000 publications, 15,000 online sites and over 3,000 companies in more than 120 countries. Its core mission is to defend and promote press freedom, quality journalism and editorial integrity and the development of prosperous businesses.


ዓረና ትግራይ ራኢዩን የትግራይ ብሎም የኢትዮጵያ ህዝብ ምርጫ በማድረግ ወደፊት ይገሰግሳል እንጂ በህወሓት የሽብር ተግባር አይታጠፍም !!! (ከዓረና ትግራይ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ)

 


የዓረና ትግራይ 3ኛ ድርጅታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎች ተግባራዊ ለማድረግ በትግራይ ከተሞች ተከታታይ የህዝብ ፖለቲካዊ ስብሰባዎች በማካሄድ በክልሉ ያንሰራፋው ብልሹ ኣስተዳደር ምንጩና መፍትሄው፣ የዓረና ትግራይ ፓርቲ የፖለቲካ ራኢና ኣማራጭ ያንሰራፋው ብልሹ ኣስተዳደር የማስቀረት ብቃት ለማሣየት አስመልክቶ ከህዝብ ለመምከርና በትግራይ ከተሞች ህዝባዊ ፖለቲካዊ ስብሰባዎች ለማካሄድ እቅድ ተይዞ ከመጀመርያው የጥቅምት ወር 2006 ዓ/ም ጀምሮ በተከታታይ ለማካሄድ እንቅስቃሴ ተጀመረ። ህዝባዊ ፖለቲካዊ ስብሰባው በቅደም ተከተላቸው በውቕሮ፣ በማይጨው፣ በዓብይ ዓዲ ከተሞች ህዝባዊ ፖለቲካዊ ስብሰባዎች ሲካሄዱ ህዝብ ወደ ስብሰባው እንዳይመጣ የማደናቀፍ ተግባር በገዢ ፓርቲው የአከባቢ ካድሬዎች የታየ ቢሆንም ህዝቡ የማዳመጥ ፣አስተያየት የመስጠት መብቱን ለመጠቀም ባሳየው ፍላጎት በስብሰባው አዳራሽ በመገኘቱ ውጤታማ የህዝብ ስብሰባዎች ማካሄድ የተቻለ ሲሆን በሽረ ከተማ የህዝብ ስብሰባ ለማካሄድ ህዝቡ ወደ ስብሰባ ኣዳራሽ እንዲመጣ በሚገባ ከተቀሰቀሰ ህዝቡም ጥሪውን ኣክብሮ ወደ ኣዳራሹ በጥዋቱ እንደመጣ የከተማው ኣስተዳደርና በፓርቲው መዋቅር በተደራጀ ረብሻ የህዝብ ስብሰባው ሳይካሄድ መቅረቱን ይታወሳል፡፡

 በዕቅዱ መሰረት ፓርቲያችን በምስራቃዊ ዞን ዋና በዓዲግራት ከተማ ጥር 18 ቀን 2006 ዓ/ም የህዝብ ፖለቲካዊ ስብሰባ ለማካሄድ ኣዳራሽ እንዲሰጠን ለከተማው ኣስተዳደር ተጠይቆ ኣዳራሽ ተይዞኧል ኣይቻልም የሚል መልስ በመስጠታቸው እንግዲያው ስብሰባው በኣደባባይ እናደርገዋለን ሲባሉ ተመልሰው ኣዳራሽ ተፈቅዶላችኃል የሚል ምላሽ ተስጥቶን በስብሰባው ቀን ህዝቡ ተገኝቶ ዓረና ባዘጋጀው ኣጀንዳ እንዲመክር ለማስቻል የዓረና ከፍተኛ ወጣት ኣመራሮችና ኣባሎች በዓዲግራት ከተማና ኣከባቢዋ ተሰማርተው በሕገ መንግስቱ የተረጋገጡ ሃሳብነ በነፃ የመግለፅና የፖለቲካ ፓርቲዎች የመንቀሳቀሰ ነፃነት የሚያረጋግጡ መብቶች በመጠቀም በህዝባዊ ስብሰባው የሚመክርባቸው ኣጀንዳዎችና የስብሰባው ቀን፣ ስዓትና ቦታ የሚገልፀው ፅሑፍ በማደል ተሰማርተዋል፡፡

ለህዝቡ የሚታደለው ፅሑፍ የሚፈነዳ ቦንብ ኣልነበረም ወደ ህዝቡ ህሊና ዘልቆ የሚገባ ሓሳብ ብቻ ነበር፡፡ ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ዓረና ትግራይ የመሬት ባለቤትነት የመንግስት መሆኑ ቀርቶ የህዝብ/ዜጎች እንዲሆን የመሬት ሊዝ ኣዋጅ እንዲሻር፣ ዜጎች ለመኖርያ የሚስፈልጋቸው ቦታ በሕገ መንግስቱ መሰረት ያለ ሊዝ የማግኘት መብታቸው እንደሚረጋገጥ፣ ለወጣት ሴቶችና ወንዶች በግፍ ለስደት መዳረግ ምክንያት የሆነው ብልሹ ኣስተዳደር በማስወገድ በሃገራቸው ሥራ የማግኘት መብታቸው እንደሚረጋገጥ፣ የሙያ ብቃት መስፈርት መሰረት ባደረገ መርህና የሙያና የኣካዳሚ ነፃነት በማረጋገጥ የመመህራንና የመንግስት ሠራተኞች ችግር ለማስወገድ እንደምንሰራ፣ በኣስገዳጅ የማዳበርያ ግዢ ለገዢው ፓርቲ የንግድ ድርጅቶች ብዝበዛ የተጋለጡና በእዳ ተጭነው ለጎስቋላ ኑሮ የተዳረጉት የትግራይ ገበሬዎች ችግር ለማስወገድ የማደባርያ ግዢ በውዴታ እንደሚሆንና ግብርናውና ገበሬው ለመደገፍ ለገበሬው ድጎማ ማድረግ እንደማያስፈልግ፣ ትምህርት ቤቶች ከፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ነፃ እንደሚሆኑ ዋና ስራቸው የፓርቲ ኣባል ምልመላና በትምህርት ቤቶች ለሚነሱ የመብት ጥያቂዎች ማኮላሸት የሆነ የህ.ወ.ሓ.ት (ኢህኣደግ) የ 1-5 የትምህርት ኔትወርክ እንደሚቀር፣ በትግራይ ህዝብ ደምና ኣጥንት የተገኘው ሙሉ በሙሉ የትግራይ ህዝብ ሃብትና ንብረት የሆነው ት.እ.ም.ት ከህወሓት መንጋጋ ኣውጥቶ ተጠሪነቱ ለክልሉ መንግስት በሆነ በነፃ የባለሙያ ቦርድ እንዲተዳደር በማድረግ የክልሉን ማሕበራዊ ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ለመፍታት እነዲውል የማደረግ መሆኑ፣ በት.እ.ም.ት ሥር የሚተዳደሩ የልማት ድርጅቶች ሠርተው የሚያገኙት ትርፍ በትግሉ ለተጎዱ ታጋዮችና ሲቭል ኣርበኞች እንዲሁ የሻዕብያን ወራራ ለመመከትና ሃገራቸውን ለመጠበቅ ለጉዳት የተዳረጉ ኣርበኞችና ቤተሰባቸውን ለመደገፍ እንደሚውል፣በሕገ-መንግስቱ እንደተደነገገው ገዢው ፓርቲ በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባት እንዲያቆም የሚጠይቁ ነበሩ፡፡ እነዚህ የአማራጭ ፖለቲካዊ ፕሮግራም ኣጀንዳዎች ሙሉ በሙሉ ሓሰቦች እንጂ የሚፈነዱ ፈንጂዎች ኣልነበሩም ! እነዚህ በጠራራው ፀሃይ ለህዝቡና ለህ.ወ.ሓ.ት ኣባላትና ደጋፊዎች ጭምር የቀረቡ ኣጀንዳዎች ነበሩ፡፡

እነዚህ ለህዝቡ የቀረቡ የአማራጭ ፖሊሲ ኣጀንዳዎች በሳዕሲዕ ፃዕዳ እንባ ወረዳ ዋና ከተማ ዕዳጋ ሓሙስ ለህዝቡ ሲታደሉ አንዲት ወረቀት ሳትቀደድ ኣንድ ሰው እንኳን ኣልቀበልም ሳይል ሁሉም በደስታ ተቀብሎ ለወጣት ኣመራሮቹ በኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርስቲ የታሪክ ሙሩቕና የዓረና የሥራ ኣስፈፃሚ ኣባልና የህዝብ ግንኙነት ሓላፊ ኣቶ ዓምዶም ገ/ስላሴና መም/ ሃይለ ገብረፃዲቕ ያሳየው አክብሮት የሚደነቅ እንደነበረ ይመሰክሩለታል፡፡ በሻዕብያ የወደመችው የጎሎመኸዳ ወረዳ ዋና ከተማ የነበረችው ውብዋ ዛላንበሳን በመተካት የከተመችው የፋፃ ከተማ ነዋሪዎችና የኣካባቢው ገበሬዎች የስብሰባው ኣጀንዳ፣ ጊዜና ቦታ የሚገልፀው ፅሑፍ ሲታደላቸው ህዝቡ በሰላም ተቀብሎ እንዳስተናገዳቸው ” ቀድመን መመጣታችሁ ብናውቅ ኖሮ ሻይ ቁርስ ኣዘጋጅተን እነቆይ ነበር” በማለት በኣክብሮት እንደተቀበላቸው በኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ ምሩቅና የዓረና ትግራይ የድርጅት ጉዳይና የፅሕፈት ቤት ሓላፊ የሆኑት ኣቶ ስልጣኑ ሕሸ ና ኣቶ ሃይለኪሮስ ተፈሪ የህዝቡ ጨዋነት እንግዳ ተቀባይነትና ለኣማራጭ ሓሳብ ያለው ጥማት ይመሰክሩለታል፡፡ የዓዲግራት ከተማ ህዝብ ኣቀባበልም ተመሣሣይ ነበር፡፡

