Wednesday 29 July 2015

ኦባማ የአፍሪካን ገዢዎች እያዋዛ ደቆሳቸው! – መስፍን ወልደ ማርያም




ኦባማ በአፍሪካ ኅብረት ያደረገው ንግግር ብዙ ጥያቄዎችን መልሷል፤ የኦባማ ጉብኝት ያስከተለው ጫጫታ ሁሉ መልስ አገኘ፤ የሰው ልጆች በመሀከላቸው ምንም ዓይነት የአድልዎ ልዩነት ሳይደረግባቸው በሰውነታቸው ብቻ በተፈጥሮ ያገኙትን ክብራቸውንና መገሣቸውን አስከብረው መኖር እንዳለባቸው በአጽንኦት ተናገረ፤ ዛሬ የአሜሪካኑ ፕሬዚደንት ያደረገው ንግግር ከፕሬዚደንትና ጠቅላይ ሚኒስትር ጀምሮ እስከፖሊሶች፣ መርማሪዎችና አዛዦቻቸው፣ እስከጦር ኃይሉና አዛዦቻቸው፣ አስከዓቃብያነ ሕግና ዳኞች፣ እስከወህኒ ቤት ጠባቂዎችና አዛዦች በየሥልጣን ተዋረዱ ላይ ሆነው የኢትዮጵያውያንን የሰውነትና የዜግነት እኩልነት አፈራርሰው በጎሣ መሠረት ላይ ሊበታትኑት የሚሞክሩትን በኃይለኛ ቃላት ከመሬት በታች ከቶአቸዋል፤ ማሰብና ማስተዋል የጎደለው፣ ከአፍንጫ የራቀ አመለካከት የሌለበት፣ አገርን የሚያጠፋ፣ ከሰውነት ጎዳና የሚያወጣ የድንቁርና መንገድ መሆኑን ገልጧል፡፡


ኦባማ የኢትዮጵያን ገዢዎች ብቻ ሳይሆን የአፍሪካን ገዢዎች በሙሉ አላግጦባቸዋል፤ በሥልጣን ላይ ሙጭጭ በማለታቸው፣ በሙስናቸው፣ በአፈናቸው፣ ልክ ልካቸውን ሲነግራቸው እፍረታቸውን ውጠው ያጨበጭቡለት ነበር፤ የአፍሪካ ገዢዎች ሕጉን እንደፈለጉ የሚጠመዝዙትን መሳቂያ አድርጓቸዋል፤ በአዳራሹ ውስጥ የነበሩ ወጣቶች የኦባማን ንግግር በማድነቅ በጭብጨባና በጩኸት ይገልጹ ነበር፤ ለወግ ብቻ የሚደረግ ምርጫ የዴሞክራሲ መግለጫ አይሆንም አለ፤ ዴሞክራሲ ነጻና ትክክለኛ ምርጫን፣ ሀሳብን በነጻነት መግለጽን፣ በነጻነት መደራጀትንና መሰብሰብን ያካትታል፤ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድረጅቶችን ማገድና መገደብ ለዴሞክራሲ እንቅፋትና ለእድገት ጸር ነው፡፡

አገዛዞች ነጻነትን በማፈናቸው ሁለት ዋና ዋና የማኅበረሰብ ዓምዶችን ማለትም ደኅንነትንና ሰላምን ያጣሉ፤ ሰላምና ደኅንነት ሰጠፋ ማኅበረሰቡ የጉልበተኞች መጫወቻ ሆኖ ይደናበራል፤ ይህ አደገኛ ጉዞ ነው፤ መልካም አስተዳደር ከሰፈነ ሽብርተኛነት የሚበቅልበት መሬት አያገኝም፤ ሰዎች ሁሉ በሰውነታቸውና በዜግነታቸው እኩልነት ሰብአዊ መብቶቻቸው ሁሉ ከተከበሩላቸው ወደኃይል እርምጃ የሚወስደውን መንገድ የሚከተሉበት ምክንያት የለም፤ እድገት የነጻነትና የዴሞክራሲ ውጤት ነው፤ ነጻነት የሰው ልጆች ሁሉ ዓላማ ነው፡፡

