Wednesday 30 April 2014

ከዛሬ ጀመሮ የዞን ዘጠኝ ኩሩ አባል መሆኔን አረጋግጣለሁ – ግርማ ካሳ

ርዮት አለሙ፣ እስክንድር ነጋ፣ በቀለ ገርባ …….እያልን ስሞችን መዘርዘር እንችላለን። በብዙ ሺሆች የሚቆጠሩ ዜጎች ሕገ ወጥና ኢፍትሃዊ በሆነ መንገድ የታሰሩ ወገኖቻችን፣ ከእሥር እንዲፈቱ ስንጠብቅ ፣ ሌሎች እየተጨመሩ ነው። ከቃሊት ዉጭ ሆነው እነ ርዪትን ሲጎበኙ የነበሩ አሁን እነ ርዮት አለሙን እየተቀላቀሉ ነው።
ዞን ዘጠኞች ፣ እነ ጋዜጠኛ ተስፋአለም፣ የሚጽፉትን ፣ የሚጦምሩትን እኛም አንብበነዋል። በድብቅና በሚስጠር አልነበረም ሃሳባቸውን ሲያካፍሉን የነበሩት። የኛ አካል ናቸው። እነማን እንደሆኑ እናውቃቸዋለን። የታሰሩት ወንጀል ስለፈጸሙ አይደለም። ሕግን ስለጣሱ አይደለም። ወንጀላቸው አገራቸውን መዉደዳቸው ነው። ወንጀላቸው ለፍትህ መቆማቸው ነው። ወንጀላቸው ዶር መራራ ጉዲና እንዳሉት፣ ከጫካ የወጡ ግን ጫካ ከነርሱ ያልወጣ፣ ከበስተጀርባ ሆነው እነ ኃይለማሪያም ደሳለኝ እያዘዙ የሚፈልጡና የሚቆርጡ፣ ከሕግ በላይ የሁኑና ለሕግ ደንታ የሌላቸው፣ ጥቂቶች እንዲጽፉ የማይፈልጉት ስለጻፉ ነው። «እነዚህን የሳይበር ስፔስ አርበኞች ልክ ብናገባቸው፣ ሌሎችም ፈርተው አርፈው ይቀመጣሉ» የሚል የተሳሳተና እንጭጭ አስተሳሰብ ስላላቸው ነው።
እንግዲህ ጥያቄዉ «የኛ ምላሽ ምንድነ ነው የሚሆነው ? » የሚለው ነዉ። የአለም አቀፍ ድርጅቶች፣ በግለሰብ ደረጃ በርካታ ኢትዮጵያዊያን የተሰማንን ሐዘንና ንዴት ገልጸናል። ተገቢም ነው።
ነገር ግን ከዚያ አልፈን መሄድ መቻል ያለብን ይመስለኛል። አገዛዙ ዋና ግቡ እኛን ተስፋ ማስቆረጥ ነው። ገዛ ተጋሩ በሚባል የፓልቶክ ክፍል አንዲት የአገዛዙ ካድሬ ትሁን ደጋፊ፣ አገዛዙ ላይ ችግር ያለንን ሰዎች »ፓፕ ኮርኖች» (ፈንድሻውች) ነበር ያለችን። ለጊዜ ቡፍ ብለን ጸጥ የምንል !!!!!!
እንግዲህ ምርጫዉ የኛ ነው። እኛ ሚሊዮኖች ነን። እነርሱ ጥቂቶች ናቸው። እኛ ፍቅርን ፣ ሰላምን፣ እኩልነትን አንድነት እንፈልጋለን። እነርሱ ዘረኝነትን፣ ጭካኔን፣ ግፍን፣ መከፋፈልን ይሰብካሉ። እኛ አገራችን በፍቅር እንገባ እንላለን። እነርሱ ግን «እኛ ስልጣን ላይ እንቅይ እንጂ አገር ብትፈልግ ትፈራርስ» ይላሉ። እኛ የዘር፣ የሃይማኖት የጾታ፣ የእድሜ ልዩነት ሳይኖር እያንዳንዱን ዜጋ፣ አዎ ከጠ/ሚኒስተሩ ጀመሮ እስከ ሊስትሮዉ ፣ በስብእናዉና በኢትዮጵያዊነቱ የከበረ ነው እንላለን። እነርሱን ግን« ሁሉንም አዋቂዎች፣ ፖሊሱም ፣አቃቢ ሕጉም፣ ዳኛዉም፣ ሕግ አውጭዉም፣ ሕግ አስፈጻሚዉም፣ ኢኮኖሚስቱም፣ ኢንጂነሩም እኛ ብቻ ነን። ሌላዉ ከጫማችን በታች ተረግጦ መቀመጥ ነው ያለበት» ይላሉ።
እንግዲህ ምርጫው የኛ ነው። እንደ እንስሳ አንገታችን ላይ ማነቆ ታስሮ፣ ጥቂቶች እየጎተቱን እና እንደፈለገ እየተጫወቱበን መኖር፣ ወይም ነጻነታችንን ማወጅ። ዝም ብለን ለጊዜው ብቻ የምንጮህ ፓፕኮርኖች መሆን ወይም አለትን የሚሰባብር ዳይናሚት መሆን። እነርሱ እንደሚፈልጉትና እንደሚመኙት፣ ዝምታን መርጠን፣ አፋችን ዘግተን መቀመጥ፣ ወይም ዳግማዊ ዞን ዘጠኖች በመሆን የዞን ዘጠኝ አባላት ቁጥርን ከስድስት፣ ወደ 6 ፣ ስድሳ ሚሊዮን ማሳደግ። የናንተን አላውቅም እኔ ግን፣ ከዛሬ ጀመሮ የዞን ዘጠኝ ኩሩ አባል መሆኔን አረጋግጣለሁ።
መርዛማ እባብ ከመንደፍ ዉጭ፣ ሌላ ነገር አያውቅም። እነርሱም ማሰር እንጂ መፍታት አያውቁም። ዜጎችን ማሸበር እንጂ ማረጋጋት አያውቁም። ኢትዮጵያዉያንን ማዋረድ እንጂ ማክበር አያውቁም። ይህ ለሃያ አመታት የዘለቀ ግፍ አንድ ቦታ ላይ መቆም አለበት። አሁን መቆም አለበት። ሊያስቆሙት የሚችሉት ደግሞ እነ ጆን ኬሪ አይደሉም። እኛ ብቻ ነን።
ሚያዚያ 26 (ሜይ 3 ቀን) በአንድነት ፓርቲ የተዘጋጀ የእሪታ ቀን ሰላማዊ ሰልፍ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ከብዙ ግፊትና ትግል በኋላ አስተዳደሩ ለሰልፉ እውቅና ሰጧል። ሰልፉ ሰላማዊና ሕጋዊ ሰልፍ ነው። የምንፈራበትም፣ የምንሸሽበት ምንም ምክንያት የለም። ሰልፍ የምንወጣዉ ለፖለቲከኞች ወይንም ለአንድ ፓርቲ ፣ ወይንም ለሌሎች አይደለም። ሰልፍ የምንወጣው ለራሳችን ስንል ነው። «በአዲስ አበባ እድገት አለ። ዴሞክራሲ አለ። ስርዓቱ መቀጠል አለበት። ኢሕአዴ ጥሩ እያደረገ ነው። የታሰሩትም መታሰራቸው ተገቢ ነው» የሚሉ እነ ሚሚ ስብሀቱ ሰልፍ ባይወጡ ብዙ አያስገርምም። ግን በልባችን ለውጥ እየፈለግን፣ መሰረታዊ የመብትና የኢኮኖሚ ጥያቄዎች እያሉን፣ ዝምታን ከመረጥን ግን፣ ይሄን የሚያዚያ 26ቱን ሰልፍ እንደ አንድ መድረክ ተጠቅመን ድምጻችንን ማሰማት ካቃተን ግን፣ ታዲያ እንዴት እንዘልቀዋለን ?
እንግዲህ ከሚሊዮኖች አንዱ እንሁ እላለሁ። እንዉጣ። ድምጻችንን እናሰማ። መብታችንን እናስከበር። የሕዝብ ጉልበትና አቅም ምን ማለት እንደሆነ እናሳይ። ለታሰሩ አጋርነታችንን እንግለጽ። ስድስት ዞን ዘጠኖች ቢታሰሩ ሚሊዮኖች እንደተወለዱ እናስመስክር።
እመኑኝ የሕዝብን ጉልበት ሊቋቋም የሚችል ማንም ኃይል የለም !!!!!!1512409_847636081919521_8670816689421983005_n (1)

Tuesday 29 April 2014

Ethiopian Journalists Forum (EJF) is attending the AU meeting in Angola, made a presentation about the current situation of Ethiopia

Image

 MINILIK SALSAWI 

EJF made a presentation about the current situation of Ethiopia including the unlawful arrest of Zone 9 members and Other Journalists . Ethiopia was an agenda and participants were discussing in depth about it. The recent crackdown was something that shocked many. The Head of the EJF delegation said that There were some people crying when we explained what is happening there. By the way we issued a joint statement there. We are also working to submit a letter to AU to work on the case.

EJF Delegation said We also recommended what the AU should do to overcome the problem in Ethiopia.We also meet with AU commissioner and discussed with him about the situation of journalists. We did the same thing with IFEX director. We made an aggement with her to join her org. as a member. We have done a lot of things there. We have distributed a document about the freedom of speech and of the press in Ethiopia to all participants. We explained about what is going in Ethiopia and the way out.