የህዝቡን የልብ ትርታ ያለማራቸው የዘኑ የገዢው ፓርቲ ኣስተዳዳሪዎች ዓረናና ህዝቡ የማይገናኙበት፣ የህዝቡ ስብሰባ የማካሄድበትና የዓረና ወጣት ኣመራሮች ሞራላቸው ተጎድቶ የሚያርፍበት እኩይ ብልሃት መዘየድ ጀመሩ፡፡ በዕዳጋ ሓሙስ የህ.ወ.ሓ.ት መታወቅያቸውን በማሣየት ለህዝቡ የስብሰባ ጥሪ የሚያድሉ የዓረና ኣባላትን ማቆም ጀመሩ፤ በፓርቲ መታወቅያ የመንግስት ሥራ መስራት ኣትችሉም ሲባሉ ሁሉም በእጃቸው ሁሉም በደጃቸው የሆነላቸው የህወሓት አባላቱ ወድያው ፖሊስ ጠርተው የዓረና ኣባላትን ኣቶ ዓምዶም ገ/ስላሴንና መም/ሃይለ ገ/ፃድቅን ወደ ፖሊስ ጣብያ በእስር ወሰዱ፡፡ አባላቶቻችን መታወቅያቸውን እንዲያሳዩ ተጠየቁ ኣሳዩ፡፡ (1) መመ/ሃይለ ገ/ፃድቅ የዓረና መታወቅያ ስለሌህ የዓረና ፅሑፍ ማደል ኣትችልም ተባለ (2) የሚታደሉት ፅሑፍ የዓረና ማህተም ስለሌለው ለህዝብ መሰጠት ኣትችሉም ተባሉ (3) ፅሑፍ እያደላችሁ የመኪና መንገድ ትዘጋላችሁ ኣሉ የህወሓት ካድሬዎቹ በድፍረት !? በስንት ንትርክ ለሚያጋጥማቹሁ አደጋ በራሳችሁ ሓላፊነት ተብለው ሥራቸውን ቀጠሉ፡፡ በራሳችሁ ሓላፊነት? ሲባል ብትደበደቡ ብትዋረዱ ብትገደሉ የሕግ ከላላ ኣንሰጥም ማለት ነበር፡፡ ያለምንም እንከን ህዝቡ በሰጣቸው ሞራል ስራቸውን በሚገባ ፈፅመው በደስታ ወደ ዓዲግራት ተመለሱ። ይህ የሆነው ዕለት ሓሙስ ጥር 15 ቀን 2006 ዓ/ም ነበር፡፡ በዓዲግራት ኣቶ ኣስገደ ገ/ስላሴና ኣቶ ኣብርሃ ደስታ እንዲሁም መም/ፍፁም ግሩምና መመ/ገዛኢ ንጉሰ ኢሉ፡፡ ሓሙስ ጥር 15 ቀን 2006 ዓ/ም የስብሰባ ጥሪ የሚገልፀው ፅሑፍ በዓዲግራት ማደል ማደል ተጀምረዋል፡፡ ዕለተ ዓርብ ጥር 16 ቀን 2006 ዓ/ም የዓዲግራት ከተማ ሰፊ በመሆኑ ኣቶ ስልጣኑ ሕሸ፣ ኣቶ ሃይለኪሮስ፣ መም/ገዛኢ ንጉሰ፣ መመ/ፍፁም ግሩም በቀበሌ 01 ሲንቀሳቀሱ ህዝቡ ምግብና ውሃ እየሰጠ የስብሰባው ጥሪ እየተቀበለ በክብር እንዳስተናገዳቸው ይመሰክራሉ።

ይህንኑ እውነት እየተከታተሉ ይታዘቡ የነበሩ የጥፋት መልእክተኞች የዓረና መመራርና ኣባላት ለማወክ ተዘጋጅተው ኖረው የስብሰባው ጥሪ ለህዝቡ የሚያድሉ ወደ ሆስፒታል ኣከባቢ ሲደርሱ የቀበሌ ካድረ የሆኑ ሴቶች ወረቀቱን ተቀብለው መቅደድ ጀመሩ፡፡ ዕድሜኣቸው ከ12-16 ዓመት እንደሆኑ የሚገመቱ ህፃናትም መሰብሰብ ጀመሩ ሆ! እያሉ መረበሽ ጀመሩ፣ ሴቶቹ መብታቸው በማለት አደፋፈሩ። የማወክ መብት? ህፃናቱ የተላኩ እንጂ የራሳቸው ኣጀንዳ የሌላቸው መሆኑ በተግባር ለመፈተን የወዳደቁ የስኳርና የቡና መጠቃለያ የደብተርና የጋዜጣ ፅሑፎች ሲሰጣቸው የዓረና ፅሑፍ መስሎአቸው ሳያዩት ተቀብለው ወድያው ይቀዱታል ልክ የስብሰባው መጥሪያ ፅሑፍ ተቀብለው እንደቀደዱት፡፡ ለህፃናቱ መብታችሁ ነው እያሉ የሚያጅቡ ትላልቅ ወንዶችና ሴቶችም ነበሩበት ። ህፃናቱ ሁሉም ሊባል በሚችል ሲጋራ ያጤሳሉ ፣ ስትቀርባቸው መጠጥ መውሰዳቸው የሚሳውቅባቸው በእጅጉ ጠጅ ይሸቱ ነበር። የአከባቢው ሰዎች በሰጡት መረጃ መሰረት የተለያየ ሱስ ተጠቃሚዎች ለመሆናቸው በከተማው ፖሊስ የሚታወቁ ናቸው።በዚህ የውንብድና ተግባር በዓረና ከፍተኛ ወጣት አመራሮችና አባሎች የአካልና የሞራል ጉዳት ተፈፅሞአል ፣ የቀበሌ ሴቶች በፌስታል አፈር እያቀበሉ ህፃናቱ በአዓረና አባላት በላያቸው ላይ አፈር በማፍሰስና እክታ በመትፋት አሳፋሪ ወንጀል ሲፈፀም በዓዲግራት ከተማ የሚገኙት የከተማው አስተዳደርና ፖሊስ የዞኑ አስተዳደርና ፖሊስ መብታቸው ነው እያሉ ያሳዩት የወንጀል መተባበር አሳፈፋሪ ተግባርና መንግስታዊ ውንብድና የሚያሰኝ ነው።

በዛው ጨዋ ህዝብ ፊት እነደዚህ ያለ የውንብድና ተግባር ተፈፀመ፡፡ ከላይ ለመግለፅ እንደተሞከረው ተግባሩ የተቀነባበረው በዞኑ በከተማው መስተዳድር ስለመሆኑ ኣስተዳዳሪዎች፣ ፖሊስ ያሳዩት ተግባራቸው ይመሰክርላቸዋል፡፡

በነዚህ ጥቂት ቀናት የዞኑ መስተዳድር የፀጥታ ኣደጋነቱን በተግባር ሲያስመሰክር ህዝቡ ደግሞ የሕግ ኣስከባሪነት ሚናው መወጣቱን በገሃዱ ዓለም ቁጭ ብሎ ታይቶኣል፡፡ መስተዳደሩ በራሳችሁ ሃላፊነት የህግ ከለላ ኣንሰጣችሁም ሲል በዓረና ኣመራሮችና ኣባላቶች ሊያወርዱት የከጅሉት ወንጀል ጠቋሚ ነበር። የህዝብ ስብሰባው እንዳይካሄድ የተፈጠረው ውንብድና የመስተዳድሩ እጅ እንዳለበት የሚያሳየው -
የዞኑና የከተማው መስተዳደርና ፖሊሲ በኣባሎቻችን የተፈፀመውን በዓይናቸው ያዩት ወንጀል ማጠራትና ማስቆም ሲገባቸው ፍርደ ገምድል እንዲሉ በሞባይል ስልክና፣በካሜራ ቀርፃችሁናል ህፃናቱም ቀርፃችሁኣል ትፈተሻላችሁ ብለው የሁሉም አባሎቻችን ሞቫይልና ካሜራ ያለ ፍርድ ቤት ትእዛዝ መቦርበራቸው፣
በተደራጀና በህፃናት ከለላ የተደበቀ የወንብድና ተግባር ሲፈፀም መስተዳደሩና ፖሊሱ እያዩ በጠራራ ፀሃይ በኣባላቶቻችን ላይ ኣሰቃቂ ግፍ እነዲፈፅሙ ሙሉ ፍቃድ ማሳየታቸው የሚያስቆጥራቸው በመሆኑ ፣
በሕግ የተቋቋመ ፓርቲ የቆመለትን ራኢና ፖሊሲ ለህዝቡ ለማስተዋወቅና በክልሉ ያንሰራፋው ብልሹ ኣስተዳደር የሚገራበት መንገድ ከህዝቡ ለመምከር ያደረግነው ጥሪ እንዳይሳካ ለማወክ የተላኩ ህፃናት መብታቸው ነው እያሉ የሕገ-ወጥ ተግባር ከለላ መስጠታቸውና ለባሰ ጥፋት እንዲዘጋጁ ማበረታታቸው የወንጀሉ ተሳታፊ የሚያደርጋቸው መሆኑን
የከተማ ፖሊስ የኣረና ኣባላት ባረፉበት ሆቴል ማታ አልጋ በያዙበት ሆቴል ከምሽቱ 4፣00 ሰዓት ተገኝቶ እሁድ ለሚካሄደው ስብሰባ የእግር ኳስ፣ የብስከሌታ ውድድር ስላለ በቂ የፖሊስ ሃይል የለንም በማለቱ ስብሰባው እንዳይካሄድ በማደናቀፍ ምክንያት መሆኑን
በተደራጀ ወንብድና የኣካል ጉዳት የደረሰባቸው የኣረና ኣባላት በከተማው ጤና ጣብያ ተመርምረው የራጀ ምርመራ እንደሚያስፈልጋቸውና ሆስፒታል እንዲወሰዱ በሃኪም የተሰጠ ትእዛዝ በፖሊስ ኣለመፈፀሙን፣
የተፈፀመው የወንብድና ተግባር ለማድበስበስ በሃሰት ክስ፣ በኣቶ ኣስገደ ገ/ስላሴና መም/ፍፁም ግሩም የተቀነባበረው ወንጀላ እየተፈፀመ መሆኑን ነው ።