ማንም ቢሆን ከሕግ በታችና ለሕግ ተገዢ መሆን አለበት፤ ሕገ መንግሥቱን ለእሱ እንደሚበጀው እያደረገ በመተርጎም በሥልጣን ላይ መቆየት አይቻልም፤ ሊፈቀድም አይገባም፤ በአጠቃላይ አባማ በአፍሪካ ኅብረት በአደረገው ንግግር የአፍሪካ ገዢዎችን ሁሉ ቁስላቸውን በአልኮል ሲያጥብላቸው እየለበለባቸው ተመልክተውታል፤ አዳምጠውታል፤ አንዳንዶቹም እያፈሩ አጨብጭበውለታል፡፡

የዚህ ንግግር የመጨረሻው ግብ ያልገባቸው የአፍሪካ ገዢዎች ክፉ ነገር ይጠብቃቸዋል፤ በሽብርተኛነት መነገድ መልኩን ሊለውጥ ነው፤ ካላወቁበት የማያውቁት ሽብር ቤታቸውን ይጠርግላቸዋል!

Tuesday 21 July 2015

የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች መቃወሚያ ውድቅ ተደረገ


• ለነሀሴ 14/2007 ዓ.ም ለብይን ተቀጥረዋል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

በእነ ዘላለም ወርቃገኘው የክስ መዝገብ ከ1-6ኛ እንዲሁም የ9ኛ ተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት ተማም አባቡልጉ በደንበኞቻቸው ላይ በቀረበባቸው የክስ ማስረጃ ላይ ያቀረቡት ባለ 10 ገፅ መቃወሚያ በፍርድ ቤቱ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ ተደርጓል፡፡ ጠበቃው ተከሳሾቹ ሀምሌ 1/2006 ዓ.ም ተይዘው ከሶስት ወር በኋላ ጥቅምት 7/2006 ዓ.ም ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት ተገኘ የተባለ መረጃ ከአቃቤ ህግ ማስረጃዎች ማስረጃ ዝርዝርነት እንዲወጣ፣ ተከሳሾቹ ለፖሊስ መረጃ የሰጡበት መንገድና ፖሊስ የሰነድ ማስረጃዎችን የያዘበትን መንገድም አቃቤ ህግ ህጋዊ መሆኑን ስላላረጋገጠ በደንበኞቼ ላይ በማስረጃነት እንዳይያዝ ሲሉ መቀወወሚያ አቅርበው ነበር፡፡

ከተከሳሾቹ መካከል በዛሬው ችሎት አንደኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ‹‹መቃወሚያው የቀረበው ከተከሳሾች እጅ ተገኙ የተባሉት ማስረጃዎች በህጋዊ መንገድ የተገኙ ስለመሆናቸው አቃቤ ህግ በማስረጃ ስላላረጋገጠ ነው›› ሲል ፍርድ ቤቱ መቃወሚያውን እንዲቀበለው ጠይቋል፡፡ ሆኖም ዛሬ ሀምሌ 14/2007 ዓ.ም በልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት መቃወሚያውን ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጎታል፡፡ በሌላ በኩል ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ በነፃ ይሰናበቱ ወይንም ይከራከሩ የሚለውን ለመወሰን ለብይን ለነሀሴ 14/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

በዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ ከ1-6ኛ እንዲሁም 9ኛ ተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት ተማም አባቡልጉ ከጥብቅና በመታገዳቸው ምክንያት ሰባቱም ተከሳሾች በዛሬው ችሎት ያለ ጠበቃ ቀርበዋል፡፡ በዚህ መዝገብ ተከሰው አቶ ተማም መቃወሚያ ካቀረቡላቸው መካከል አቶ የሸዋስ አሰፋ፣ አቶ አብርሃ ደስታ፣ አቶ ሀብታሙ አያሌውና አቶ ዳንኤል ሺበሽ ይገኙበታል፡፡