The EJF Delegation also added that We gave detail information about Ethiopian Journalists and Zone 9 Bloggers and the unlawful acts.Also also discussed the situation of Ethio Mihdar newspaper Journalist Ephrem, the journalists experianced a car accident recently. 

The Chairman of EJF Journalist Betr yakob Getahun said that Ethiopian Journalists Forum will become a member of international journalists federation, East African journalists Association, and Ifex. and He said ".. I discussed with the directory of ifex and she promised us to write a letter to organizations to accept us to their membership.We have also made an agreement to work together in the future...

Journalist Betre Yakob Getahun said ; "we have made an appointment with African Union representative to meet and Addis and see what we can do in the future...the meeting was sucssesful for us. We did what we had planed to do. it was our plan to do when we left Addis to show the real situation of Ethiopia and to integrate our association we the international and regional organizations.EJF has got welcome by almost all organization including AU... " 

EJF Delegation said that There was a team comprised of different organization to issue a statement about Zone 9. I hope it will be issued these days. EJF was the coordinator and main actor of the team. A representative of the AU was a part of the team. The team is also to submit a letter to AU to actively react against the Ethiopian government with regarding to zone 9.

አንዷለም አራጌ እና የቃሊቲው ህይወት




(EMF) – አንዷለም አራጌ የአንድነት ፓርቲ አመራር አባል የነበረ ወጣት ነው። በኋላ ላይ የኢህ አዴግ ሰዎች ባቀናበሩት ድራማ አሸባሪ ተብሎ ለእስር ተዳረገ። ቃሊቲ በእስር ላይ ሆኖ ብቻውን በጨለማ ቤት ውስጥ ከመታሰር ጀምሮ ብዙ እንግልት እና መከራን እየተቀበለ ይገኛል። ይህ ሁሉ የሆነው አንዷለም በተቃዋሚው ጎራ በመቆሙ ብቻ ሳይሆን፤ ጎበዝ መሪ በመሆኑም ጭምር ነው። አሁን በ እስር ላይ ሆኖም እንኳን፤ ስሜቱን ለመጉዳት ሲባል እሱን ለመጠየቅ የሚሄዱ ጠያቂዎች ይዋከባሉ፤ እንዲጠይቁትም አይፈቀድላቸውም።
ከትላንት በስትያ አንዷለምን ለመጠየቅ ወደ እስር ቤት ያመሩት፤ ብቸኛው የፓርላማ ውስጥ ተቃዋሚ ክቡር አቶ ግርማ ሰይፉ ትዝብታቸውን ገልጸዋል። የአቶ ግርማ ትዝብት “አንዱዓለምን ለመጠየቅ ቃሊቲ ጎራ ብዬ ነበር፡፡” በማለት ይጀምሩና በአንዷለም ላይ እየደረሰ ያለውን እንግልት በዝርዝር ገልጸውታል። እንዲህ በማለት ይቀጥላሉ አቶ ግርማ….
አንዱዓለም እንደተለመደው በጠንካራ ሞራልና ለሰው ልጅ ክብር በሚሰጠው መንፈሱ ላይ ምንም ለውጥ አይታይም፡፡ የሚበድሉትን ቢሆን ለምን? ብሎ ይጠይቃል እንጂ የበቀለኝነት ሰሜት የለበትም፡፡ ነገር ግን በፍፁም ተሰፋ እያሰቆረጠው ምን አልባት ወደ ርሃብ አድማ ሊገፋኝ ይችላል ብሎ የሰጋው ከብዙ ሺ ከሚቆጠሩ እሰረኞች በተለየ ሁኔታ የሚሰተናገድበት አያያዝ ምቾት አልሰጠውም፡፡ መብቱን እያስደፈረ እንደሆነ ይሰማዋል፡፡
እሱን ለመጠየቅ ከባለቤቱ እና ከእኔ በስተቀር ይህን ሁሉ ኪሎ ሜትር አቋርጠው የመጡ ሰዎችን እየመለሱ ችግር እየፈጠሩበት እንደሆነ ነግሮኛል፡፡ ማንም ጠያቂ እርሱ እንዲጠይቅ አይፈቀድለትም፡፡ ይህ ደግሞ ፌዝ የሚሆነው ለእርሱ ደህንነት ብለን ነው የሚሉት መልስ ነው፡፡ በተለይ ትላንት ምሽት ድንገት በተደረገ ብረበራ ከማረሚያ ቤቱ ላይብረሪ ተውሶ ሲያነባቸው ከነበሩተ መፅኃፎች ላይ የያዛቸውን ማስታወሻዎች በሙሉ ወስደውበታል፡፡ በማረሚያ ቤቱ ደንብ ላይ ይህ ክልከላ ስለመኖሩ ጠይቄው የማረሚያ ቤቱን ደንብና መመሪያ እንዲሰጡኝ ከጠየቅሁ ስድሰት ወር ያለፈ ቢሆንም እስከ አሁን እንዳልሰጡት ነግሮኛል፡፡
ማረሚያ ቤቱ ከህገ መንግሰት በተቃራኒ የሆነ መመሪያ የማውጣት መብትም የለውም፡፡ በነገራችን ላይ የአንዱዓለም ጠያቂዎች እንዳይጎበኙት የተጣለበትን ክልከላ አምሳደር ጥሩነህ ዜናም እንደሚያውቁት ነገር ግን ይህ መመሪያ ስለሆነ እንደሆነ ገልፀውልኝ፣ መመሪያው ከህገመንግሰት ጋር የሚጋጭ ነገር ካለው እንደሚያዩት መደበኛ ባልሆነ ውይይት ገልፀውልኝ ነበር፡፡ አንድ እስረኛ በተለየ ሁኔታ በዘመድ አዝማድ ጓደኛ እንዳይጠየቅ ገደብ ለምን እንደሚደረግበት ሊገባኝ ባይችልም፡፡ ማረሚያ ቤቱ ውስጥ ከመደበኛው በተለይ የሚደረጉ ተግባራትን ተዉ የሚል ያለ አይመስልም፡፡
አንዱዓለም ቃሊቲ ከገባ ጀምሮ በልዩ ቅጣት ክፍል የሚገኝ ሲሆን በዚህ ክፍልም ልዩ ጥበቃ ይደረግበታል፡፡ አንዱዓለም የሚላኩለት መፅሃፎች በጊዜው እንደማይገቡለትና ከተላከለት ስምንት መፅሃፍ ውስጥ 2 አይገባም ከተባለ በኋላ ወደ ቤተሰቦቹም አለመመለሱንም ገልጾልኛል፡፡ ለክፉም ለደጉ አንዱዓለም ለመጉዳት የሚንቀሳቀሱ የመንግሰት ኃላፊዎችም ሆኖ ልወደድ ባይ የማረሚያ ቤት ሹሞች ከዚህ ተግባራቸው ቢቆጠቡ ጥቅሙ የጋራ ነው፡፡ አንዱዓለም ሰርቆ ወይም ሀገር ከድቶ አይደለም በእስር ላይ የሚገኘው፡፡ ለሀገሩ ነፃነት የድርሻዬን እውጣለሁ ብሎ በሰላማዊ መንገድ ሲንቀሳቀስ ይህ ዜጋ ለወንበራችን ጠር ነው ብለው በፈሩ እና በሀሰት በወነጀሉት አካላት ምክንያት ነው፡፡ ሌቦችን ወንጀለኞች እንደፈለጉ በሚሆኑበት እስር ቤት ጀግኖችን ማሰቃየት ማንገላታ አሁንም ፍርሃታቸው እንዳለቀቃቸው ከማሳየት ውጭ አንዱዓለምን መንፈስ እንደማይጎዳው እርግጠኛ ነኝ፡፡ የአሳሪዎቹን በቀለኝነት ግን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡

የታሰሩት የሰማያዊ አመራሮችና አባላት በደል እየደረሰባቸው ነው

(EMF) ባለፈው ሳምንት ሰማያዊ ፓርቲ ላደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ቅሥቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ አመራሮችና አባላት በእስር ቤት ውስጥ መሆናቸው ይታወቃል። እነዚህ በቅስቀሳው ወቅት ፖሊስ በህገ ወጥ መንገድ ያሰራቸው የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት እስር ቤት ውስጥ በደል እየደረሰባቸው መሆኑንም ተናግረዋል። ዮናታን ተስፋዬ ይህን በተመለከተ እንዲህ ብሏል።
የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እና አመራሮች
የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እና አመራሮች

በየካ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የሚገኙት አባላትና አመራሮች ትናንት ምግብ እንዳይገባላቸው በመከልከሉ ጾማቸውን አድረዋል፡፡ በተመሳሳይ በቤተሰብና በአባላት እንዳይጠየቁም እየተከለከሉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ በጉለሌ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ከሌሎች እስረኞች በተለየ በር በጊዜ እንደሚዘጋባቸው፣ እንዳይጠየቁ እንደተከለከሉና ሌሎችም በደሎች እየደረሱባቸውመሆኑን ገልጸዋል፡፡ ታሳሪዎቹ እየተበደሉ መሆኑን ለፖሊሶች በሚናገሩበት ወቅትም ‹‹እኛ ምን እናድርጋችሁ! ታዘን ነው! እናንተን ያሰራችሁ ሌላ አካል ነው፡፡ እኛ አይደለንም!›› የሚል መልስ እደተሰጣቸው ገልጸዋል፡፡


