Wednesday 7 January 2015

ኮማንደር ቢኒያም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን በድቅድቅ ጨለማ ብርድ ላይ እያስተኛው በማሰቃየት ላይ ነው



በካንጋሮው ፍርድ ፍትሃዊ ባልሆነ ፍርድ እስር ቤት የተወረወረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ፍርድ ቤት በማያውቀው ሁኔታ በአንድ የህወሓት ኮማንደር በእስር ቤት ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰበት እንደሚገኝ ከስፍራው ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመለከተ።
ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት ማን እንደሚመራት በማይታወቅባት ሁኔታ አንድ ደህንነት ወይም ወታደር የፈለገውን የማዘዝ ስልጣን ያለው ሲሆን እንገዛለታለን የሚሉትን ህገመንግስት ወደ ጎን በመተው የፈለጋቸውን እርምጃ እየወሰዱ በመሆኑ በስር ዓቱ ውስጥ ያለውን አለመደማመጥ ያሳያል የሚሉ የፖለቲካ ተንታኞች በቅርቡ ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን በአንድ ደህንነት ት ዕዛዝ ብቻ ለ3 ሳምንታት ከሃገር እንዳይወጣ ፓስፖርቱን መቀማቱን ያስታውሳሉ።

በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ በዝዋይ እስር ቤት እየደረሰ ያለው ስቃይ ኮማንደር ቢኒያም በሚባል አዛዥ ሲሆን ተመስገንን በአንድ ምሽት ከ5 ጊዜ በላይ በድቅድቅ ለሊት በማስወጣት ብርድ ላይ እንደሚያስተኙት ከስፍራው የደረሰው መርጃ ያጋልጣል።
በተለይ ተመስገን ደሳለኝ “የመንግስት ገመና” በሚል ከእስር ቤት ከፃፈ በኋላ ደህነነቶች እና ይኸው ኮማንደር ቢኒያም የሚባል አዛዥ የእንግልሃለን ሬሳህን እዚህ ብንጠለው ዞር ብሎ የሚያይህ የለም በሚል እንደሚያስፈራሩት የጠቆሙት የዜና ምንጮቻችን ድብደባ እንደተፈጸመበትም ታውቋል።

ኢትዮጵያ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ግለሰቦች የሚያዙባት፤ በአንድ ግለሰብ ትዕዛዝም ሕይወት የሚጠፋባትና የሚበላሽባት ሃገር እየሆነች መምጣቱ የስርዓቱን ደጋፊዎች ሳይቀር እያስቆጣ እንደሚገኝ ከተለያዩ ስፍራዎች የሚገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

Source:: Zehabesha

0 comments:

Post a Comment