Thursday 16 July 2015

Newly-freed Ethiopian Journalist Vows to Continue Work

Reeyot Alemu, an Ethiopian journalist who was unexpectedly released from prison last week after being convicted on terrorism charges, vows to continue her work as a reporter.Reeyot Alemu is a budding Ethiopian poet, essayist, and journalist.
“I am sure I will continue my writings because it’s my job, and also its my passion to write,” she said. “And also I want to serve my country. I want to make Ethiopia a democratic country, it is my responsibility as a citizen and as a journalist also.”
Reeyot had spent four years and 17 days in prison after a conviction many believe was a result of her articles which criticized the Ethiopian government.
She believes that her writings may lead to future imprisonment, as she does not believe this government allows anyone to live safely in Ethiopia while opposing those in power.
In 2011, Reeyot was arrested and then sentenced to 14 years in prison, which was reduced to five years after appeal. Her release last week came one day after five other imprisoned journalists and bloggers were released unannounced.
During most of her imprisonment, Reeyot shared one room with four other prisoners. The most difficult part, she says, was not not being able to receive visitors while dealing with a breast tumor.
“They denied my rights to be visited by my friends, my legal advisors. Even with my sister, they allow her these two months,” she lamented. “Before that for one year and eight months, even I did not see my sister. Only my parents, my mother and my father.”
Her father is also her lawyer, but during visitations they were not allowed to discuss legal matters.
While in prison, she says there were many offers for early release under the condition that she would agree to sign a letter admitting her wrongdoings or falsely accusing others. Reeyot refused and as a result, was ordered to spend another 11 months in prison.
These days Reeyot’s house is filled friends, family and other visitors welcoming her back. Next week she will go for a medical check up to continue treatment for her breast tumor.
Reeyot also plans on doing what she missed very much – reading books on political issues.
“I want to read how this country is, about the world,” she explained. “Because these four years I did not know, I did not get many information.”
Many international organizations continuously pressured the Ethiopian government to release the imprisoned journalists. The country has been frequently criticized by human rights organizations for repressing dissident voices.
The Committee to Protect Journalists says Ethiopia is Africa’s second worst journalist jailer with 11 other journalists and bloggers still imprisoned.
On social media, some people commented that the decision to release the journalists is linked to the visit of U.S. President Barack Obama to Ethiopia later this month.

ፍርድ ቤቱ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ የመከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ወሰነ

የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ድረስ ለተጠቀሱት ተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ወሰነ፡፡ የፌደራል አቃቤ ህግ ‹‹ከአንዳርጋቸው ጋር በአካል ተገናኝታችኋል›› የሚል ክስ የመሰረተባቸው ተከሳሾቹ ‹‹ከአንዳርጋቸው ጋር ተገናኝታችኋል ከተባለ አቶ አንዳርጋቸው ኢትዮጵያ ውስጥ ታስረው የሚገኙ በመሆናቸው መከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ፍርድ ቤቱ ይታዘዝልን›› የሚል ጥያቄ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡

የፌደራል አቃቤ ህግ በበኩሉ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በእነ ጀኔራል ተፈራ ማሞ መዝገብ እና በእነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ መዝገብ ላይ ክስ ቀርቦባቸው በእድሜ ልክና በሞት እንዲቀጡ ተወስኖባቸው የህዝባዊ መብታቸው የተሻረ በመሆኑ በምስክርነት ሊቀርቡ አይችሉም ብሎ ተቃውሟል፡፡ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ህዝባዊ መብት በመሻሩ ለፍርድ ስራ ልዩ አዋቂ ወይንም ነባሪ ሆነው መስራት አይችሉም ያለው የፌደራል አቃቤ ህግ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በተጨማሪ ምስክርነት ቀርበው መመስከር አይገባቸውም ሲል የተከሳሾቹ ጥያቄ ውድቅ እንዲሆን ለፍርድ ቤቱ አመልክቶ ነበር፡፡