Monday 28 April 2014

አገር እንዲህ ኾናም አትቀርም

በጽዮን ግርማ

Mimi Sebhatu
Mimi Sebhatu
ዘወትር እንደምታደርገው ሁሉ በምታዝበት ሬዲዮ ጣቢያ ጓደኞቿን ሰብስባ ወደ ስቱዲዮ የገባችው ሚሚ ስብሃቱ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ ስለታሠሩት ሁለት ጋዜጠኞችና ሰባት ጦማሪዎች ከፖሊስ አገኘኹት ያለችውን መረጃ ጠቅሳ ስታወራ ነበር፡፡ ኢትዮጵያን ለማተራመስ ከሚሠራው አርቲክል ዐሥራ ዘጠኝ ከሚባል ድርጅት ጋር ሲሠሩ ነበር፣ ትልልቅ ሆቴል እየተገናኙ ይወያዩ ነበር፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰዎችን ያደራጁ ነበር፣ ከሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅትና ከአምነስቲ እንዲሁም ከግብጽና ከኤርትራ ገንዘብ ይቀበሉ ነበር፤  የሚሉ ውርጅብኞችን በማውረድ እነርሱን የኢትዮጵያ ጠላት እራሷን ደግሞ የኢትዮጵያ ወዳጅ አድርጋ በመሳል ውንጀላዋን ስታዥጎደጉደው ነበር፡፡
በወሬዋ መካከልም ‹‹ይህ ሞያ ሠላሣ ዓመት ያገለገልኩበት ነው፡፡ ታአማኒነት ያለኝ ጋዜጠኛ ስለመኾኔ ደግሞ የኢትዮጵያ ሕዝብ ምስክር ይኾነኛል›› ስትል ነበር፡፡ እንዳለችው ሠላሳ ዓመት በማገልገል ተአማኒነት የሚገኝ ቢኾንማ ዛሬ ጋዜጠኝነት በዚህ ደረጃ አይዘቅጥም ነበር፡፡ ሚሚ ዛሬ እንኳን ከፖሊስ አገኘኹት ያለችውን መረጃ ዜና አድርጋ ለማቅረብ አልፈለችገም፡፡ ከእርሷ በዕድሜ በጣም የሚያንሱትን በአስተሳሰብ ግን በእጅጉ የሚልቁትን ወጣቶች አገር ሊያተራምሱ ስትል ወቀሰቻቸው፡፡ ኢትዮጵያ እኮ የአንድ ግለሰብ መኖሪያ አይደለችም፡፡ የሁላችንም ናት፣ ሁላችንም ባለመብቶች ነን፡፡ እነዚህ ወጣቶች እዚሁ አገር ቤተሰብ አላቸው አገሪቱ ስትተራመስ ቤተሰቦቻቸው ይተራመሳሉ ቢያንስ እርሱ ያሳስባቸዋል፡፡
በአመለካከት እና በአስተሳሰብ ስለተለዩ አገር ያተራምሳሉ ማለት ትንሽ እንኳን ጉሮሮን ያዝ አያደርግም?
ተስፋለም በዕድሜም በጋዜጠኝነት ልምድም በቁጥር ከእርሷ በእጅጉ ያንሳል፡፡ በአስተሳሰብ፣በጠንካራ ሞራሉ፣ለሞያው በሚሰጠው ትልቅ ክብር ደግሞ ከእርሷ በእጅጉ ይለያልም ይልቃልም፡፡ እርሱ የሞያው ሥነምግባር በሚፈቅድለት ልክ ‹‹ጋዜጠኛ›› ነው፡፡ እርሱ የተቀደደ ጫማ አድርጎ ይሄዳታል እንጂ ለገንዘብ ሲል እስኪሪፕቶውን አያንሻፍፍም፡፡ እንደርሱ ቢኾንማ በጣም ቀላል ነበረለት እኮ እርሷ እንዳለችው ምን አርቲክል 19 ድረስ አስኬደው እርሷ የምታደርገውን ከእርሷ በላይ ማድረግ ይችል ነበርኮ ያውም ከእርሷ በተሻለ፡፡ እርሱ ግን የእዚህ ሰው አይደለም የእርሱ ፍላጎትና ጥረት ኢትዮጵያ ውስጥ ጋዜጠኝነት በራሱ ኃይል እንዲቆም የሚጥር፣ለሞያው ሥነ ምግባርና ክብር አንገቱን የሚሰጥ በማንኛውም መልኩ ትክክለኛ ዘገባ ለማቅረብ የሚጥር ጋዜጠኛ ነው፡፡ ለነገሩ ሚሚ ጋዜጠኞችን ለመወንጀል ስትሽቀዳደም ዛሬ የመጀመሪያዋ አይደለም፡፡ እኔም ከዛሬ በስተቀር ለዚች ሴት ቦታ ሰጥቼያት አላውቅም፡፡
ከእሥረኞቹ አንዱ ማንነቱን አበጥሬ የማውቀው ጋዜጠኛ ተስፋለም ነውና በእንደርሷ ያለች ጋዜጠኛ ተብዬ ‹‹ጋዜጠኛው ተስፋለም›› ሲወነጀል እየሰማኹ ግን መቻል አቃተኝ፡፡ እናም ወ/ሮ ሚሚን እንዲህ ልላት ፈለኩ፤ ‹‹ይቺ አገር የእሷና የጓደኞቿ ብቻ አይደለችም፣ ይቺ አገር እንዲህ ኾናም አትቀርም፤ምናልባት ነገ እርሷ በተስፋለም ቦታ እርሱ ደግሞ በእሷ ቦታ ይኾኑ ይኾናል፤   ዕድሜ ይስጣት እንጂ ያኔ ተስፋለም የጋዜጠኝነትን ሀሁ ጥሩ አድርጎ ያስተምራታል›› አበቃሁ!

Zone 9

Ethiopian Security Forces Open Fire on Students

There has been widespread protest by Oromo students in universities in Ethiopia against unpopular ‘Addis Ababa-Finfinnee surrounding integrated master plan’. Oromo students in Haromaya, Jimma, Ambo and Wollega universities held protests.
Although officials in Oromia state and Addis Ababa city administration insist the plan only intends to develop Addis Ababa and its surrounding, Oromo students and the wider Oromo elites believe the plan is to displace farmers in the outskirts and suburban areas of the city, meet the growing demand for land, and weaken the Oromo identity. The Ethiopian constitution grants a special interest to the Oromia state regarding administrative, resource and other socio-economic matters in Addis Ababa, in its article 49 which never have been implemented. This has largely resulted in significant resistance within the ruling party, OPDO, in Oromia and a continues pressure to materialize the implementation.
students shot2
students shot
The protest against the doomed to fail master plan is held in four universities sofar. Yesterday (26/04/2014) at Wollega University, the infamous and notorious Federal police opened fire at innocent Oromo students. Reports and eye witness indicate unknown number of students were hurt and some have fled to the bushes. The people of Nekemete town were prevented from joining the resistance. Even then some of the residents broke through line of federal police force and joined the protest.
At similar protest in Jimma university, the security forces picked more than 10 students and jailed them. Further 15 students in Ambo university were jailed.
The uproar against the plan is resonating across different segments of Oromo society. A singer by name Jafar Yusuf was jailed last week that is believed to be because he released a single condemning the plan. The diaspora is is voicing its concerns through the newly launched diaspora based Oromia Media Network
The security forces in Ethiopia are dominated by the Tigrayan minority who have been in power since the downfall of Derg communist regime in 1991. The Oromos are the most prosecuted in Ethiopia. More than 40000 Oromos are in jail, although the correct figure is hard to know.
Source: CNN

Ethiopia: Arrests Upstage Kerry Visit

9 Bloggers, Journalists Held Before US Official Arrives


(Nairobi, April 28, 2014) – The Ethiopian authorities should immediately release six bloggers and three journalists arrested on April 25 and 26, 2014, unless credible charges are promptly brought, Human Rights Watch said today.

United States Secretary of State John Kerry, who is scheduled to visit Ethiopia beginning April 29, should urge Ethiopian officials to unconditionally release all activists and journalists who have been arbitrarily detained or convicted in unfair trials, Human Rights Watch said. The arrests also came days before Ethiopia is scheduled to have its 
human rights record assessed at the United Nations Human Rights Council’s universal periodic review in Geneva on May 6.

“The nine arrests signal, once again, that anyone who criticizes the Ethiopian government will be silenced,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director at Human Rights Watch. “The timing of the arrests – just days before the US secretary of state’s visit – speaks volumes about Ethiopia’s disregard for free speech
.” 

On the afternoon of April 25, police in uniform and civilian clothes conducted what appeared to be a coordinated operation of near-simultaneous arrests. Six members of a group known as the “Zone9” bloggers – Befekadu Hailu, Atnaf Berahane, Natnael Feleke, Mahlet Fantahun, Zelalem Kibret, and Abel Wabela – were arrested at their offices and in the streets. Tesfalem Weldeyes, a freelance journalist, was also arrested during the operation. Edom Kassaye, a second freelance journalist, was arrested on either April 25 or 26; the circumstances of her arrest are unclear but all eight individuals were apparently taken to Maekelawi Police Station, the federal detention center in Addis Ababa, the capital.