ህ.ወ.ሓ.ትና መስተዳድሩ ወደዚህ የፖለቲካ ቅሌት የሚገፋፋቸው ያለው በዓረና የኣማራጭ ፖሊሲ ልዕልና መርበትበቱንና ወደ እራቆቱ የወጣ በጠራራ ፀሃይ የኣማራጭ ፓርቲ ወጣት መሪዎችን በማፈን ማንበርከክ መምረጡንና የትግራይ ህዝብና ወጣት ልጆቹ የከፈሉት መስዋእትነት ጭራሽ ከምድረ ትግራይ ጠራርጎ ለማጥፋት መቑረጡን የሚያሳይ እኩይ ተግባር በመሆኑ የዓረና ትግራይ ፓርቲ የተቃውሞ ድምፁን ከፍ በማድረግ ለትግራይ ህዝብና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያሰማል፡፡ ዓረና ትግራይ የትግራይ ህዝብ የከፈለው የ17 ዓመታት የትግል ዘመን ብህ.ወ.ሓ.ት ተቀብሮ እንዳይቀር በማደስ የተነሳ ፓርቲ እንደመሆኑ በህ.ወ.ሓ.ት የሽብር ተግባር የማይታጠፍ መሆኑን በማረጋገጥ በህዝባችን ፊት የሚከፈለውን ሁሉ መስዋእትነት እየከፈልን ብፅናት የምንቀጥልበት መሆኑን ለመግለፅ ይወዳል፡፡

የዓዲግራት ከተማ ወጣቶች የተደረጁ ኣሸባሪ ወንጀለኞችን በመመከት የኣባለቶቻችን ህይወት ለመታደግ ያሳየው ድፍረት እንዲሁም የዕዳጋ ሓሙስ ከተማ ነዋሪዎችና የፋፂ ከተማ ነዋሪዎች ዓረና ለህዝቡ የቀረበው ጥሪ በማክበር ያሳያችሁት ኣክብሮትና ፍላጎት ኣክብሮታችን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ ዓረና ትግራይ ፓርቲ በዚሁ የወንብድና ተግባር ሳይንበረከክ ከትግራይ ምስራቃዊ ዞን ህዝብ በኣጠቃላይና በዓዲግራትና ኣከባቢዋ የህዝብ ስብሰባ በመጥራት ከህዝቡ መምከር በፅናት እንደንቀጥልበት በእርግጠኝነት ለማረጋገጥ እንወዳለን፡፡

ጥር 18 ቀን 2006 ዓ/ም
መቐለ

Monday 27 January 2014

የብኣዴን እና የኦሕዴድ ባለስልጣናት ቅርርብ ለሕወሓት አልተመቸውም:: "...አደጋ ውስጥ ነን::" የሕወሓት የደሕንነት መሪዎች የኦህዴድ ውስጥ ውስጡን መደራጀት ሕወሓትን አሳስቦታል::

ምንሊክ ሳልሳዊ 

በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ከፍተኛ የሆኑ የብኣዴን እና የኦሕዴድ ከፍተኛ ባለስልጣናት መቀራረብ እና አብሮ መዋል የሕወሓት ሰዎችን ማሳሰቡን እና የደህንነት ክትትል እያደረጉባቸው መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል:: ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከደመቀ መኮንን እና ከሙክታር ከድር ጀምሮ እስከ በታች የፌዴራል ባለስልጣኖች ላይ ከፍተኛ ስለላ እየተካሄደ መሆኑን ታውቋል::

ሃገሪቱ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሳለች ከፊታችን አደጋ ተደቅኗል::የሚሉ የተቆጡ ድምጾች በስፋት በእሕኣዴግ አባላት እየተሰሙ ያለበት አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው ሕወሓት በግል እና በጋራ ባለስልጣናቱ ላይ ከፍተኛ ማስፈራራት እና ዛቻ እያደረገባቸው መሆኑን የተናገሩት ምንጮቹ ኢሓዴግን ለመናድ ብትሞክሩ ሃገሪቷ ትበታተናለች ;እንደ ሱማሊያ መንግስት አልባ ሆና ትበጠበጣለች እያሉ ከማስፈራራትም አልፎ በግል የተነከራችሁበት ሙስና አደባባይ እናወጣዋለን:: እኛን ማንም ሊተይቀን አይችልም ቁልፉ እኛ ጋር ነው የሚሉ በኣደገኛ መርዞች የተሞሉ ማስፈራሪያዎች በመሰንዘር ላይ ናቸው ሲሉ ምንጮቹ ተናግረዋል::

የብኣዴን እና የኦሕዴድ ባለስልጣናት የየቀን ሪፖርት እና ግንኙነት በተመለከተ ማን ከማን ጋር እንደዋለ ማን እነማን ቤት እንደሄደ በመከታተል እየቀረበ ሲሆን የሃገሪቱን የደህንነት ቢሮ በጋራ የሚመሩት አቶ ጸጋዬ አቶ ጌታቸው እና ዶ/ር ደብረጺሆን በየቀቱ ለትግሪኛ ተናጋሪ ደህንነቶች በአጫጭር ስብሰባዎች መመሪያ እያወረዱ ከመሆኦኑም በላይ አደጋ ውስጥ መሆናቸውን እየደጋገሙ እንደሚናገሩ ምንጮቹ አክለዋል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከዚህ ቀደም በእሕዴድ ወጣቶች የተጀመረው እና የሌንጮ ለታ ወደ አገር ቤት የሚለውን ዜማ ተከትሎ የለውጥ ጥያቄ እያንሰራራ መሆኑ ታውቋል:: በዚህም ምክንያት የኢሕኣዴግ አጋር ድርጅት የሆነው ኦሕዴድ ወጣት አባላት እና ለውጥ ፈላጊዎች ራሳቸውን ውስጥ ውስጡን እያደራጁ ነው በሚል ሕወሓት የድርጅቱን መዋቅር ሊበርዘው መሆኑ ተሰምቷል:: በተለያዩ ፖለቲከኞች ዘንድ ኦሕዴዶች ድምጻቸውን አጥፍተዋል እየተባለ ባለበት በዚህ ወቅት ሕወሓት አሳሳቢ ጉዳይ ላይ ነው ሲል ይነጋገርበት ጀምሯል::

በወጣቶቹ የኦሕዴድ አባላት መሃከል በተፈጠሩ መግባባቶች እስከመቼ ድረስ የፖለቲካ አሽከር ሆነን እንቀጥላለን የሚሉ የድርጅቱ ካድሬዎች በዙሪያቸው እየተቧደኑ ሲሆን ይህ ያሰጋው ሕወሓት የእነዚህ ሰዎች ዝምታ ይህን ሰሞን በአመራሮቹ ደረጃ በቢሮ ስብሰባ እየተነጋገረበት ይገኛል::

ጥርሳቸውን ነክሰው አድፍጠው ያሉት የኦሕዴድ አባላት በስልጣን ክፍፍሉ እና ራሳችንን መምራት ያለብን ራሳችን ነን በሚል እንዲሁም በተያያዥ የፖለቲካ ጉዳዮች በተጨማሪም በኦሮሚያ ክልል ያሉት የህዝብ ሃብቶች ላይ የሕወሓት ባለስልጣናት የሚሰጡት ውሳኔ እንደፖለቲካ ባርነት ነው የሚሉ ሮሮዎች በመደመጥ ላይ ሲሆኑ ነጻነታችንን መረጋገጥ አለብን የሚሉ ቢሊሶማ2 የተሰኙ ወጣት ባለስልጣናት ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ ከተውታል::ምንሊክ ሳልሳዊ

ONLF Condemns Nairobi Abduction of Two Senior Officers by Ethiopian Intelligence Agents

ONLF Press Release
Sulub Abdi abducted in NairobiSulub Abdi abducted in Nairobi
Somalilandsun - The Ethiopian security abducted Mr Sulub Ahmed and Ali Hussein, two senior ONLF leaders from Nairobi yesterday afternoon. The leaders, who were members of the ONLF negotiation team, were in Nairobi for a proposed third round of talks.
This is not the first time that the Ethiopian government has acted in an unethical and uncivilised manner by killing or abducting ONLF delegates engaged in peace talks. In 1998, the Ethiopian Army killed three members of an ONLF delegation team and abducted two members, who were coming back to ONLF base after participating in bilateral negotiations with the Ethiopian government inside the Ogaden. Two years ago, the Ethiopia government assassins killed another senior leader in Nairobi too.
This heinous act constitutes a breach of confidence in dealing with Ethiopia and will gravely hamper any further talks with Ethiopia. This cowardly act, will further invigorate the quest of the Somalis in Ogaden for freedom.
It is the practice the current Ethiopia regime to capture or abduct ONLF members and force them under duress to claim that they are ONLF members who had formed a new faction and has accepted peace and surrendered
We call upon the Kenyan government, which took the responsibility to be a neutral venue, and as a facilitator to investigate fully this travesty and request the Ethiopian government to return the abductees.
ONLF calls the international community to condemn Ethiopia and understand that the regime is anti-peace.

Friday 24 January 2014

የሁለት አመት ህዝባዊ ንቅናቄ ዛሬም ተደገመ! (ድምፃችን ይሰማ)

የትግላችን ማረፊያ ድል ብቻ መሆኑን ዛሬም አውጀናል!