ሆኖም ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው እንዲቀርቡላቸው የጠየቁት ለዋስት አሊያም ልዩ አዋቂ ምስክር ሆነው ሳይሆን ነበሩበት የተባለውን ጉዳይ ለመናገር ለምስክርነት በመሆኑ፣ ምስክርነትም ግዴታ እንጅ መብት በመሆኑ ሰኞ ሰኔ 13/2007 ዓ.ም በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ለተከሰሱት ተከሳሾች ልደታ ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲመሰክሩ ወስኗል፡፡ ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው የት እንደሚገኙና ማዘዢያው የት ተብሎ ሊፃፍላቸው እንደሚገባ ተጠይቀው ለቃሊቲ ማረሚያ ወይንም ለፀረ ሽብር ግብረ ኃይል ሊጻፍላቸው እንደሚገባ፣ ካልቀረቡላቸውም ክሳቸው ከአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ጋር የተገናኘ በመሆኑ አቶ አንዳርጋቸው በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡ እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድረስ አቤቱታ እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል፡፡

ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡላቸው በጠየቁበት ወቅት በዳኞችና በአቃቤ ህጎች ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ መፈጠሩንና ከአቶ አንዳርጋቸው ይልቅ ሌሎች መከላከያ ምስክሮችን ማቅረብ እንደሚችሉ፣ አቶ አንዳርጋቸውን በመከላከያ ምስክርነት ለማቅረብ መሞከር እንደሌለባቸው እንደገለፁላቸው ታውቋል፡፡ ዳኛው በድንጋጤ ‹‹እኛ እዚህ ጉዳይ ላይ የለንበትም›› ማለታቸውን ተከሳሾቹ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ውስጥ ላነጋገራቸው የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ገልጸውለታል፡፡
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

Wednesday 15 July 2015

Rights groups press Obama to meet activists on trip to Kenya and Ethiopia

President Obama pauses as he speaks

The groups voiced concerns about “grave and worsening human rights challenges” in the two countries.

MORE than 50 African and global human rights groups on Tuesday called on US President Barack Obama to publicly meet democracy activists when he visits Ethiopia and Kenya later this month.



In a letter delivered to the White House, groups welcomed Obama’s planned visit but voiced concerns about “grave and worsening human rights challenges” in his host countries.
Signatories included a host of African non-governmental groups as well as Human Rights Watch, Freedom House, the Open Society Foundation and the Robert F. Kennedy Human Rights Center.
“We believe it imperative that you take the opportunity of your visits to meet publicly with pro-democracy and human rights activists,” the letter said.

Citing the arrest of six bloggers in Ethiopia—five of whom have recently been released—and sanctions against two Kenyan human rights groups, the signatories described a “shrinking civic space” in both countries.

Obama’s willingness to meet activists, they said, would afford the groups protection and send a message that Washington stands with them.

Obama is due to visit Ethiopia later this month as well as Kenya, where his father was born.
A presidential visit to Kenya had been put on ice while President Uhuru Kenyatta faced charges of crimes against humanity for his role in 2007-2008 post-election violence.
The International Criminal Court has since suspended that prosecution, citing a lack of evidence and Kenya’s failure to cooperate.

Human rights groups have criticised the Kenya trip, but have also questioned why Obama is visiting Ethiopia so soon after a contested election, which saw the ruling party win all parliamentary seats.
The White House stressed that it frequently addresses issues of democracy and political rights with countries in the region.

Source: Mail & Guardian Africa

Tuesday 14 July 2015

ሰማያዊ ከምርጫ ማግስት እየተወሰደ ያለው እስርና ግድያ እንዲቆም ጠየቀ

ሰማያዊ ፓርቲ ከ2007 ሀገራዊ ‹‹የውሸት ምርጫ›› ማግስት በገዥው አካል እየተወሰደ የሚገኘው ግድያ፣ እስር፣ ከስራ ማፈናቀል፣ ማሸማቀቅና ድብደባ በአስቸኳይ እንዲቆም ጠየቀ፡፡