The police searched the bloggers and journalists’ offices and homes, reportedly with search warrants, and confiscated private laptops and literature. On April 26, another journalist, 
Asmamaw Hailegeorgis of Addis Guday newspaper, was also arrested and is reportedly detained in Maekelawi. 

The detainees are currently being held incommunicado, Human Rights Watch said. On the morning of April 26, relatives were denied access to the detainees by Maekelawi guards, and only allowed to deposit food. 

Human Rights Watch released a report in October 2013 documenting serious human 
rights abuses, including torture and other ill-treatment, unlawful interrogation tactics, and poor detention conditions in Maekelawi against political detainees, including journalists. Detainees at Maekelawi are seldom granted access to legal counsel or their relatives during the initial investigation phase.

The Zone9 bloggers have faced increasing harassment by the authorities over the last six months. Sources told Human Rights Watch that one of the bloggers and one of the journalists have been regularly approached, including at home, by alleged intelligence agents and asked about the work of the group and their alleged links to political opposition parties and human rights groups. The blogger was asked a week before their arrest of the names and personal information of all the Zone9 members. The arrests on April 25, 2014, came two days after Zone9 posted a statement on social media saying they planned to increase their activism after a period of laying low because of ongoing intimidation.

A Human Rights Watch 
report in March described the technologies used by the Ethiopian government to conduct surveillance of perceived political opponents, activists, and journalists inside the country and among the diaspora. It highlights how the government’s monopoly over all mobile and Internet services through its sole, state-owned telecom operator, Ethio Telecom, facilitates abuse of surveillance powers. 

Kerry is scheduled to meet with Prime Minister Hailemariam Desalegn and Foreign Minister Tedros Adhanom in Addis Ababa “to discuss efforts to advance peace and democracy in the region.” Kerry should strongly urge the Ethiopian government to end arbitrary arrests, release all activists and journalists unjustly detained or convicted, and promptly amend draconian laws on freedom of association and terrorism that have frequently been used to justify arbitrary arrests and political prosecutions. The Obama administration has said very little about the need for human rights reforms in Ethiopia, Human Rights Watch said.

“Secretary Kerry should be clear that the Ethiopian government’s crackdown on media and civil society harms ties with the US,” Lefkow said.  “Continued repression in Ethiopia cannot mean business as usual for Ethiopia-US relations.”

Saturday 26 April 2014

Urgent action: Opposition leaders denied medical treatment (AI)



AI – Olbana Lelisa and Bekele Gerba are being denied medical treatment. The two men, political opposition leaders and prisoners of conscience, are reported to be ill in Kaliti prison, Ethiopia. Olbana Lelisa’s friends believe his condition may be life-threatening.
Several months ago Olbana Lelisa and Bekele Gerba were moved from Ziway prison south of Addis Ababa, to Kaliti prison on the outskirts of the capital city, reportedly after a doctor in Ziway referred the two men for hospital treatment.
However, since the transfer, the men have been denied access to a hospital. It is not clear what is wrong with the wo men as they have not access to a full diagnosis. continue reading...

Six Members of Blogging Collective Arrested in Ethiopia (globalvoices)

zonenine
Six bloggers arrested on April 25 in Addis Ababa. Photos from Facebook, assembled by Endalk.
On April 25, six members of the Zone Nine blogging collective [am] were arrested in Ethiopia. Allies report that they are now being held at Maekelawi, a detention center in Addis Ababa, the nation’s capital.
News of the arrests first broke on Twitter, where fellow bloggers and social media users voiced support for those arrested and expressed their own fears about what may be to come.
Formed in 2012, the Zone Nine group has leveraged significant critiques of ruling government policy and practice. We have managed to conduct online campaigns in an effort to raise awareness about political repression in the country. We are also dedicated to translating international news for local audiences — through our partnership with Global Voices, we launched Global Voices in Amharic two years ago.
We believe we have been a surveillance target of the Ethiopian government since the death of the Prime Minister Meles Zenawi. We have written critical articles about Zenawi’s so-called economic development and other achievements. While he received favourable reports we have shown his achievement is dubious
As of today, no charges had been issued to the members of our group who were arrested today.
Unfortunately, these arrests are not the first of their kind. In the suburbs of Addis Ababa, there is a large prison called Kality where many political prisoners are currently being held, among them journalists Eskinder Nega and Reeyot Alemu. The journalists have told us a lot about the prison and its appalling conditions. Kality is divided into eight different zones, the last of which — Zone Eight — is dedicated to journalists, human right activists and dissidents. When we came together, we decided to create a blog for the proverbial prison in which all Ethiopians live: this is Zone Nine.

Police arrest Blue Party leaders, members ahead of protest rally on Sunday



ADDIS ABABA - Police have arrested key figures as well as dozens of members of the rising opposition Blue Party. The detainees include the party's deputy chairperson as well as several executive committee members. The political detainees are being held at several police stations in the capital.

The arrests were made at least 48 hours ahead of a protest rally Blue Party had organized for Sunday, April 27 in Addis Ababa.

Party chairperson Yilikal Getnet was plucked out of prison by force, after resisting police orders to leave the jail house. Yilkal sought to remain in jail but police said they received no orders to keep him there.

Blue Party is largely a political organization of the youth, who are characterized as non-violent, law-abiding and yet defiant to fight the tyrannical regime to the end.

In the meantime, police have arrested about half a dozen bloggers. No reason was given for the arrest of the activists who are collectively known as 'Zone Nine' bloggers.


The detainees are Atnafu Berhane, Mahlet Fantahun, Zelalem Kibret, Befekadu Hailu, Natnael Feleke, Abel Wabela and journalist Tesfalem Woldeyes.

Thursday 24 April 2014

Ethiopia: Trapped By a Crippled Telecom

By Kalkidan Yibeltal | addisstandard.com

A soaring number of option-deprived customers and eye-watering packages continue to swell the earnings of the state monopoly Ethio telecom. In return the inglorious institution kept on crippling everything this country has achieved in the past with banks being the hardest hit 



ethio_telecom

In February this year, while hosting his third presser with the local media since he assumed office as Prime Minister of Ethiopia, Hailemariam Desalegn was resolute in his response to a question from this magazine on whether or not his government was willing to assess the impact of running a dysfunctional state run telecommunication company on the economy. His government, PM Hailemariam said, was not ready to privatize the telecom sector, “Not now, not in the near future.” Needless to say, that was not the right answer to the question, but it is the incumbent’s long held stand on the state monopoly, Ethio telecom.
The giant service provider is spoiled by grave impairments and is often a source of growing public frustration. Yet a soaring number of option-deprived subscribers especially to mobile phones and its eye-watering packages continue to swell its earnings. In the past six months alone Ethio telecom has amassed some $350 million (7 billion br.) in revenue. Numbers like this corroborate the ruling party’s recurring reference to the sector as a ‘cash cow.’ But it is a cash cow that is wreaking havoc to almost everything this country has achieved in the past two decades, particularly to most of the things the nation’s infant banking sector wanted to accomplish as of late.

Shake off traditional banking, and get stuck with a mediaeval telecom

Three years after the collaps of the military Dergue regime in 1991, the country’s central bank, the National Bank of Ethiopia (NBE), was reconstituted by the Monetary and Banking Proclamation No 83/1994 as an autonomous financial regulatory organ. And more importantly, the subsequent Licensing and Supervision of Banking Business No 84/1994 laid down the legal basis for the participation of the private sector in the banking business. The first privately owned commercial bank, Awash International (AIB), therefore, came into existence shortly afterwards. Today the Ethiopian banking industry comprises of 15 more private and two state owned commercial banks as well as one state owned development bank.
A dynamic move in opening new branches by many of these banks saw a dramatic fall in the bank-branch-to-population ratio from 1: 116, 847 in 2009/10 to 1: 69, 000 in 2011/12. The recent figures indicate the ratio might even be lower than 1: 50, 000, according to a data obtained from the NBE.
However, Ethiopia’s law prohibits foreign nationals from involving in the financial sector, impending, among others, negotiations of accession to World Trade Organization (WTO), a process that has begun as far back as 2003, NBE admits. The toddling domestic banks are not financially, technically and technologically competitive either, compared to the sector in neighboring countries, for example; liberalization of the sector is may be one issue, but it is not everything to it. Cocooned from global banking heavyweights, the localbanks are moving at a snail’s pace towards modern banking trends. There are many reasons for that of which having a dysfunctional telecom system is the giant one.
As part of the NBE’s national payment system, all authorized banks are required to acquire Centralized online Real-time Electronic System (Core banking), which creates an electronic link that enables a given bank’s branches access applications from centralized data centers. So far, about twelve banks have completed the implementation and interface of core banking, NBE told Addis Standard. Five banks have completed the implementation and are in the final stages of interface. The remaining two banks are in the procurement process.