የዛሬዋ እለት ለህዝበ ሙስሊሙ ካለፉት ስድስት ወራት ለየት ያለ ክስተትን አስተናግዳ ያለፈች ጁሙዓ ነች፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ ላለፉት ስድስት ወራት ለመንግስት በጥሞና የማሰቢያ ጊዜ ለመስጠት ከማንኛውም የአደባባይ የተቃውሞ ስነ ስርአቶች ተቆጥቦ ቆይቶ ነበር፡፡ መንግስት የእፎይታ ጊዜውን በአግባቡ ሊጠቀም ያለመፍቀዱ እንዳለ ሆኖ የሰላማዊ ትግሉን ሁለተኛ አመት ለማሰብም ‹‹730 ቀናት ለሃይማኖት ነጻነት›› በሚል ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ ዘመቻ ታውጇል፡፡ የዛሬዋ ጁሙአ የዘመቻው ኦፊሴላዊ መክፈቻ ነበረች – ደማቅ መክፈቻ! ህዝበ ሙስሊሙ በበርካታ የአገሪቱ ከተሞች በሚገኙና የትግሉን መንፈስ አማክለው በቆዩ መስጊዶች በከፍተኛ ቁጥር ተሰባስቦ በመስገድ ለትግሉ ቀጣይ እርከን ሙሉ ዝግጁነቱን በከፍተኛ ወኔ አሳይቷል፡፡
በአዲስ አበባ አንዋር መስጂድ ከጁምአው አስቀድሞ መምጣት የጀመረው ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ አንዋርና አካባቢውን ለመሙላት ቅጽበትም አልወሰደበትም፡፡ የህዝቡ ቁጥር እንዲታይ ያልፈለጉት ፖሊሶች እንደተለመደው መኪኖችን ለህዝቡ በማስቆምና መስገጃውን እንዲያነጥፍ በመፍቀድ ፋንታ ለመከልከልና ግርግር ለመፍጠር የሞከሩ ሲሆን ለማረጋጋት የሞከሩ ወጣቶችንም ለማሰር ሙከራ አድርገው ሳይሳካላቸው ቀርቷል፡፡ መዲና ህንጻ ላይ የኢቲቪ ካሜራዎች ተደግነው ህዝቡን ሲቀርጹ የነበሩ ሲሆን ህዝቡም በመሸማቀቅ ፋንታ እነሱኑ መልሶ ሲቀርጻቸው ማየት በእርግጥም አስገራሚ ነበር፡፡ ከጁምአው ስግደት በኋላ ደማቅ የዱአ ስነስርአት ተደርጎ ሰው የተበተነ ሲሆን በመምጫና መመለሻ ሰአቶችም በድልና ነስር ኒያ የአንድ ብር ሰደቃ ለችግረኞች ተሰጥቷል፡፡ በሺዎች ፊት ላይ ይታይ የነበረው ደስታና የማይሸነፍ ወኔ በእጅጉ ማራኪ እንደነበር ሁላችንም እዚያው የመሰከርነው የትግላችን ደማቅ ትእይንት ነበር፡፡
የክልል ከተሞችም እንዲሁ በከፍተኛ ድምቀት መርሀ ግብሩን አከናውነዋል፡፡ ለአዲስ አበባ አጎራባች በሆነችው አዳማ ከተማ አቡበክር መስጂድ በህዝበ ሙስሊሙ አሸብርቆ መዋሉና የዱዓና የሰደቃ ፕሮግራሙም ባማረ ሁኔታ መጠናቀቁን ማወቅ ተችሏል፡፡ በተመሳሳይ በጂማ ፈትህ መስጂድ ደማቅ ሆነ የዱአና የሰደቃ ፕሮግራም የተካሄደ ሲሆን በቀደሙ ደማቅ ተቃውሞዎቻቸው የሚታወቁት ሻሸመኔና መቱ ከተማም በደማቅ ሁኔታ ለትግሉ ያላቸውን አጋርነት ገልጸው አልፈዋል፡፡
ካሁን ቀደም የመንግስት የሀይል እርምጃ ሰለባ የነበረችው አጋሮ ከተማም በአል አዝሀር መስጂድ ላይ በከፍተኛ ቁጥር ለጁምአ በተገኘው ህዝበ ሙስሊም ዱአና ሰደቃ ደምቃ ውላለች፡፡ በዚያው በኦሮሚያ ክልል በደሌ ከተማ የሚገኘው መስጂደ ራህማ ላይም ተመሳሳይ ደማቅ ፕሮግራም ተካሂዶ የዋለ መሆኑ ተዘግቧል፡፡
ካሁን ቀደም በራሷና በሀምሳ ያክል በዙሪያዋ በሚገኙ ወረዳዎች ላይ አስገራሚ ተቃውሞ ያካሄደችው ዶዶላ ከተማም በፈትህ መስጂድ ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን ህዝበ ሙስሊም አስተናግዳ ውላለች፡፡ በዶዶላ በኢማሙ አማካኝነት ከሰላት በፊት አላህ ትግሉን ለድል እንዲያበቃው ዱአ የተደረገ ሲሆን ሰደቃውም በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል፡፡ ዶዶላ በጥልቅ ዱአ ውስጥ ሆና ሳለች በርቀት በደምቢ ከተማ የሚገኙ ሙስሊም ነዋሪዎች ደግሞ በታላቁ መስጂዳቸው ተሰባስበው ተመሳሳይ የአጋርነት ፕሮግራም እያካሄዱ ነበር፡፡
በግዙፍ የቀደሙ ተቃውሞዎቿ የምትታወቀው ወልቂጤም የዛሬው የጁምአ ውሎ ተጋሪ ነበረች፡፡ በረቢእ መስጂድ የተሰባሰቡ ምእመኖቿ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትግል አጋር መሆናቸውን አስመስክረውባት ውለዋል፡፡
ገና በማለዳው ከ 50 ሺህ በላይ በራሪ ወረቀቶች ተበትነው ያደሩባት የደሴ ከተማም በዳውዶ መስጂድ በተሰባሰቡ ሙስሊም ነዋሪዎቿ አማካኝነት እስከ ድል ጫፍ የሚያብበውን የትግል ስሜት ያሳየች ሲሆን የዱአና የሰደቃ ፕሮግራሙም በድምቀት ተካሂዶባታል፡፡ በተመሳሳይ ሰአት በኸሚሴ ኹለፋኡ ራሺዲንም ደማቅ የዱአና የሰደቃ ፕሮግራም ተካሂዶ መዋሉ ታውቋል፡፡
በምስራቅ ኢትዮጵያ በሐረር ከተማ 4ኛ ኢማን መስጂድ፣ በአፋር ሎጊያ ከተማና በድሬዳዋ ከተማ አሸዋ ቢላል መስጂድ የተሰባሰቡ ሙስሊም ነዋሪዎችም ደማቅ የዱአና የሰደቃ ስነስርአት አድርገው ተመልሰዋል፡፡ በተመሳሳይ በሐዋሳ ከተማ ዐረብ መስጂድና ቤሎችም በርካታ ከተሞች ህዝበ ሙስሊሙ ዳግም ድምጹ አንድ መሆኑንና ወኔውም አንዳች እንዳልጎደለ ያለማወላወል አረጋግጦ አልፏል፡፡ /በተለያዩ የውጭ አገራት ከተሞች የተደረጉ ፕሮግራሞችን ለብቻ የምናወሳቸው ይሆናል!/
የዛሬው ስኬታማ መርሀ ግብር በተለያዩ ከተሞችና መስጂዶች የተደረገ ቢሆንም ያስተላለፈው መልእክት ግን አንድ እና አንድ ነው፡፡ ያም ህዝበ ሙስሊሙ ከድል ደጃፍ ሳይደርስ በምንም መልኩ ሰላማዊ ትግሉን እንደማያቆም ነው፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ ዲኑ ላይ የሚሰነዘረውን ጥቃት እየተመለከተ እንዴትስ እጁን አጣጥፎ ሊቀመጥ ይችላል? ህዝብ የአገር ዋነኛ መሰረት መሆኑ እየታወቀ የሚፈጸምበትን በደል ተቋቁሞ የጥሞና ጊዜ መስጠቱስ እንደምን በስህተት ሊተረጎም ተገቢ ሆነ? አዎን! የዛሬው ከረጅም የጥሞና ጊዜ በኋላ የተደረገው መርሀ ግብር መልሶ ያለፈው እኒህን ጥያቄዎች ነው፡፡ ህዝብ እንደማይሸነፍና መንግስትም ለህዝብ ፍላጎት በትክክል ተገዥ እስኪሆን ድረስ ሰላማዊ ትግሉ እንደማይገታ፣ ብሎም ለድል መብቃቱ እንደማይቀር ልቦና ላለው ሁሉ ያስገነዝባል፡፡
በቀጣዮቹ ሁለት ሳምንታት የሚኖሩት መርሃ ግብሮች በሙሉ የሁለት አመት ትግላችንን በመንፈስም በተግባርም ድጋሚ እንድናልፍባቸው የታሰቡ ናቸው፡፡ ይህንን ደግሞ ዛሬ ‹‹ሀ›› ብለን ስንጀምር በህዝብ ውስጥ የተቀጣጠለ ቁጣ መብረጃው ድል ብቻ እንደሆነ ባመለካተ ህዝባዊ ወኔ ነው፡፡ ቀጣዩ የትግላችን ጉዞ እንቀደሙት ሁሉ ህዝባዊ መሰረቱን ይዞ ይቀጥላል፡፡ አሁን የምንገኝበት የእፎይታ ጊዜ በትግላችን ውስጥ እንዳለፉት እና እንደሚመጡት ምዕራፎች አንዱ ወሳኝ እርከን ነው፡፡ የእፎይታ ጊዜውን በዓላማው አምኖበት እና ለኢስላማዊ አንድነት ቅድሚያ ሰጥቶ፣ የመንግስት ግብታዊ አካሄድ እና ለከት የለሽ የጭቆና መብዛት የፈጠሩበትን ቁጣ ዋጥ አድርጎ ለመርሁ ተገዥ የሆነው መላው ሙስሊም ማህበረሰብ ‹‹የጀግኖች ጀግና›› ቢባል ያንሰው ይሆን?
በትግል ላይ መስዋእት መሆን እና በትእግስት መፅናት ሁሉም የአንድ ትግል ማዕዘናት ናቸው፡፡ ይህን መስፈርት ደግሞ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በተግባር እያሳየን እንገኛለን፡፡ ላለፉት ሁለት አመታት በጀግንነት እና በመሰዋእትነት ፀንተናል፡፡ ዛሬ ደግሞ የቀደመውን ጀግንነታችንን እንደያዝን በትግል ቃልኪዳናችን ፀንተናል፤ ወደፊትም እስከድል ደጃፎች ድረስ ጸንተን እንቀጥላለን፤ ድልም ከአላህ እንጂ ከሌላ አይደለምና!
‹‹ሁለት ጁሙአዎችን በሁለት አመት የትግል ወኔ!››
ድምጻችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

Ethiopia Has a Terrible Human Rights Record - Why Is the West Still Turning a Blind Eye?