ፓርቲው ዛሬ ሐምሌ 7/2007 ዓ.ም ‹‹የወለደውን የረሳ ብሶት የወለደው ስርዓት! የዘመቻ እስርና ግድያ ተጠናክሮ ቀጥሏል!›› በሚል በጽ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እዳመለከተው፣ ምርጫው ከተጠናቀቀበት ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም ማግስት በምርጫው በንቃት ይሳተፉ የነበሩና በአስተሳሰባቸው በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸውን ዜጎች በማንአለብኝነት መደብደብ፣ ከሰራ ማፈናቀል፣ ማሰር፣ ማሸማቀቅና መግደል የአገዛዙ ዋና መገለጫ ሆኗል፡፡

ሰማያዊ በመግለጫው ‹‹በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ የሰማዊ፣ የመኢአድ፣ የቀድሞው አንድነት፣ የመድረክና የሌሎችም የፖለቲካ ፓርቲ አባላት በተለዬ ኢላማ ተጠምደው እየተሳደዱ፣ እየተደበደቡና በጅምላ እየታሰሩ አለፍ ሲልም በአሰቃቂ ሁኔታ እየተገደሉ ይገኛሉ›› ሲል ገልጾአል፡፡


አሁን በገዥው አካል እየተወሰደ ያለው ድርጊት ዜጎች በሰላማዊ መንገድ ለውጥ እናመጣለን የሚለውን አስተሳሰባቸውን የሚያጨልምና የሰላማዊ ትግል አቀንቃኞችን አንገት የሚያስደፋ ይዋል ይደር እንጅ መዘዙም ለማንም ወገን በተለይም ለገዥው መደብ የማይጠቅም መሆኑንም ፓርቲው በመግለጫው አስገንዝቧል፡፡


‹‹የአፈናው ስርዓት ብዙ ዓይነት አስተሳሰብና ልዩነት ባለባት ኢትዮጵያ ምርጫን መቶ በመቶ አሸንፌአለሁ ቢልም ሃቁ ግን የዲሞክራሲና የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግብዓተ መሬት እየተቃረበ መምጣቱን የሚያሳይ ነው፡፡ ይህንን እውነታ ገዥው ቡድንም የማይክደው መሆኑን በምርጫው ማግስት ጀምሮ የተዘፈቀበት ህዝብን እንደጦር የመፍራት አባዜው ገሃድ አድርጎታል›› በሏል ፓርቲው በመግለጫው፡፡ 


ሰማያዊ ፓርቲ ገዥው አካል ከሚፈፅማቸው ህገ ወጥና የማን አለብኝነት ተግባሩ እንዲቆጠብ፣ የዜጎች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች እንዲከበሩ ደጋግሞ መጠየቁን አስታውሶ፣ አሁንም ይህ አይነቱ ህገ-ወጥና የማንአለብኝነት ድርጊት በአስቸኳይ እንዲቆም ጠይቋል፡፡ 


መግለጫውን የሰጡት የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት እንደተናገሩት አሁን ያለው ትግል ‹‹ከአገዛዝ ወደ ዴሞክራሲ የሚደረግ የነጻነት ትግል›› ነው፡፡
በመጨረሻም ፓርቲው ሕዝብ የስልጣን ባለቤትነቱን እንዲያረጋግጥ በሚያደርገው ትግል ሁሉ ከጎኑ እንዲሰለፍ ጥሪውን አቅርቧል፡፡


Sunday 12 July 2015

“የኢትዮጵያ ህግ ልዕልና ከአሜሪካ ፕሬዘዳንት ክብር በላይ ሊሆን ይገባዋል” – በስደት ከሚገኙ የኢትዮጵያ ነጻ-ፕሬስ ጋዜጠኞች የተሰጠ መግለጫ