BankNumber of ATMs by a bank (2013)
CBE120
Dashen105
Wogagen27


The state owned Commercial Bank of Ethiopia (CBE), which is going through a massive crusade of branch expansion since the past few years, opened 150 new local bank branches all over the country in 2013 alone, raising the number of its branches to 780 as of the end of the stated year and enabling it to sustain the quasi monopolistic power it holds – some estimate the CBE mobilizes around 80% of the country’s finances.
When the biannual report of CBE for 2013/14 (2005/6 Ethiopian calendar) fiscal year was presented in February this year in the lakeside city of Bahir Dar, the capital of the Amhara regional state 578 km North of Addis Abeba, the bank has announced that 470 of its branches were networked with Core banking solutions technology. It was possible to install 368 Automated Teller Machines (ATMs) and 367 Point of Sale (PoS) machines as well. As of September 30, 2013, the number of banks providing ATM services reached seven, collectively possessing 562 machines. By 2013 Dashen Bank, the pioneer to start the service, has 105 ATMs and 254, 933 cardholders, making it the largest from the private banks in the country. It also offers 780 PoS terminals. Three banks, Awash International Bank (AIB), Nib International Bank (NIB) and united bank, have launched Premium Switch Solutions (PSS) S.C. to help them provide ATM services by deploying shared switch card payment system machines. A forth bank, Berhan International, has joined this group recently while a fifth one, Addis International Bank, is on the way.

After announcing the winning bidder that will supply 100 ATMs and 80 PoS terminals in May 2013, AIB became the second largest from the private banks to operate ATMs and PoS terminals in the country next to Dashen. Some of the ATMs are being installed within bank branches, while the rest, known as lobby ATMs, are being installed in hotels and shopping malls. In theory, customers who hold AIB cards can get the service for free while customers of other banks under the umbrella of PSS will be charged 40 cents for every 100 birr withdrawal. Most banks in Ethiopia do not charge their customers at every ATM withdrawal to encourage the practice.

                   Head to Head
 KenyaEthiopia
No of commercial banks4319
ATMs2205562
Internet penetration9.70.1
Fixed broadband prices as %of GNI P.C49.371




No network no money

Apart from technical problems such as the breaking down of the machines or the deterioration of money notes, currently a major problem facing ATM services in Ethiopia is attributed to network failures, according to a document by the NBE. In the same manner the unreliability of telecom services is put forward as one of the challenges in implementing core banking. In their study titled “Competition in Ethiopian Banking Industry” published on The African Journal of Economics in December 2013, Zerayehu Sime, Kagnaw Wolde and Teshome Ketama maintain “in less monetized countries like Ethiopia, whilst financial sector is dominated by banking industry, effective and efficient functioning of the latter has significant role in accelerating economic growth.” However recent telecom realities appear to make that road to efficiency and effectiveness intolerably bumpy. Customers of banks in Addis Abeba and in major towns throughout the country are well acquainted with the unfortunate times when there is no internet connection at all not only for hours but for days. It is also becoming routine that hundreds of employees had to wait for days to get their salaries. Equally familiar is the sight of customers queuing around a network deprived ATM machine, hoping in despair that it may start working any minute.
The city’s hotels and recreational centers that have helped the service sector contribute to a tune of 46% to the national GDP are unable to host guests because of non-responding PoS machines. Ethio telecom, which has 27 million mobile phone and 4.5 million internet subscribers as of mid February 2014, complains 80% of its network problem is caused by the incessant power cuts, a claim that convinces no one. For starters it is Ethio telecom’s responsibility to prepare abackup power source, something banks are forced to do, according to a banker.
For banks that have interlinked all or many of their branches in core banking system, power outage around the headquarters where the central server is located means unless they have a power backup they are unable to conduct business in all the connected branches. So they set up backup generators, although it means adding extra operational cost. But what they can’t do is have a replacement scheme to run the internet when it is no longer available.Occasionally when the cable networks are problematic, banks use expensive Enhanced Voice-Data Optimized (EVDO) network. But it is not unusual that both the cable and EVDO networks are unavailable at the same time.
An employee of a private bank who requested to remain anonymous told Addis Standard that many banks take three measures to tackle these difficulties. First, in the absence of sufficient information due to their inability to access the central data, branch managers sometimes risk in handling their known customers by offering them basic services without cross checking with their online database.  Second, many banks are forced to look into offline solution, which allows each bank branch to assemble enough data to be able to carry on offering limited services in the absence of connection to the main server. Third, some banks are attempting to strike a deal with Ethio telecom to enable them obtain exclusive network services from the later.

On top a mobile banking?

In a conference titled “Catalyzing Transformation through Technology: How Mobile Financial Services Contribute to the Growth of Ethiopia”, held in early February this year here in Addis Abeba, Dr. Debretsion Gebremichael, Minister of Communication and Information Technology (MCIT), with the rank of Deputy Minister, said that 80% of Ethiopians, currently estimated to be above 90 million, reside in rural areas. “Because of that financial institutions have been unable to reach the majority of these people,”he said. Alternative ways to reach those people must be found, he said, adding it was his government’s belief that cheaper financial services with a better quality can be accessible. But that is an apple pie in the sky; something Ethio telecom can’t bring in as of yet.  In his 2012 study titled “Prospects and Challenges of Private Commercial Banks in Ethiopia,” Simeneh Terefe of the Department of Economics at Unity University identifies lack of appropriate technology and inflation as a major challenge banks in Ethiopia are facing today. In most parts of Africa mobile banking has revolutionized access to finance serving as a virtual bank, a PoS terminal, an ATM and an internet banking terminal all together when need be. In most Sub Saharan Africa, where having bank accounts is not common, mobile banking is offering an opportunity to millions of unbanked people. Unfortunately though, it is a technology bypassing Ethiopia, one of the “fastest growing economies” in Africa, according to World Bank, and a country that is generating “more millionaires” than countries such as Tanzania and Ghana, according to New World Wealth.For now Banks in Ethiopia have set their eyes fixed on bank branch expansion as a way of reaching out to more customers – a costly and ineffective move for financial institutions to venture into. Unfortunately however, the government of Hailemariam Desalegn thinks it is better to keep the ‘cash cow’ as it is than calculating the chaos it imposes on everything this country has achieved from the financial to the service providing industry.

AN URGENT APPEAL – From Mesfin Wolde-Mariam

The UN Human Rights Commission
The African Union Human Rights Commission
The International Red Cross
Amnesty International
Human Rights Watch
And
All Men and Women of GOOD WILL
Reeyot Alemu
Reeyot Alemu
Reeyot Alemu is a budding Ethiopian poet, essayist, and journalist. There are not many Ethiopians of her caliber inside the country. She has been languishing in the famous Ethiopian Prison in Qalliti for almost three years. She was charged of terrorism, a crime she totally abhors. She was sentenced first for eighteen years but later reduced to three.
With the exception of her mother and father, she is not allowed to communicate with anyone, including her sisters, brothers as well as her fiancée.
Reeyot, although constantly in agonizing pain and in need of help, is held in solitary confinement with a very old and sickly foreign woman who herself requires assistance.
Reeyot is suffering from some growth in her breasts. The prison authorities have been reluctant to take her to hospital for medical checkup, even when her parents were prepared to pay the bill. When she became seriously ill she was allowed to see a doctor as a result of which she was taken to the hospital and operated upon. But no sooner had the surgeon finished the operation than she was immediately taken back to prison even before she had fully recovered from the Anastasia.
She now suffers from a relapse on the operated breast and similar growth in her other breast. The prison authorities still demonstrate their reluctance to provide medical treatment even at the expense of her parents.
May God provide the necessary courage to all those institutions and organizations to cry out effectively for this young lady who is suffering at the hands of insensitive prison administration.