Some disappeared, others were given lengthy prison sentences. One thing all thirty men arrested in 2012 in Ethiopia had in common was that they had criticised the state and the policies of the former Premier, Meles Zenawi.
And yet last week Japan's Prime Minister Shinzo Abe and a group of Japanese business leaders met with the current Prime Minister of Ethiopia, Hailemariam Desalegn to discuss further support for Ethiopia at "government and private sector level."
The former Meles Zenawi was a staunch supporter of American counter-terrorism policy while at the same time overseeing a country with a violent human rights record. In the eyes of the USA, Ethiopia is strategically situated. Located in the Horn of Africa, next to Somalia, northern Kenya and Sudan, it acts as a buffer zone between the growing Islamic extremism of Somalia and the West. As a result, the human rights violations of Zenawi were ignored.
As one of the first signatories of the UN in 1948, Ethiopia is a Western ally: 11 per cent of its entire GDP comes from Foreign Aid. The US is one of Ethiopia's largest donors: it is estimated that it gave $3.3bn in 2008 alone. The two countries benefited from their close relation: there have been rumours that America hosted "black sites" in Ethiopia; bases where the CIA interrogated undeclared prisoners during the "War on Terror."
But Meles Zenawi died in 2012. The opportunity for a more liberal government was not seized: Zenawi was replaced by Hailemariam Desalegn, described by critics as an "identikit Zenawi" running the country on "auto-pilot". Desalegn is following the same political manifesto as Meles - he hasn't changed one member of parliament.
The arena for debate and discussion is narrowing. Critics argue that Ethiopia is fast becoming a "one party democracy" where there are many parties but the same one wins again and again. Meles spoke to foreign press in 2005 and defended his 97 per cent electoral victory: "In democracies the party with the best track record remains in power." The years since 2005 have seen growing unrest among the Ethiopian population and serious repression against critics of the regime. Human Rights Watch reported that Ethiopia "continues to severely restrict freedom of movement and expression". It adds that "30 journalists and opposition members have been convicted under...vague anti-terrorism laws".
The day before World Press Freedom Day on May 2 2013, the Ethiopian government ruled to uphold the imprisonment of one of its most well-known prisoners of conscience, Eskinder Nega. He was jailed for being a journalist who criticised the government, and yet, by standing up for his beliefs and expressing his basic human right for Freedom of Speech, he earned an 18 year jail sentence.
Prime Minister Hailemariam Desalegn has denied his release. America and Britain have done little to challenge their ally, so worried are they about creating another enemy in the Horn of Africa. Britain and America have consistently failed to challenge their ally about its abhorrent Human Rights record. Ethiopia flaunts its apathy towards the UN convention of Human Rights, denying opposition members a right to fair trial and repressing people for trying to voice their opinions peacefully.
Ethiopian political repression is worsening. There have been repeated crackdowns against the country's Muslim minority. This has included arbitrary arrests as Muslims make peaceful demands for freedom of worship. Again, critics have voiced concern with the regime. Mehari Taddele Maru, head of the African Conflict Prevention Program at the Institute for Security Studies expressed concern that "if legitimate grievances are not met then there is a risk that extremist violent elements will exploit those grievances to further their own."
The world is waking up to Ethiopia's increasingly poor human rights track record and yet the United States hasn't stopped aid flowing to Ethiopia or threatened the country with sanctions. Japan still tries to conduct business with Ethiopia when instead they should be holding Ethiopia to account.
As a founding member of the UN and an "ally" of the West, Ethiopia must be held accountable for her crimes. If the West does not challenge Ethiopia and demand that it releases its prisoners who have been locked up without fair trial, then notions of democracy and human rights accountability as embedded in the Human Rights Charter look ever more vulnerable-Human Rights globally will be laughed out of the door.
By Eleanor  Ross, huffingtonpost

የእነ አንዱዓለም አራጌ ቀጠሮ ተምታታ


ፍርድ ቤቱ ለጥር 30 ቀጥሯቸዋል ሬጅስትራር በበኩሉ ጥር 24 ቀን 2006ዓ.ም መቅረብ አለባቸው ይላል

በነአቶ አንዱአለም አሬጌ ስም ያለው የክስ መዝገብን በሚመለከት በፌዴራል ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከተከሳሽ ጠበቆችና ከቤተሰቦች ጋር ብንቀርብም ፍርድ ቤቱ ቀጠሮው ትላንት ስለ ማለፉ ተናግሯል፡፡ የተከሳሽ ጠበቆች በበኩላቸው አጀንዳቸው ላይ የያዙት ዛሬ ጥር 16 ቀን 2006 ዓ.ም መሆኑን ቢገልፁም በዳኛ አዳነ ንጉሴ፣ ዓሊ መሐመድ፣ አልመው ወሌ እና ሙስጠፋ አህመድ የተሰየመው ችሎት በበኩሉ የቀጠሮው ቀን ትላንት ማለፉን ተናግረዋል፡፡

ችሎቱ ቀጠሮው ዛሬ እንኳ ቢኆን መዝገቡ እጅግ ሰፊ በመሆኑ ውሳኔው እየተጻፈ በመሆኑ ምክንያት ለጥር 30 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲቀርቡ አዟል፡፡

በሌላ በኩል የፍርድ ቤቱ ሬጂስትራር ቀጠሮው ዛሬ መሆኑን አምኖ ነገር ግን ለከሳሽ አቃቤ ህግ መጥርያ ያልተላከ በመሆኑ ለአቃቤ ህግ ድጋሚ ትዕዛዝ ለማፃፍ ጥር 21 ቀን 2006 ዓ.ም ችሎት እንድቀርቡ አዟል፡፡ ከሬጂስትራሩና ከፍርድቤቱ ቀጠሮ የትኛው ትክክል እንደሆነም ለማወቅ አልተቻለም፡፡

በሌላ በኩል አንድነት ፓርቲ ለክትትል ያመቸው ዘንድ የእስክንድር ነጋን የሰበር ሰሚ ይግባኝ ለማጣራት ሙከራ ቢያደርግም በእስክንድር ስም የቀረበ አንዳችም ይግባኝ እንደሌለ ሬጂስትራሩ አረጋግጧል፡፡ ባለቤቱን ጨምሮ ሎሎች አስተያየት ሰጪዎች ግን እስክንድር ያለ ጠበቃ ለመከራከር ይግባኝ ማለቱን አምነዋል፡፡

መንግስት ለአቶ አንዱአለም አያሌው ያቆማቸው ጠበቃና በሽብር ድርጊት ተጠርጥረዋል የተባሉትን ሰዎች ክስ የመሰረተው የመንግስት ዓቃቤ ህግ ከሀገር መሰደዳቸው ይታወሳል፡፡

Thursday 23 January 2014

Oromo Prisoners of Conscience, Bekele Gerba and Olbana Lelisa




On August 27, 2011, Oromo political leaders, Obbo Bekele Gerba and Obbo Olbana Lelisa, were thrown into prison by the TPLF regime, which has militarily occupied Oromiyaa since 1991. They were put in prison after meeting with an Amnesty International delegation, which was also expelled from the Empire afterwards.
The Amnesty International delegation was in the country to collect information for its report, which was later published in Dec. 2011: “Dismantling Dissent – Intensified Crackdown in Ethiopia

A report from amnesty international at that time...

Two Ethiopian opposition leaders have been arrested after meeting an Amnesty International delegation, which was afterwards expelled from the country, the organization said today. 

One of the men was accused of terror-related offences, while the charges against the other man are not known. 

“We are extremely concerned that the arrests of the two men occurred within days of talking with our delegates. Although the Ethiopian government has denied it, we are worried that their arrests are not a coincidence, but because they spoke to Amnesty International,” said Michelle Kagari, deputy programme director for Africa. 

Bekele Gerba, deputy Chairman of the opposition Oromo Federalist Democratic Movement (OFDM) and Olbana Lelisa of the Oromo People’s Congress party (OPC) were both arrested on 27 August. 

On the same day that the two men were arrested, the Amnesty International delegation was called to a government meeting, where they were ordered to leave the country. 

Bekele Gerba, an English teacher at Addis Ababa University, was arrested on allegations of belonging to the Oromo Liberation Front (OLF), a charge the government often uses to silence members of the Oromo political opposition. It has not been made public what Olbana Lelisa is accused of, but it is anticipated that the charges will be the same. 

Amnesty International delegates had met with Olbana Lelisa the day before his arrest, to exchange information. They also met with Bekele Gerba, four days before his arrest. Amnesty International delegates were photographed by secret service agents leaving his office after the meeting. 

In that meeting Bekele Gerba had explained to Amnesty International the irony of Oromo politicians being accused of belonging to the OLF. ‘The OLF don’t like us,’ he said. ‘They say we are legitimising the rule of the EPRDF [the ruling party], they say we are their puppets and our struggle does not bear any fruit.’

Both men were long-standing opposition politicians, who had campaigned openly in the 2010 national elections. “The arrests are indicative of the constant harassment of opposition politicians, and severe stifling of freedom of expression in the country”, said Michelle Kagari.   

The two men are now being held in the federal police investigation centre, ‘Maikelawi’, from where Amnesty International has received countless reports of the use of torture. Furthermore, detainees at Maikelawi are, as a general rule, denied access to lawyers or family members, for periods of up to one or two months. 

The Amnesty International delegates were under constant surveillance during the twelve days they spent in the country before being expelled. “We are now extremely concerned for the safety of everyone our delegates met with while they were in the country,” said Michelle Kagari.     