obama ethiopia







– በስደት ከሚገኙ የኢትዮጵያ ነጻ-ፕሬስ ጋዜጠኞች የተሰጠ መግለጫ
የኢትዮጵያ ነጻ ፕሬስ ጋዜጠኞችን “አሸባሪዎች” ብሎ በማሰር እና ከአገር እንዲሰደዱ በማድረግ የኢህአዴግ መንግስት ያላቋረጠ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ሲፈጽም ቆይቷል። ይህን የሰብአዊ መብት መተላለፍ በመቃወም፤ በአገር ውስጥ እና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ በመሆን ወገናቸን ታድገዋል። ሃሳባቸውን በነጻነት በመግለጻቸው ብቻ፤ “አሸባሪ” ተብለው በእስር ሲማቅቁ ከነበሩት ጋዜጠኞች እና ጦማርያን መካከል ተስፋለም ወልደየስ፣ ዘላለም ክብረት፣ አስማማው ሀ/ጊዮርጊስ፣ ርዕዮት አለሙ፣ ማህሌት ፋንታሁን እና ኤዶም ካሳዬ ተፈትተዋል።

 ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2015/07/Press-Release.pdf 

Saturday 11 July 2015

የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ እስሩ ቀጥሏል

በአዲስ አበባና በየክፍለ ሀገሩ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ እስሩ ቀጥሏል፡፡ ትናንትናው ዕለት በሸዋ ሮቢት የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪዎች የሆኑት አቶ ዘነበ ደሳለኝ፣ አቶ መንግስቱ ተበጀ፣ አቶ ቴዎድሮስ ሀብቴ እንዲሁም አዲስ አበባ ውስጥ አቶ ደብሬ አሸናፊ ታድነው የታሰሩ ሲሆን በዛሬው ዕለት አቶ መርከቡ ሀይሌና አናኒያ ኢሳያስ ለእስር ተዳርገዋል፡፡

መርከቡ ሀይሌና አናኒያ ኢሳያስ ዛሬ ሀምሌ 4/2007 ዓ.ም ከጠዋቱ ከቀኑ 4 ሰዓት ላይ አራት ኪሎ አካባቢ በፖሊስና ደህንነቶች ተይዘው ታስረዋል፡፡ እነ መርከቡ በተያዙበት ወቅት ፖሊስና ደህንነቶች ‹‹ብጥብጥ ልታስነሱ እየጣራችሁ መሆኑን ደርሰንበታል›› እንዳሉዋቸው ተገልጾአል፡፡ በተጨማሪም የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው ስለሽ ደቻሳ ሀምሌ 1/2007 ዓ.ም ከቤቱ በደህንነትና በፖሊስ ታፍኖ ከፍተኛ ድብደባ ከተፈፀመበት በኋላ ታስሯል፡፡ ስለሽ ደቻሳ በተፈፀመበት ድብደባም እጅና እግሩ ላይ ስብራት እንደደረሰበት ታውቋል፡፡ በተጨማሪም የሰማያዊ ፓርቲ ታዛቢ የነበረው አስፋው ጀማል በትናንትናው ዕለት በፖሊስ ተይዞ መታሰሩን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ መርከቡ ኃይሌና አናኒያ ኢሳያስ በአራዳ ፖሊስ መምሪያ እንዲሁም ስለሽ ደቻሳ 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ እንደታሰሩ ታውቋል፡፡

በተመሳሳይ እስሩ በየ ክፍለ ሀገሩን የቀጠለ ሲሆን በከፋ ዞን ጨላ ወረዳ 8 የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ‹‹ማዳበሪያ አልወስድም ብለዋል›› በሚል ለእስር እንደተዳረጉ ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ሌሎች የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በማዳበሪያ ሰበብ ድብደባ እየደረሰባቸው እንደሆነ የገለጹት የዞኑ የፓርቲው አስተባባሪዎች ነሲብ አደነ የተባለ የሰማያዊ ፓርቲ አባል ከፍተኛ ድብደባ ደርሶበት ሆስፒታል ውስጥ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

Wednesday 8 July 2015

BREAKING - Mahlet & Zelalem of Zone9 and jurnos Edom,Tesfalem & Asmamaw are released

Image

After a year and three months since they were first detained by the police, charges were dropped this afternoon against Journalists Tesfalem Wadyes, Asmamaw Hailegiorgis and Edom Kassaye as well as Zelalem Kibret and Mahlet Fantahun, members of the blog Zone9.