Wednesday 23 April 2014

እውቅና የተሰጠው የሚያዚያ 26ቱ የአንድነት ሰልፍ በደህንነቶች ትእዛዝ እውቅና ተነፈገ

አቡጊዳ


ከአዲስ አበባ የደረሰን ዜና እንደሚጠቁመው፣ የአንድነት ፓርቲ ሚያዚያ 19 ሰልፍ ለማድረግ ቢጠይቅም፣ የፖሊስ አዛዞች በዚያን ቀን በቂ ጥበቃ ማዘጋጀት አንችልም በማለታቸው፣ አስተዳደሩ ሚያዚያ 26 ቀን እንዲደረግ ጠይቆ የነበረ ሲሆን፣ ለሚያዚያ 26 የእውቅና ደብዳቤ ለመዉሰድ ወደ አስተዳደሩ ጽ/ቤት ያመሩት የአንድነት ከፍተኛ አመራሮች፣ የእውቅና ደብዳቤ ሳይቀበሉ መመለሳቸውን ያነጋገርናቸው የአንድነት አመራር አባል ገለጹ።
የአስተዳደሩ ሃላፊዎች፣ ከደህንነት ጽ/ቤት ለአንድነት ሰልፍ እውቅና እንዳይሰጡ በቀጥታ መታዘዛቸዉን የገለጹት የአንድነት አመራር ፣ አዲስ አበባ በከንቲባው ሳይሆን፣ የአዲስ ሕዝብ ባልመረጣቸው ከበስተጀርባ ሆነው በሚፈልጡና በሚቆርጡ ጥቂቶች መዳፍ ስር የወደቀችና በአምባገነኖች የምትገዛ መሆኑን አመላካች ነው ብለዋል።
አንድነት ፣ ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ፣ ሰልፍ ለማድረግ በአገዛዙ እውቅና ያልተሰጠበት የሚያዚያ 26 ቀኑ፣ አራተኛው ቀን ሲሆን፣ ከፋሲካ እሁድ ዉጭ ባሉ ሶስት እሁዶች ፣ መጋቢት 28፣ ሚያዚያ 5 እና ሚይዚያ 19 ቀንም ሰልፍ ለማድረግ ተጠይቆ በደህንነቶች ትእዛዝ እውቅና አለመሰጠቱ ይታወቃል።
ከሰልፍ ጋር በተገናኘም የአዲስ አበባ አስተዳደር ሚያዚያ 19 ቀን ሰልፍ ለማድረግ አንድነት ፓርቲ ጠይቆ እውቅና አልሰጥም ቢልም፣ ለአንድነት በተከለከለበት ቀን ለሰማያዊ ፓርቲ እውቅና እንዲሰጥ የደህንነት ሃላፊዎች መመሪያ መስጠታቸውን፣ በአዲስ አበባ ያሉ ምንጮቻችንን በመግለጽ መዘገባችን ይታወቃል።
በአንድነት ፓርቲ ላይ እየተደረገ ያለው ሕግ ወጥ እርምጃ፣ ከአስተዳደሩ ዉጭ ያሉ የደህንነት ሃላፊዎች፣ በቀጥታ የአስተዳደሩ የሰማያዊ ሰልፍ ፍቃድ ኦፊሰር የሆኑትን፣ አቶ ማርቆስን ፣ በማዘዝ እየፈጸሙት ያለ አሳዛኝ ተግባር እንደሆነ የገለጹት የአንድነት አመራር፣ ከከንቲባው ጽ/ቤት ሃላፊዎች ጋር የፓርቲዉ ከፍተኛ አመራሮች ችግሮችን ለመፍታት በስፋት እንደተነጋገሩ ገልጸዋል። አንድነት ሚያዚያ 19 ቀን ጠይቆ ፣ «ሌላ ዝግጅት አለ። በቂ ጥበቃ የለም» በሚል ሚያዚያ 26 ማድረግ እንደሚቻል እንደተነገራቸው የገለጹት የአንድነት አመራር፣ አሁን ሌሎች ድርጅቶች በሚያዚያ 19 ሰልፍ እንዲጠሩ እውቅና ለመስጠት መዘጋጀቱ፣ በቂ ጥበቃ ከየት ሊገኝ ቢችል ነው በሚል የአስተዳደሩን ሃላፊዎች ጠይቀዋል።
የአስተዳደሩ ሃላፊዎች ጉዳዩን ተከታትለው፣ ነገ ሚያዚያ 15 ቀን እንደሚያሳውቋቸው መግለጻቸዉን፣ የሚናገሩት የአንድነት አመራር አባል፣ አስተዳደሩ መጀመሪያ ለጠየቀዉ ፓርቲ፣ አስፈላጊዉን ቅድሚያ እንደሚሰጥና ሕግን አክብሮ በሕግ የተደነገገለትን ሃላፊነት እንደሚወጣ፣ ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል።
በሃያ ሶስቱም የአዲስ አበባ ወረዳዎች በመቶዎች የሚቆጠሩ አባላትና ደጋፊዎች እንዳላቸው የገለጹት የአመራር አባሉ፣ አስተዳደር እውቅና ሰጠ አልሰጠም፣ በቅርብ ቀናት ዉስጥ ለሚያዚያ 19 ይሁን ሚያዚያ 26 ቅስቀሳ እንደሚጀምር አሳወቀዋል።
አገዛዙ የዜጎችን መብት ማፈን እንደማይችል ያስረዱት አመራር አባሉ፣ አንድነት በሰለጠነና በመግባባት ፖለቲካ ቢያምንም፣ ሕግ መንግስቱ የሚደነግግለት መብት ላይ እንደማይደራደር አረጋግጠዋል። «ሰልፉ ይደረጋል። ጥያቄዉ ፖሊስ ሕዝብን ይጠብቃል ወይንስ ከሕዝብ ጋር ይጋጫል? የሚለው ነው» ሲሉ ነበር የአንድነት ቁርጠኝነት ለማሳየት የሞከሩት።
ፓርቲዉ በዚህ ረገድ፣ እየትሰራ ያለዉን ደባ ለማጋለጥና ሕዝብ አጥርቶ እንዲያወቀው ለማድረግ፣ በመረጃ ላይ የተደገፈ መግለጫ እንደሚሰጥም ለማወቅ ችለናል።
የአዲስ አበባ አስተዳደርና አንድነት ከመግባባት ደረጃ ደርሰው፥ የታቀደው ሰልፍ ሕጉን በጠበቀ መልኩ ሚያዚያ 19 ይሁን ሚያዚያ 26 ይደረግ እንደሆነ፣ ያ ካልሆነ ደግሞ የአንድነት ፓርቲ ዉሳኔ ምን እንደሚሆን ተከታትለን ለማቅረብ እንሞክራለን።

ህወሓት እስከመቼ ደም ማፍሰሱን ይቀጥላል ?


ሀገር የመገንጠል ዓላማ ይዞ የተነሳው የህወሓት ጁንታ በስውር እና በአደባባይ የጫካ ልማዱን መሰረት አድርጎ ሲገድል መኖሩ አዲስ ባይሆንም ከሰሞኑ መረር ያለ እርምጃ ‹‹ግድያ›› ማሰቡን ከጓዳው የወጣ የወሬ ምንጭ ደረሰን፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ አስተዳደር ጽ/ቤት ተገኝቼ ነበር፡፡ የመገኘቴ ዓላማም የፊታችን እሁድ ሚያዚያ 26 የሚደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ የዕውቅና ደብዳቤውን ለመስጠት የተያዘውን ቀጠሮ በማክበር ነበር፡፡ የሰላማዊ ሰልፍ እውቅናን በተመለከተ ኃላፊ የሆኑት አቶ ማርቆስ ፎርም እንዲሞላ አዘዙ፤ የተባለውን ፎርም ሞላን፤ ያን ጊዜ የአቶ ማርቆስ የቢሮ ስልክ አንቃጨለ፤ አነሱት ……ቀጭን ትዕዛዝ ከወዲያ ማዶ…………… ‹‹የአንድነትን ሰላማዊ ሰልፍ በተመለከተ ዕውቅናው እንዳይሰጥ ይቆይ›› አቶ ማርቆስ ፊቱ ተለዋወጠ ‹‹ ይቅርታ አድርግልኝ የኔ ችግር አይደለም›› ሌላ ቃል ካፉ አልወጣም፡፡Ato Habtamu Ayalew (UDJ)
አልገባኝም ….ቀጠልኩ ….የአንድነት ሰላማዊ ሰልፍ ተከለከለ እያልከኝ ነው ? መለሰ …..እኔ ምን ላድርግ ? …..የከለከለው ማነው የበላይ ኃላፊ ነው ? አዎ አጭር መልስ፡፡ ትቼው ወደ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊው አመራሁ፤ ስብሰባ ላይ ናቸው፡፡ ወደ ፓርቲ ጽ/ቤት ደውዬ ሁኔታውን አሳወኩ የፓርቲው ፕሬዘዳንት ኢንጅነር ግዛቸውን ጨምሮ በርካታ አመራሮች ፈጥነው ደረሱ፡፡ የአስተዳደሩ ስብሰባም ለሻይ እረፍት ተቋርጦ ኃላፊው ወደ ቢሯቸው ሲገቡ ተከታትለን ገባን፡፡ ላለማናገር ጥቂት አንገራገሩ የቢሯቸውን በር አንቀን አናግሩን በማለት ጸናን፡፡ ‹‹ምንድነው ችግሩ የሰልፉ ጉዳይ ከሆነ ጨርሰናል፤ እውቅናውን ወሰዳችሁ አይደለም›› ባጭሩ መልስ ተሰጣቸው ፤ አልወሰድንም የአቶ ማርቆስ መልስ ተከልክሏል የሚል ነው፡፡
ጥያቄ አስከተልን ……እርሰዎ መረጃ የለዎትም ? መንግስታዊ ኃላፊነቱ የርስዎ ነው፤ ማነው ከልካዩና ፈቃጁ ? መልስ የለም ጥቂት ዝም ብለው ‹‹የጠየቃችሁን ሚያዚያ 19 ለማድረግ ነበር፡፡ በዚያ ቀን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የጥበቃ እጥረት አለብኝ በማለት ስላመለከተ የእናንተ ሰልፍ ለሚያዚያ 26 እንዲደረግ ጠየቅናችሁ ተስማማን ከዚህ ውጪ የተደረገ ነገር ካለ በኔ በኩል መረጃ የለኝም ማን እንደከለከለ አናውቅም›› ስለዚህ ይህንን ከተማ ከንቲባው ካልሆነ ማን ነው የሚመራው? ከወዲያ ማዶ መልስ የለም……….ስልክ አነሱ እና አቶ ማርቆስን ወደ ቢሯቸው ጠሩ ሰውዬው መጡ ማጣሪያ ተጠየቁ መመሪያ ደርሶኛል ሲሉ ለከንቲባው ጽ/ቤት ኃላፊ በኛው ፊት ተናገሩ፡፡ መመሪያ ሰጪው ማነው? ወደ አንዱ ቢሮ ዘው ብለን አንድ ሰው አናገርን ……….. ‹‹እባካችሁ ይቅርባችሁ ደህንነቶቹ የሚውሉት እዚህ ግቢ ነው፡፡ አንድነቶች ከወጡ እርምጃ ይወሰድ ሲሉ ሰምቻለሁ›› አለን በማንሾካሾክ ድምጽ ………….
ጎበዝ ይሙት ሰነፍ ይኑር ቢሻው
አተላ መሸከም ይችላል ትከሻው
ፍርሃት ማነው ቢሉኝ ስሙን አላውቀውም
ሞትን በቁሜ እንጂ ሞቼ አልጠብቀውም፡፡
ህወሓት ሊተኩስ ተዘጋጅቷል እኛም የነሱን ጥይት የሚሸከም ደረት …….እመነኝ ካልገደሉ አያቆሙንም፡፡፡

አቶ ሀብታሙ አያሌው UDJ

Monday 21 April 2014

Stop military aggression against civilians in Afar Region of Ethiopia!