ዓረና መድረክ የእሁድ ስብሰባ

አብርሃ ደስታ

ዓረና መድረክ ከዓጋመ (ዓዲግራት) ህዝብ ጋር በፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ለመወያየት ለእሁድ ጥር 18, 2006 ዓም በዓዲግራት ህዝባዊ አዳራሽ (ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ) ቀጠሮ መያዙ ይታወቃል። ዓረና ፓርቲ ለተሰብሳቢው ህዝብ አማራጭ ፖሊሲው ያስተዋውቃል፣ ፖለቲካዊ ትምህርት ይሰጣል፣ ያደራጃል፣ መረጃ ይለዋወጣል። የዓረና ዋነኛ ዓላማ ህዝብ ከጭቆናና ባርነት ለማላቀቅ ማስተማር ነው።

ህዝብ ካሁኖቹ ጨቋኞች እንዲሁም ለወደፊቱ ሊመጡ ከሚችሉ ጨቋኞች ነፃ እንዲወጣ ለማድረግ ፖለቲካ (ስለ መብትና ነፃነት) እናስተምራለን። ምክንያቱም አንድ ህዝብ (ወይም ብዙ ህዝቦች) ከጭቆና ለማላቀቅ ህዝብ መሳርያ ማስታጠቅ አለብን። የፀረ ጭቆና ሚሳኤል ፖለቲካዊ ትምህርት ነው። የፖለቲካ ትምህርት በመስጠት የህዝብ የፖለቲካ ንቃተህሊናው ከፍ እንዲል ማድረግ ይቻላል። ህዝብ የፖለቲካ ንቃተህሊናው ካዳበረ ለማንም ጨቋኝ ስርዓት አሜን ብሎ አይገዛም። መብቱ ማስከበር ይችላል። ነፃነቱን አሳልፎ አይሰጥም። ስለዚህ ፖለቲካዊ ትምህርት ፀረ ጭቆና ሚሳኤል ነው። ህዝብ ራሱ ከጨቋኞች ነፃ ለማውጣትና ለመከላከል ከፈለገ (አንድ) ፖለቲካ ማወቅ አለበት፣ (ሁለት) መደራጀት አለበት። ወደ ዓዲግራትና ሌሎች አከባቢዎች የምንቀሳቀሰውም ይህንን ፀረ ጭቆና ሚሳኤል ለማስታጠቅና ለማደራጀት ነው።

ህወሓቶች ግን ይህን ዓላማ እንዳይሳካ ጥረት ማድረጋቸው አይቀርም። ምክንያቱም ህዝብ ፀረ ጭቆና ሚሳኤል ከታጠቀ ለህወሓቶች አሜን ብሎ የሚገዛ አይሆንም። መብቱ ይጠይቃል፤ ነፃነቱ ይፈልጋል። ስለዚህ ህወሓቶች ህዝብ ይህንን ፀረ ጭቆና ሚሳኤል እንዲታጠቅ አይፈልጉም። በዚህ መሰረት ህዝብ ዓረና በጠራው የህዝብ ስብሰባ እንዳይሳተፍ የተለያዩ ዕንቅፋቶች መፍጠራቸው አይቀርም። ህዝቡ በስብሰባ እንዳይሳተፍ ማስፈራራታቸው አይቀርም። ምክንያቱም ህወሓቶች የህዝብን ማወቅ ያስፈራቸዋል። ምክንያቱም የህዝብ ማወቅ ለስልጣናቸው ስጋት ነው። ህዝብ አሜን ብሎ የሚገዛ እስካላወቀ ድረስ ብቻ ነው። ስለዚህ የህወሓቶች ስትራተጂ ህዝብ ወደ ስብሰባው እንዳይገባና እንዳያውቅ መከልከል ነው የሚሆነው።

የህወሓቶች ዕንቅፋት ሳይበግረን እንገባበታለን። ምክንያቱም የህዝብን የማሳወቅ ዓላማ አንግበናል። የኛ ዓላማ ህዝብ ስለ ፖለቲካዊ መብቱ ግንዛቤ ኖረት የራሱ ዕድል በራሱ እንዲወስን ማስቻል ነው። ለዚሁ ዓላማ ሟቾች ነን። ህወሓቶችም ለስልጣናቸው ሟቾች ናቸው። የህወሓት ሃይማኖት ስልጣን ነው። ስለዚህ ህወሓት ለስልጣኑ መስዋእት ይከፍላል። ለስልጣኑ ይሞታል። እኛም ለዓላማችን እንሞታለን። ሁለታችን ለተለያየ ዓላማ እንሞታለን፤ እንፎካከራለን። በመጨረሻም ሁላችን ፖለቲከኞች ሞተን የመጨረሻ ድሉ የህዝብ ይሆናል። ህዝብ ያሸንፋል።

Wednesday 22 January 2014

አንድነት ፓርቲ ፓርላማውን ማብራሪያ ጠየቀ



አንድነት ለጠ/ሚ/ሩና ለአማራ ክልል ፕሬዚዴንት የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ጉዳይን አስመልክቶ የፃፈው የማብራሪያ ጥያቄ መልስ ባለማግኘቱ እነሆ ዛሬ ደግሞ ወደ ፓርላመው ዞሯል፡፡

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)
ቁጥር አንድነት /811/2ዐዐ6
ቀን 11/ዐ5/2ዐዐ6 ዓም

ለተከበሩ አቶ አባዱላ ገመዳ
ለኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ-ጉባኤ
አዲስ አበባ

ጉዳዩ፡- በኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር አካባቢ ያለውን የወሰን ጉዳይ ለሕዝብ ግልጽ ስለማድረግ
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) በአገራችን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲሰፍን በሠላማዊ መንገድ ከሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች አንዱ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሠረት በአገራችን የሚካሄዱ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮችን በቅርብ ይከታተላል፡፡ በዚሁ ክትትል መሠረት በአሁኑ ወቅት ከተከሰቱ አብይ አገራዊ ጉዳዮች አንዱ የኢትዮጵያ ሱዳን ድምበር ይገኝበታል፡፡ ጉዳዩ ለሕዝቡ ግልጽ ያልሆነ አብይ የአገር ጉዳይ በመሆኑና ኃላፊነት ካለበት መንግሥት በማይጠበቅ መልኩ ሂደቱ ከሕዝብ ተሰውሮ በአገር ውስጥ ካለ የግልና የውጭ ሚዲያዎች እንድንሰማ ተገደናል፡፡

ስለሆነም

1. የወሰን ማካለል ጉዳይ በዋነኝነት ታሪካዊ፣ ሕጋዊና የመልካምድር አቀማመጥ ላይ ጥልቅ ጥናት ተደርጎ፤ ሠፊ ሕዝባዊ ውይይት ተካሂዶ የአካባቢውና የኢትዮጵያ ሕዝብ ሂደቱና ውጤቱን በግልጽ ማወቅ ይኖርበታል፡፡

2. ይህ ተግባር የግዛት ሉዓላዊነት ጉዳይ በመሆኑ ሕገ መንግሥታዊ መብትና ግዴታም ጭምር ስለሚሆን አሁን በተለያዩ የውጭ ሚዲያዎች ሱዳን ትሪቢዩንን ጨምሮ እንዲሁም ከአካባቢው ሕብረተሰብ በሚሰማው ሁኔታ መጓዙ አካባቢውን የግጭት ቀጠና ሊያደርገው ስለሚችል የጥንቃቄ ሂደት ያስፈልገዋል፡፡

3. ይህን እጅግና አብይ አገራዊ ጉዳይ ግልጽነት በጎደለው መልክ ምናልባትም ለጊዜያዊ የፖለቲካ ጥቅምም ከሆነ ወደፊት ሊያመጣ የሚችለውን ከባድ ችርግርና አካባቢያዊ ብሎም አገራዊ አለመረጋጋት ስለሚያመጣ ከወዲሁ አይነተኛ መፍትሔ ሊሰጠው እንደሚገባ ፓርቲያችን በጽኑ ያምናል፡፡

በመሆኑም የጉዳዩን አሳሳቢነት ለተከበሩ አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና ለክልሉ ፕሬዚደንት ለተከበሩ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ጥር 7 ቀን 2ዐዐ6 ዓም ደብዳቤ የፃፍን ቢሆንም እነሆ እስከ አሁን ግልጽና ሕገ-መንግሥታዊ መልስ አልተሰጠውም፡፡ ፓርቲያችን አሁንም ቢሆን ድንበሩን በተመለከተ እያንዳንዱ ሂደትና ውሳኔ አብይና የሉዓላዊነት ጉዳይ በመሆኑ የተወካዮች ም/ቤት በጥልቀት ተወያይቶ ለሕዝብ ግልጽ ማድረግ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታው ነው እንላለን፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለሚፈጠረው ማንኛውም ዓይነት የድንበር ችግር የተወካዮች ም/ቤት ከሁሉም በላይ ከፍተኛ ኃላፊነት ያለበት መሆኑን እያስገነዘብን፣ አሁንም ቢሆን በዚህ አብይ አገራዊ ጉዳይ ላይ በም/ቤቱ አባላት ውይይት ተካሂዶበት ለሕዝብ ይበልጥ ግልጽ እንዲደረግና ሕገ-መንግሥታዊ መፍትሔ እንዲያገኝ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
ከሠላምታ ጋር
ግዛቸው ሽፈራው (ኢ/ር)
የአንድነት ፓርቲ ፕሬዚደንት

እንዲታወቅ
- ለተከበሩ አቶ ካሣ ተ/ብርሃን የፌዴሬሽን ም/ቤት ፕሬዚደንት
- ለተከበሩ አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር
- ለተከበሩ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የአማራ ክልል ፕሬዚደንት
- ለተከበሩ አቶ ግርማ ሠይፉ የተወካዮች ም/ቤት አባል
- ለመገናኛ ብዙሃን

Tuesday 21 January 2014

ድሃን የምትወድና የምትረዳ ሴት፣ ርዮት፣ ሽብርተኛ ስትባል !