Afar People’s Party (Qafar Ummattah Party)
PRESS RELEASEAfar People’s Party's logo
The ongoing atrocities committed by the TPLF/EPRDF regime are reaching the limit in Ethiopia in general and that of the Afar region in particular. April 20, 2014 the regime instigated conflict flared around Awash killing 12 Afar civilians. This act of state terror was committed by the federal polis. Outraged by this act of terror, the civilians in Awash blocked Addis Ababa-Djibouti road causing stop for all gods coming from Djibouti port demanding the of removal corrupt army from the locality. Likewise, in March 2014 the militia of the Tigray Region besieged Konnaba district in North West of the Afar Region, which also ended in blocked road to Tigray Region until today. As usual, the Afar regional officials seem to be paralyzed to act on behalf of the Afar civilians. Hence, TPLF/EPRDF regime and its army should be held accountable for the brutal crime against humanity. Since Woyane seized power in Ethiopia, the Afar population is harassed, humiliated and hundreds of them have been killed by the army throughout these years.
In addition, displacement of thousands of Afar pastoralists continues due to land grabbing for Woyane affiliated investors in vicinities Afdera, Dallol, Teru and along the Awash Valley. The pastoralists have been evicted to desert areas without access to water and other facilities. Afar People’s Party condoms the killing of the civilians, forced displacement, land grabbing, social injustices with strongest possible terms. Afar People’s Party also shares the concerns of Horn of African analysts who indicate that the situation in the Afar region could lead to a civil war and destabilize Ethiopia. We encourage the civilian to continue their peaceful demonstrations to denounce the state terror in different places for the coming two weeks.
  • We call on the army to immediately end the act of terror on civilian!
  • We call on Amnesty International and Human Rights Watch and Journalists to investigate the situation in Afar regional state.