ጃኑዋሩ 22 ቀን 33ኛ አመቷን ታከብራለች። በሃይ ስኩል የእንግሊዘኛ አስተማሪ ነበረች። በሕገ መንግስቱ ላይ የተደነገገዉን መብት በመጠቀም፣ በተለያዩ አገር ውስጥ በሚታተሙ ሜዲያዎች ትጽፋለች። «እነርሱ እንዲጻፍ ከሚፈልጉት ዉጭ እንዲጻፍ የማይፈልጉት ባለስልጣናት፣ የሃሰት ክስ መሰርተዉ፣ ዳኛ ለተብዬዎች መመሪያ ሰጠዉ፣ መሰረተ ልማቶችን ለማፍረስ አሴራለች፣ ሽብርተኛ ናት» ብለዉ ፈረዱባት።
1185860_10200561003368447_1105290103_n
ይች ሴት ርዮት አለሙ ትባላለች። ጡቷ አካባቢ ችግር ስላለበት ክትትል እንደሚያሰልጋት እየታወቅም ክትትል ለማግኘት አልቻለችም። ከሁለት አመት ተኩል በላይ፣ ባላጠፋችዉ ጥፋት፣ ኢሕአዴግን ስለተቃወመች ብቻ፣ እየማቀቀች ነዉ። የርዮት ወንጀል አገሯ፣ ሕዝቧን መዉደዷ ነዉ።
ርይቶ አለሙ፣ ከጋዜጣኛ ነብዩ ሃይሉ ጋር በአዲስ ፕሬስ፣ ከጋዜጣኛ ስለሺ ሃጎስ ጋር በ ቼንጅ መጽሄት ላይ ሰርታለች። ነብዩና ስለሺ፣ በአንድነት ራዲዮ ስለርዮት አለሙ፣ ከሚያወቁት ያጋሩንን ጥቂቱን ላካፍላችሁ።
ያዉ በአገራችን ባለዉ የዘር ፖለቲካ ምክንያት «የትግራይ ልማት ማህበር»፣ «የአማራ ልማት ማህበር» የሚባሉ አሉ። እነዚህ ማህበራት በየቦታዉ ለልማት ሥራ በሚል ገንዘብ ያሰባስባሉ። የአማራዉ ልማት አማራ የሚላቸዉን ነዉ የሚያነጋግረዉ፣ የትግሬዉ ደግሞ ትግሬዎችን።
አንድ ጊዜ የትግራይ ልማት ማሕበር ርዮት በምታስትምረበት ትምህርት ቤት የገንዘብ ማሰባሰቢያ ትኬቶች ይሸጣል። አንዱ ትኬት 30 ብር ነበር። በትግራይ፣ መቀመጫ አጥተዉ በመሬት ላይ ተቀምጠዉ የሚማሩ ተማሪዎች የሚያሳይ ቪዲዮ አሳዩ። ርዮት «ይሄማ መሆን የለበትም» ብላ በቪዴዎ የታዩ ተማሪዎችን ለመርዳት ወሰነች። እርሷ ብቻ 300 ብር አወጥታ አሥር ትኬቶች ገዛች። ሌሎች ጓደኞቿም እንዲገዙ ግፊት አደረገች። ምንም እንኳን ትግሬ ባትሆንም፣ የትግራይ ልማት ማህበሩ ያነጣጠረው ትግሬዎች ላይ የነበረም ቢሆን፣ እርሷ ግን ያየቸው የተማሪዎችን ዘር ሳይሆን፣ ስብእናቸዉን እና ኢትዮጵያዊነታቸውን ነበር።
ርዮትን ያሰሩ ሰዎች፣ «መሰረተ ልማትን ለማፍረስ ፣ በሰዎች ላዩ ጉዳት ለማድረግ የምትፈልግ ፣ አሸባሪ ናት» ነዉ የሚሉን። እንግዲህ በትግራይ ያሉ ተማሪዎች ይመስክሩ።
በአገራችን ትልቅ የኢኮኖሚ ችግር እንዳለ የሚታወቅ ነዉ። ጥቂቶች እላይ ሲመጠቁ፣ አብዛኛዉ ኑሮ ከብዶት፣ በቀን አንዴ እየተመገበ ነዉ የሚኖረዉ። ርዮት አስተማሪ እንደመሆኗ በተማሪዎቿ አካባቢ ያለዉን ችግር ታዉቃለች። ብዙ ጊዜ በጠኔ ሲወድቁ አይታለች። ብዙዎች እንደ ታላቅ እህት ችግራቸውን ያጫዉቷታል። አቅሟ በፈቀደ መጠን ከማስተማር በተጨማሪ ተማሪዎቿን የምትረዳ ፣ የተከበረችና የተወደደች ምህሩ ነበረች። በጣም ችግረኛ ለሆኑ፣ አሥራ ሁለት ተማሪዎች፣ የሚለብሱት ዩኒፎርም በየአመቱ የምታሰፋ ነበረች።
ርዮትን ያሰሩ ሰዎች፣ «መሰረተ ልማትን ለማፍረስ ፣ በሰዎች ላዩ ጉዳት ለማድረግ የምትፈልግ አሸባሪ ናት » ነዉ የሚሉን። እንግዲህ በአዲስ አበባ ያሉ፣ ርዮት እንደ ታልቅ እህት የረዳቸቸዉን የደገፈቻቸው ተማሪዎች ይመስክሩ።
አንድ ጊዜ ደግሞ እንዲህ ሆነ። አንድ በጣም ጎበዝ የሆነ፣ ተማሪዎ፣ የማትሪክ ዉጤት እንደጠበቀዉ አልመጣለትም። የመንግስት ተቋማት መመደብ አልቻለም። በዚህም ምክንያት በጣም ተስፋ ቆርጦ እራሱን ወደ ማጥፋት ደረጃ ደረሰ። ይሄንን ስትሰማ ቤተሰቦቹን አነጋገረች። ያለዉን ነገር አስረዷት። በጣም ድሃዎች እንደመሆናቸው፣ ልጃቸውን የግል ትምህርት ቤት ከፍለው ሊያስተምሩት እንደማይችሉ ነገሯት። ይህን ወጣት፣ ወጭዉን በሙሉ ሸፍና፣ ዩኒቲ ኮሌጅ ገብቶ እንዲማር አደረግቸው።
እንግዲህ አስቡት ወገኖቼ፣ እንደ ርዮት አለሙ አይነት የተከበሩ፣ አገር ወዳድ፣ ለሰው የሚያዝኑ ኢትዮጵያዉያንን ነዉ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ሽብርተኞች እያለ ወደ ቃሊቲ የሚወረወረው። ዜጎች መልካም በሰሩ፣ የአገርንና የወገንን ጥቅም ባስቀደሙ፣ ለሕዝብ ክብርና ነጻነት በቆሙ፣ ፍትህን በሰበኩ፣ የአገሪቷ ባለስልጣናት የሚሰሩትን ስህተቶችን በደሎች ባጋለጡ ለምንድን ነዉ የሚታሰሩት ? ኢትዮጵያስ እስከምቼ ለልጆቿ ሲኦል ትሆናለች ?
አንዳንድ ሰዎች በጣም ክፉ ከመሆናቸው የተነሳ ሌሎች ሲሰቃዩ የሚደስቱ አለ። እነዚህ በዉስጣቸው ያለው የሕሊና ድምጽ የማይቃጭልባቸዉ ፣ ርህራሄና ሃዘኔታ የሚባል ነገር የሌላቸው፣ ለስብእና ክብር የማይሰጡ ናቸው። ኢሕአዴግ እየተመራ ያለ በእንደነዚህ አይነት ሰዎች ነዉ። እነዚህ ሰዎች የራሳቸዉን የጠላቻ እርካታ ለማጥገብ ሲሉ በሚሰሩት ግፍ፣ ኢሕአዴግን ወደ ገደል እየወሰዱኢት ነዉ።
የርዮት አለሙ መታሰር እንደ ፓርቲ ኢሕአዴግ ለሚያደርጋቸው የልማት እንቅስቃሴዎች ምንም አይጠቅምም። በፖለቲካም የበለጠ እንዲጠላ ነዉ እያደረገው ያለዉ። የኢሕአዴግ አባላትና ደጋፊዎች የሚመሯቸውን አክራሪዎች ገፍተዉ እንዲያስወጡ እመክራቸዋለሁ። በአስቸኳይ ርዮት አለሙ እንዲሁም ሌሎች የሕሊና እስረኞች መፈታት አለባቸው። ቀናት እየጨመሩ በሄዱ ቁጥር ነገሮች እየተወሳሰቡ ነዉ የሚመጡት። ኢሕአዴግ እየመነመነ፣ እነርዮት አለሙ ደግሞ ተወዳችነታቸው እየጨመረ ነዉ የሚመታዉ።
ርዮት አለሙ፣ አሁን ብትታሰርም፣ ሚሊዮኖች የርዮት አፍ ሆነዉ ድምጻቸዉን ያስተጋባሉ። የሚሊዮኖች የፍትህ ድምጽ የአራት ኪሎ ቤተ መንግስት ግድግዳን እያለፈ፣ ባለስልጣናቱ በተኙበት ይሰሙታል። ያለ ምንም ጥርጥር ርዮት አለሙ፣ እንደ ደራርቱ ቱሉ የኢትዮጵያን አረንጓዴ፣ ቢጫ ቀይ ሰንድቅ አላማ በላይዋ ላይ ለብሳ በክብር ከቃሊቲ ትወጣለች።
በርዮት ዙሪያ በአንድነት ራዲዮ የቀረበዉን ለማዳመጥ የሚከተለዉን ይጫኑ !

ግርማ ካሳ

Monday 20 January 2014

ዶ/ር ነጋሶ አንድነት ፓርቲ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ስላልተመቻቸው ለብሔራዊ ምክር ቤቱ ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ ምላሽ ባለማግኘታቸው ከፖለቲካው ዓለም ለመሰናበት ወሰኑ ::



‹‹የሕዝብ መብት ከሚቃወም የፖለቲካ ድርጅት ጋር መሥራት አስቸጋሪ ነው›› ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ
‹‹የአንድነትን አቋም ሳያውቁ የፓርቲው አባል ሆነዋል ለማለት ያስቸግራል››  አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ

ላለፉት ሁለት ዓመታት የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀመንበር የነበሩትና ለ45 ዓመታት በፖለቲካ ውስጥ እንደቆዩ የሚናገሩት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ ከጥር 8 ቀን 2006 ዓ.ም.
ጀምሮ ከማንኛውም ዓይነት የፖለቲካ እንቅስቃሴ ራሳቸውን ማግለላቸውን አስታወቁ፡፡ በአሁኑ ወቅት ከፖለቲካው ዓለም ለመሰናበት የወሰኑት አንድነት ፓርቲ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ስላልተመቻቸው ለብሔራዊ ምክር ቤቱ ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ ምላሽ ባለማግኘታቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ዶ/ር ነጋሶ እንደገለጹት፣ መድረክ ግንባር ከመሆኑ አስቀድሞ ባነሳቸው ሐሳቦች ላይ ሁሉም ድርጅቶች ጠቅላላ ጉባዔ በማድረግ ከተወያዩባቸው በኋላ ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ መስማማታቸውንም ለመድረክ በመግለጽ መድረክ ወደ ግንባር መሸጋገሩን አስታውሰዋል፡፡