ቴሌፎኑ ‘ለግዜው’ ጥሪ አይቀበልም

ክንፉ አሰፋ
“የደወሉላቸው ደምበኛ ለግዜው ጥሪ አይቀበሉም።…” የምትለዋ አሰልቺ የቴሌ መልእክት ያላጋጠመው ቢኖር ወደ ኢትዮጵያ ስልክ ደውሎ የማያውቅ ሰው ብቻ መሆን አለበት። ኮ/ል መንግስቱ ሃይለማርያም ወደ ቀድሞ ወዳጆቻቸው መደዋወል ጀመሩና በመሃል ተስፋ ቆረጡ አሉ። አስር ለሚያህሉ አርሶአደሮች እና የሰራዊቱ አባላት ዘንድ ደውለው አልተሳካለቸውም። ለሁሉም ጥሪ ያገኙት ምላሽ “የደወሉላቸው ደምበኛ ለግዜው ጥሪ አይቀበሉም።” የሚል ሲሆንባቸው ራሳቸውን ነቀነቁ። ሰው ሁሉ የጨከነባቸው መሰላቸው። እንዲህም አሉ። “የሃገሬ ሰው እንኳን የስልክ ጥሪ፤ የእናት ሃገር ጥሪስ መች ተቀበለ።”
ለአመታት በተከታታይ በሁለት ድጅት እያደገች ያለች ሃገር የስልክ መስመር ችግር ይገጥማታል ብሎ ማሰብ ይከብዳል። ችግሩን በደንብ ላልተረዳው፣ ሰው የሞባይል ስልክ የሚገዛው እንዲሁ ይዞ ለመታየት ነው ያስብል ይሆናል። ይህ አባባል በከፊል ትክክል ነው። ዘመናዊ ስልክ በመያዝ ለላንቲካነት ብቻ የሚጠቀሙበት ሰዎች አይጠፉም። የቻይናው ቀፎ ከሞዴል አርሶ አደሮች አልፎ ተራው አርሶ-አደር እጅ ላይም ገብቷል። አብዛኞቹ ግን ተንቀሳቃሽ ስልካቸውን አይጠቀሙበትም። ለዚህም ይመስላል በርካታ ተንቀሳቃሽ ስልክ የሚይዙ ሰዎች እንዲሁ ለእይታ እና ለላንቲካ ብቻ የሚመስላቸው። አገልግሎቱን በተመለከተ ግን 99 በመቶ የሚሆነው ችግር የመዋቅር ችግር ነው።
ለዓውዳመቱ ወደ ኢትዮጵያ ስልክ የደወላችሁ ካላችሁ፤ ይህ ነገር እንደገጠማችሁ እርግጥ ነው። ዘንድሮ ደግሞ ቴሌ ከፍቷል። የሞባይሉ መስመርማ እንደ አይን እልም ብሎ ነው የጠፋው። ከበርካታ ሙከራ በኋላ መስመር ያገኘ ሰው ካለ በደስታ ይዘልላል። የተቀባዩም ስልክ ካቃጨለ ተዓምር ነው የሚባለው። ከርማ ብቅ እንደምትለው የአዲስ አበባ መብራት… ልክ እንደ ቧንቧ ውሃ፤ ስልኳም “መጣች – መጣች!” ብሎ መጨፈሩ አይቀርም።Ethio Telecom the worst service in Africa
“እንኳን አደረሳችሁ!” ለማለት እኔም ወደ ሃገር ቤት ስልክ መታሁ።
“የደወሉላቸው ደምበኛ ለግዜው ጥሪ አይቀበሉም።” የሚል መልስ ነበር ያገኘሁት። ለሁለተኛ ግዜ ስሞክር ደግሞ “የደወሉት ስልክ ለግዜው ከአገልግሎት መስጫ ክልል ውጪ ነው።” የሚል ምላሽ አገኘሁ። ደቂቃ ባልሞላ ግዜ ውስጥ ጥሪ ያማይቀበለው ስልክ ከአገልግሎት መስጫ ክልል መውጣቱ አስገረመኝ። ተስፋ ሳልቆርጥ ደገግሜ ሞከርኩ። ቢያንስ ከአስር ግዜ ሙከራ በኋላ፤ መስመር አገኘሁና ሎተሪ የወጣልኝ ያህል ተሰማኝ።
ደስታዬ ግን ብዙም አልዘለቀም። በመሃል እንግዳ ነገር ተፈጠረ። ስልኩን የተቀበለኝ የደወልኩለት ሰው አልነበረም። የተፈጠረው ክስተት – ባለንበት የመረጃ ዘመን እንደ 17ኛው ክፍለዘመን “ቴሌ በኦፐሬተር መስራት ጀመረ እንዴ?” ያሰኛል። ነገሩ ግን ሌላ ነው። ስልኩን ያነሳው የተለመደው የስልክ ጠላፊ ስለመሆኑ አንዳች ጥርጥር አልነበረኝም። ሶማሌያውያን መርከብ ሲጠልፉ ጸሃዩ መንግስታችን ደግሞ የስልክ ፓይረት መሆኑን ሂዩማን ራይትስ ዎች በዚያን ሰሞን ነግሮን ነበርና።
ውጭ ሃገር ያለ ኢትዮጵያዊ ዘመድ ለመጠየቅ መደወሉ አይቀርም። ተስፋ የማይቆርጥ፤ ደጋግሞ ይሞክራል። እንደ እድል የስልኩን መስመር ካገኘ ደግሞ ሌላ ችግር ይገጥመዋል። ዘው ብለው የሚገቡ የስልክ ጠላፊዎች መስመሩን ያውኩታል። ሌላው አማራጭ ደግሞ አጭር የጽሁፍ መልእክት ነው። በኢትዮጵያ ቴሌኮም አጭር መልእክት ከመላክ ይልቅ ደብዳቤ ጽፎ በፖስታ መላኩ እየፈጠነ መጥቷል። አጭር መልእክት የሚደርሰው ከቀናት ብኋላ ነው። ከላኪው ዘንድ መልዕክቱ መድረሱ ቢረጋገጥም ተቀባዩ ጋ ጨርሶ ላይደርስም ይችላል።Ethiopian telecommunication
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በቅርቡ በሰጡት ጋዤጣዊ መግለጫ “የኢትዮጵያ ቴሌኮም ቴክኖሎጂ ከዴንማርክ፣ ከኖርዌይ እና በከፊል ከእንግሊዝ ቴክኖሎጂ ጋር አንድ ነው” ብለው ነበር። በዚህ መግለጫቸው አቶ ሃይለማርያም የኢትዮጵያን የኢንተርኔት አገልግሎት፣ እንዲሁም የስልክ መስመሩ ጥራት እና አስተማማኝነት በደንብ አድርገው ነበር “ለጋዜጠኞቹ” የገለጹላቸው። ይህን ተናግረው እንዳበቁ ግን የራሳቸውም ስልክ መጠለፉን ሰማን። ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው እንዲሉ አልሰሙት ይሆናል እንጂ፤ “እኛ ሲም ካርድ፤ አንተ ደግሞ ቀፎ ነህ!” ይሏቸዋል – ከላይና ከታች ያሉ አለቆቻቸው።
የኢትዮጵያን ስልክ አገልግሎት ከዴንማርክ፣ ኖርዌይ እና እንግሊዝ ጋር አወዳድረው ማወደሳቸው ግን ራሳቸው ካዴሬዎቹንም ሳይቀር ሳያሰፍራቸው አልቀረም። ሰውየው የኢትዮጵያን ቴሌኮም እያወዳደሩ ያሉት 99.9 በመቶ ሳያቋርጥ አገልግሎት ከሚሰጠው አራተኛው ጀንሬሽን የምእራቡ ቴክኖሎጂ ጋር ነው። መቼም ሁሉም ይዋሻሉ። ነብሳቸውን ይመርና አቶ መለስ ዜናዊም ይዋሹ ነበር። ለዛ ያለው ውሸት አለ። እጅ፣ እግርና አይን የሌለው ውሸትም አለ። እንዲህ አይነት ያፈጠጠ ውሸት ግን እመራዋለሁ የሚሉትንም ሕዝብ እንደመናቅ ይቆጠራል። እኚህ ሰው የሞራል እሴታቸውን ሁሉ አሽቀንጥረው ሊጥሉት ይችሉ ይሆናል። ምሁራዊ ግብአታቸውንም ለተራ ፖለቲካ ጥቅም ሊያስወግዱት ይችላሉ። እምነታቸውስ እንዲህ አይነቱን ቅጥፈት ይፈቅድላቸው ይሆን?
የቴሌ የኢንተርኔት አገልግሎት የመንግስት አልባዋ ሶማልያን አንድ መቶኛም። ኮሜዲያን ክበበው ገዳ እንደቀልድ የነገረኝ ቁም-ነገር የኢትዮጵያን ኢንተርኔት ፍጥነት በደንብ ይገልጸዋል። ክበበው ሰሜን አሜሪካ የስራ ጉብኝቱ ወቅት ፎቶ ተነስቶ ለቤተሰቡ በኢሜይል ይልካል። የላከው ፎቶ መድረሱን ለማረጋገጥ በነጋታው ወደ አዲስ አበባ ደወለ።
“ፎቶ ደረሰ?”
“አልደረሰም!”
ሌላ ቀን እንደገና ደውሎ የላከው ፎቶ እንዳልደረሰ ተነገረው። ለሶስተኛ ግዜ ደውሎ ኢሜይሉ እንደደረሰ ጠየቀ። አሁንም አልደረሰም ተባለ። እንዲህ እያለ ሳምንት ሞላው።
“በሳምንቱ እኔ ቀድሜ ደረስኩ።” ነበር ያለው ክበበው።
የኢሜይል መልእክቱ መድረሱ ከተረጋገጠ በኋላ – ሌላ ችግር ገጠመው። ኢሜይሉ ሲከፈት ግማሽ አካሉን ነበር የሚያሳየው። ፎቶው እስኪያወርድ (ዳውንሎድ እስኪያደርግ) ደግሞ ግማሽ ቀን መፍጀቱ ግድ ነበር።
ይህንን አገልግሎት ነው አቶ ሃይለማርያም ከምእራቡ አለም አገልግሎት ጥራትና ፍጥነት ጋር እያወዳደሩ የሚነገሩን። በአስር ሜትር ርቀት ላይ ሆኖ በስልክ መገኛኘት ህልም በሆነበት ሃገር፤ ስለ ስልክ ጥራት መናገር ቅጥፈት ብቻ ሳይሆን የሰውየውንም የሞራል ውድቀት ያመላክታል።
የኢትዮጵያ ቴሌኮም ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ቀጥሎ ትልቅና ግዙፍ የሃገሪቱ ተቋም ነው። እድገቱ ግን ያሳዝናል። በአስር አመት ግዜ ውስጥ ብቻ እንኳን እድገቱ በ75 በመቶ ቁልቁል ወርዷል። ለዚህ ዋናው ምክንያት ተቋሙ አገልግሎት መስጠቱን አቁሞ ወደ ስለላ ተቋም መቀየሩ ነው። ባለፈው ወር ይፋ የሆነው ባለ 100 ገጹ የሂዩማን ራይትስ ዎች ዘገባ ይህንን መንግስታዊ የስልክ እና የኢንተርኔት ጠለፋ አረጋግጧል።
“የተቃዋሚ ፓርቲ አባል የነበረን አንድ ዜጋ አፍነው ካሰሩት በኋላ ውጭ የተደዋወለበትን የስልክ ቁጥር ዝርዝር አሳዩት።” ይላል ተቀማጭነቱ ዩናይትድ ስቴትስ የሆነው አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋም። ሰውየው የታሰረው ያልተከፈለ የስልክ ሂሳብ ኖሮበት አልነበረም። ባለስልጣናቱንም አላማም፣ ወይንም መንግስትን በሃይ ለመገልበጥ አላሴረም። ወንጀሉ፤ ከውጭ ሃገር ስልክ ስለተደወለለትና ከወዳጅ ዘመዶቹ ስለተወያየ ብቻ ነበር። ይህ ደግሞ ፍጹም እንግዳ ነገር ነው። ከተለምዶ ልማታዊ መንግስት አስተሳሰብም እጅግ የከፋ!Ethiopian telephone survive the worst in the world
የዜጎች ሁሉ ስልክ በቴሌ በኩል ይጠለፋል። እንደ ስካይፕ እና ቫይበር ያሉ የቮይስ ኦቨር ስልኮች ደግሞ ፊን ፊሸር በተባለ የኮምፒዩተር ቫይረስ አማካኝነት ይጠለፋሉ። በዚህ አይነት በዜጎች የግል ህይወት ሳይቀር እየገቡ ቴሌን ሙሉ በሙሉ የስለላ ተቋም አደረጉት።
ሞባይል ስልክ እና ኢንተርኔት በአፍሪካ አህጉር በእጅጉ እየተስፋፋ ይገኛል። ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከሆነ 30 በመቶ የሚሆነው የአፍሪካ ህዝብ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጠጠቃሚ እየሆነ መጥቷል። በኢትዮጵያ ግን የስልክ እና የኢንተርኔት ተጠቃሚው ከ2.5 በመቶ አልዘለቀም። ጎረቤት የሆነችው የኬንያ ህዝብ 40 በመቶ የዚህ አገልግሎት ተጠቃሚ ነው። መንግስት አልባዋ ሶማልያ እንኳን፣ ስድስት የቴሌፎንና ስልክ አቅራቢ ኩባንያዎች አሏት። የሶማልያ ህዝብ ጥራት ያለው የስልክ መስመር እና ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚ ከሆነ ሰንበትበት ብሏል። በኡጋንዳም የዚህ አገልግሎት ሰጪ በመንግስት ሞኖፖሊ ስር አይደለም። ከሰባት በላይ የግል ኩባንያዎች እየተፎካከሩ ፈጣን አገልግሎት እየሰጡ ጠተቃሚውን ህዝብ ወደ 50 በመቶ አድርሰውታል።
ያለነው በመረጃ ዘመን ነውና ያለመረጃ እና ያለ መረጃ ቴክኖሎጂ እድገት አመጣለሁ ማለት ዘበት ነው የሚሆነው። የኢትዮጵያ ሁኔታ ግን ሃገሪቱን ወደ መረጃ ሳይሆን ወደ ጨለማ ዘመን ነው እየመራት ያለው። እንድምናነበው ከሆነ የኢትዮጵያን ቴሌኮም ለማስፋፋት ከሶስት ቢሊየን ዶላር በላይ ወጪ ሆኗል። ይህ ገንዘብ በትክክል ስራ ላይ ቢውል አባይንም ይገድባል። ለዚህ የእድገት ሳይሆን ይልቁንም የጥፋት ጎዳና ተባባሪ የሆነቸው ቻይናም በውጭ ምንዛሪ እየተከፈላት ቴሌን ብቁ የስለላ ተቋም አድርጋዋለች። የኢኮኖሚ ልማትና ትብብር ሚኒስትሩም ከተለያዩ የኢንዱስትሪ ሃሮች ጋር በመተባበር የቴሌ ጥራት ላይ ሳይሆን የሚሰራው የስለላ ሃርድዌር እና ሶፍትዌር ማስገባቱ ላይ ነው።
የሃገሪቱ ግብር ከፋዮች ገንዘብ መልሶ ራሳቸውን እንዲያፍን መደረጉ እጅግ ያሳዝናል።
የቴሌ መልስ መስጫ ላይ ያለው መልዕክት ግን መሻሻል አለበት። “ለግዜው” የሚለው ቢቀየር ድርጅቱን ከሃሜት ያድነዋል። እናም መልእክቱ እንዲህ ነው መሆን ያለበት፣
“የደወሉላቸው ደምበኛ ‘ለሁልግዜ’ ጥሪ አይቀበሉም። ..”
ከዚያ በኋላ ደዋዩም ተስፋ ቆርጦ መደወል ያቆማል።