በሚያዝያ ወር 2005 ዓ.ም. በአንድነት ፓርቲና በእሳቸው የአመለካከት፣ የአቋምና የአቅጣጫ ልዩነት መፈጠሩን የገለጹት ዶ/ር ነጋሶ፣ አንድነት ፓርቲ መድረክ ወደ ግንባር የተቀየረው በጠቅላላ ጉባዔውና በብሔራዊ ምክር ቤቱ እምነትና ውሳኔ ሳይሆን በአመራሮች መሆኑን በመጥቀስ፣ እንደማይስማማ በዚያን ወቅት ባደረገው ግምግማ ላይ በመግለጹ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

መድረክ ወደ ግንባር ከመቀየሩ አስቀድሞ ይፋ ባደረገው ፕሮግራም ላይ ሁሉም የፖለቲካ ድርጅቶች ተወያይተውና ተመካክረው በሕገ መንግሥት ጉዳይ፣ በቤት ጥያቄና በሌሎችም በተነሱ ነጥቦች ላይ መስማማታቸውን የጠቆሙት ዶ/ር ነጋሶ፣ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 39 ላይ ብቻ ልዩነት እንዳለው አንድነት ገልጾ የሽግግር ሒደቱ በሰላም መፈጸሙን አስታውሰዋል፡፡

ሽግግሩ ወራትን ካስቆጠረ በኋላ በሕገወጥ መንገድ እንደተደረገ በማስመሰል ወደኋላ መመለስ አሳፋሪ ድርጊት ከመሆኑም በተጨማሪ የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤትና የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት፣ ፓርቲው የማይስማማበትን ነጥብ ይዞ ወደ መድረክ በመሄድ መወያየት ሲገባቸው፣ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ መስጠታቸው ትክክል አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም የነበሩትን የተሳሳቱ ሒደቶች በመጥቀስ እርማት እንዲደረግ ዶ/ር ነጋሶ ለአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት ሰብሳቢ የተለያዩ ጥያቄዎችን ያቀረቡ ቢሆንም፣ ምላሽ ሊያገኙ አለመቻላቸውን ተናግረዋል፡፡

ሌላው ዶ/ር ነጋሶ የሚያነሱት ጥያቄ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 39 ላይ የተጠቀሰውን ‹‹የብሔር ብሔረሰቦች መብት የራስን ዕድል በራስ ከመወሰን እስከ መገንጠል›› የሚለውን የሕዝቦች የመብት ጥያቄ አንድነት ውድቅ ማድረጉ ተገቢ አለመሆኑን ሲሆን፣ ‹‹የሕዝብን መብት ከሚቃወም የፖለቲካ ድርጅት ጋር መሥራት አስቸጋሪ ነው፤›› ብለዋል፡፡

አንድነት የመድረክን ወደ ግንባር መቀየር የማይቀበለው ‹‹የውህደት›› ኅብረ ብሔራዊ ፓርቲ መመሥረት እንዳለበት ስለሚፈልግ መሆኑን የጠቆሙት ዶ/ር ነጋሶ፣ በሕጋዊና በትክክለኛ መንገድ ስምምነት የተፈጸመበትን ‹‹ግንባር›› ‹‹ውህደት›› ካልሆነ ማለት የማይሆንና የማያስኬድ መንገድ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ያልተስማሙባቸውን ነጥቦችና ስምምነት ከተደረገ በኋላ ወደ ኋላ መመለስ አግባብ አለመሆኑን በመጠቆም ላቀረቧቸው ጥያቄዎች የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት ምላሽ በመንፈጉ ምክንያት፣ ዶ/ር ነጋሶ ከፖለቲካው ዓለም መሰናበታቸውን ይፋ ቢያደርጉም፣ ቀደም ብሎም ከፖለቲካ ሥራና ተሳትፎ ለመልቀቅ በማኮብኮብ ላይ እንደነበሩ አልሸሸጉም፡፡

ምክንያታቸውንም ሲገልጹ ነሐሴ 3 ቀን 2005 ዓ.ም 70 ዓመት ሞልቷቸዋል፡፡ ከዕድሜያቸው ከግማሽ በላይ ለ45 ዓመታት በፖለቲካ ውስጥ ቆይተዋል፡፡ የኦሮሞ ሕዝብን የፖለቲካ ባህል ሲያስታውሱ፣ በኦሮሞ ገዳ ዲሞክራሲ አንድ መሪ ዕድሜው 48 ሲሆነው የአመራር ሥልጣኑን ለወጣቱ መልቀቅ እንዳለበት የሚገልጸውን ተግባራዊ ማድረግ ተገቢ መሆኑንም ማሰባቸውን አብራርተዋል፡፡

ሙሉ በሙሉ ከፖለቲካ ዓለም ራሳቸውን ማግለላቸውን ከዚህ በኋላ በማንኛውም መንገድ ማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት ውስጥ በአባልነትም ሆነ በመአራርነት እንደማይሳተፉ ያረጋገጡት ዶ/ር ነጋሶ፣ ‹‹ጆሮዬ ለፖለቲካ ክፍት ይሆናል፤ የማስበውን በጽሑፍና በአፌ እናገራለሁ፤ አንድነትንም ሆነ ሌሎችንም በመዋቅራዊ መልክ ሳይሆን እደግፋለሁ፤ ሲያስፈልግ እተቻለሁ፤ ሲያስፈልግ እቃወማለሁ፤›› ብለዋል፡፡

አንድነት ፓርቲ ለዶ/ር ነጋሶ ከፖለቲካ መገለል ምክንያት ስለመሆኑ ለተነሳለት ጥያቄ በሕዝብ ግንኙነት አማካይነት ምላሽ ሰጥቷል፡፡

ፓርቲው በቅርቡ አዲስ አመራር መምረጡንና ቀደም ሲል በሊቀመንበርነት ሲመሩ የነበሩት ዶ/ር ነጋሶ፣ ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ የሥልጣን ሽግግሩን ፈጽመው ለብሔራዊ ምክር ቤቱ አቅርበው ሽግግሩን ማፅደቃቸውን የገለጹት የአንድነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ናቸው፡፡

ለብሔራዊ ምክር ቤቱ የአዲሱን አመራር ቀጣይ የሥራ የሽግግር ጊዜ ሲያቀርቡ፣ ከዕድሜያቸው ጋር በተገናኘ ለቤተሰቦቻቸው ራሳቸውን ከፖለቲካ እንደሚያገሉ ቃል መግባታቸውን የተናገሩት አቶ ሀብታሙ፣ በመድረክ ላይ ያላቸውን አቋምም ግልጽ ማድረጋቸውን አክለዋል፡፡

ዶ/ር ነጋሶ አንድነት መድረክን መገምገሙና ማጥናቱ ትክክልና ተገቢም ነው፡፡ የግንባሩ አባል የሆነ ድርጅት ፖለቲካውን አግባብ ባለው መንገድ እየመራ ነው? አይደለም? የሚለውን ጥናት ማድረግ ተገቢ ነው ካሉ በኋላ፣ መድረክ አሁን ባለው ሁኔታ የሚታየውን ነገር ሁሉ ማሻሻያ በማድረግ ሊቀጥል ይገባል የሚል አቋም እንዳላቸው መናገራቸውን አቶ ሀብታሙ ገልጸዋል፡፡

አንድነት ፓርቲ መድረክ ወደ ውህደት በማደግ አንድ ግዙፍ ብሔራዊ ፓርቲ እንዲፈጠር ያቀረበውን ሐሳብ በቀላሉ ሊሳካ የሚችል ባለመሆኑ፣ ሐሳቡን እንደማይደግፉም ዶ/ር ነጋሶ ማሳወቃቸውን አቶ ሀብታሙ ጠቁመዋል፡፡

ዶ/ር ነጋሶ ያነሱትን የልዩነትና የድጋፍ ሐሳብ አንድነት ፓርቲ እንደሚያከብር የገለጹት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው፣ ፓርቲው ግን ግልጽ የሆኑ የፖለቲካ አማራጮች እንዳሉት፣ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ትግልን ወደፊት ለመግፋት ብሔራዊ ምክር ቤቱና ጠቅላላ ጉባዔው አስቀድሞ ባዘጋጁዋቸውና በሚያሻሽሉዋቸው ነጥቦች ትግሉን እንደሚቀጥል አስረድተዋል፡፡

አንቀጽ 39ን በሚመለከት አንድነት የብሔር ብሔረሰቦችን መብት በተመለከተ ሕገ መንግሥቱ የሚያነሳቸውን ነጥቦች ፍፁም በሆነ ሁኔታ እንደሚያከብር የተናገሩት አቶ ሀብታሙ፣ ዶ/ር ነጋሶ የአንድነት ፓርቲን አቋም በግልጽ ሳያውቁ የፓርቲው አባል ሆነዋል ለማለት እንደሚያስቸግር አክለዋል፡፡ አንድነት ፓርቲ ከአንቀጽ 39 የማይቀበለው በመጨረሻው ንዑስ አንቀጽ ላይ የተቀመጠውን ‹‹እስከ መገንጠል›› የሚለውን ሐረግ መሆኑን ይህንንም በኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና አንድነት ላይ የተቃጣ አደጋ በመሆኑ፣ መቼም ቢሆን የአገሪቱን ሉዓላዊነትና አንድነት ለማንም ለድርድር እንደማያቀርብ በግልጽ ሊታወቅ እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡


ዶ/ር ነጋሶ ላለፉት 45 ዓመታት በቆዩበት የፖለቲካ ሕይወታቸው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አባል፣ እንዲሁም የኢሕአዴግ አባል የሆነው የኦሮሞ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦሕዴድ) አመራር እንደነበሩ አይዘነጋም፡፡ ከኢሕአዴግ ጋር ከመለያየታቸው በፊት ለስድስት ዓመታት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት በመሆን አገልግለዋል፡፡ ከዚያም ከቀድሞ የአገር መከላከያ ሚኒስትር አቶ ስዬ አብርሃ ጋር በመሆን የአንድነት ፓርቲ አባል ከመሆናቸውም በላይ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ የፓርቲው አመራር አባልና ሊቀመንበር መሆን ችለው ነበር፡፡

minilik salsawi