FBC, a pro government media outlet reported that charges were dropped only against five of the nine detainees by the order of the ministry of justice. Prosecutors will continue pursuing charges against Abel Wabella, Natinael Feleke, Befekadu Hailu, Atinaf Berhane and Soliana Shimelis of Zone9 bloggers, the later charged in absentia.

Tesfalem told Addis Standard that the name of the three of them were called out by a megaphone late this afternoon when they were told charges against them were dropped and “we can leave:. They were detained in Qilinto prison on the outskirt of Addis Abeba, where they were transferred to a few weeks after they have been kept incommunicado at Ma’ekelawi, a notorious prison in the heart of Addis Abeba.

They have since been charged under the country’s infamous Anti-terrorism proclamation, a charge marred by prosecutor’s inability to produce indisputable evidence. The charges have attracted global condemnation.

Their release comes a few weeks before the planned visit by President Barak Obama to Ethiopia. An unprecedented crackdown by Ethiopian security forces on April 24th and 25th 2014 saw the arrest of six independent bloggers writing for Zone9 blog post and three independent journalists.

Image

Journalist Tesfalem Wadyes, freelance journalist, Asmamaw Hailegiorgis, senior editor at an influential Amharic weekly magazine Addis Guday (which was forced to close since), and Edom Kassaye, who previously worked at state daily Addis Zemen Newspaper and an active member of the Ethiopian Environmental Journalists Association (EEJA) and a close associate of Zone9 bloggers were all rounded up and taken by security forces on Friday night May 24th 2014 to Ma’akelawi, a notorious prison located in the heart of Addis Abeba.

Along with them were six members of the Zone9 blogging collective. All are young and educated individuals with different background who come together to blog with a motto “we blog because we care”. They are: Atnaf Berhane IT professional, Mahlet Fantahun, Data expert, Befekadu Hailu from St. Mary’s University College, Abel Wabella, from Ethiopian Airlines, Natnail Feleke from the Construction and Business Bank, and Zelalem Kibret, from Ambo University.

ውጊያው ለ6ኛ ቀን ቀጥሏል * በወልቃይት ማይምቧ በተባለ አከባቢ ከበድ ያለ ውጊያ መደረጉን አርበኞች ግንቦት ሰባት አስታወቀ



(ኢሳት) ውጊያው ለ6ኛ ቀን ቀጥሏል:: በወልቃይት ማይምቧ በተባለ አከባቢ ከበድ ያለ ውጊያ መደረጉን ከአርበኞች ግንቦት ሰባት መረጃ ክፍል የደረሰን ዜና ያመለክታል:: በትላንትናው ዕለት ከአዲስ አበባ በ12 አውቶብሶች የተጫኑ ወታደሮች ወደ ወልቃይት በተለይም ውጊያው ወደበረታባቸው አከባቢዎች እንደተጓጓዙ ለማወቅ ተችሏል:: በቃፍቲያ እና አብርሃጅራር የማጥቃት እርምጃ ተውስዶ በመንግስት ሰራዊት ላይ ጉዳት መድረሱን የአከባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል:: በሰሜን ኢትዮጵያ የጦርነት እንቅስቃሴ እየታየ ነው::

በወልቃይት ማይምቧ በተባለ አከባቢ ከበድ ያለ ውጊያ መደረጉን ከአርበኞች ግንቦት ሰባት መረጃ ክፍል የደረሰን ዜና ያመለክታል:: በትላንትናው ዕለት ከአዲስ አበባ በ12 አውቶብሶች የተጫኑ ወታደሮች ወደ ወልቃይት በተለይም ውጊያው ወደበረታባቸው አከባቢዎች እንደተጓጓዙ ለማወቅ ተችሏል::

አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ የአርበኞች ግንቦት ሰባትን ጥቃት ለኤርትራ መንግስት ሸለሙት:: የኢትዮጵያን ህዝብ አስፈቅደን እርምጃ እንወስዳለን አሉ::የመከላከያ ሰራዊት አባላት አፈሙዛቸውን ወደ አፋኙ ስርዓት ማዞር አለባቸው የሚል ጥሪ እየቀረበ ነው:: ከኤርትራ መሬት ተነስቶ እየተፋለመ ወዳለው የኢትዮጵያ የነጻነት ሃይል ጥይት መተኮስ እንደሌለባቸው ከየአቅጣጫው ጥሪ እየቀረበ ነው::

በሰሜን ጦርነቱ ተጀመረ! አርበኞች ግንቦት ሰባት መግለጫ ሰጠ!

(ኢ.ኤም.ኤፍ) በዚህ ሳምንት ከተከናወኑት አበይት ጉዳዮች አንዱ፤ የአርበኞች ግንቦት 7 ጦር በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት መጀመሩ ነው። የአርበኞቹ እንቅስቃሴ በሰሜን ትግራይ ተጀምሯል። ከዚያም አልፎ ሌላው ግንባር ወደ ወልቃይት ጠገዴ ዘልቆ በመግባት፤ የወያኔ ወታደሮችን እየደመሰሰ መሆኑን ከስፍራው የሚደርሱን ዜናዎች አረጋግጠዋል።


የህዝባዊ ወያነ ሃርነት ትግራይ ወታደሮች አይሱዙ በማስቆም ተንጠልጥለው ሲሸሹ የሚያሳይ ምስል
የህዝባዊ ወያነ ሃርነት ትግራይ ወታደሮች አይሱዙ በማስቆም ተንጠልጥለው ሲሸሹ የሚያሳይ ምስል

ጦርነቱ እንደተጀመረ፤ የኢህአዴግ ባለስልጣን ፋና ሬድዮ ላይ ቀርበው፤ “ውሸት ነው። ምንም ጦርነት የለም።” ብለው ነበር። ከሁለት ቀናት በኋላ ግን ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ፤ በምክር ቤት ተገኝተው፤ ጦርነት መኖሩን አረጋግጠዋል። ሆኖም “ጦርነቱን የቀሰቀሰው ሻዕቢያ ነው” በማለት ለማስረዳት ሞክረዋል። ከአባባላቸው መረዳት እንደሚቻለው፤ ጦርነቱ መጀመሩን አምነዋል። ትንሽ የሚያስቀው በንግግራቸው መጨረሻ ላይ ለጦርነቱ ምላሽ ለመስጠት የኢትዮጵያን ህዝብ እንደሚያስፈቅዱ መግለጻቸው ነው። ይህ አባባላቸው ግን ኃይለማርያም ደሳለኝ መሳቂያ እና መሳለቂያ ነው ያደረጋቸው።


አርበኞች ግንቦት ሰባት በወልቃይት ጠገዴ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ
አርበኞች ግንቦት ሰባት በወልቃይት ጠገዴ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ

ይህ በእንዲህ እንዳለ… የአርበኞች ግንባር ግንቦት 7 ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ደግሞ፤ “…ለኢትዮጵያ ህዝብ ግልጽ ሊሆንለት የሚገባው ይሄ ጦርነት ከሻቢያ ጋር አይደለም….ይሄ ጦርነት ስለሻቢያ አይደለም…ይሄ ጦርነት የኤርትራና የኤትዮጵያ አይደለም!! ይሄ ጦርነት በዋናነት ወያኔ ስልጣን ላይ ለመቆየት የኢትዮጵያን ዲሞክራሳያዊ ኃይሎች ለመጨፍለቅ የሚያደርገው እንቅስቃሴ ነው…የኢትዮጵያ ህዝብ ይሄንን ይደግፈዋል ብየ ቅንጣትም አልጠራጠርም….የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ወያኔ እንደዚህ አይነት እብደት ውስጥ ቢገባ እንደበፊቱ እዚህ ውስጥ ይገባል ብየ አላስብም…!!!”

ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከኢትዮጵያ ህዝብ ፈቃድ እስከሚያገኙ ድረስ ግን… የአርበኞች ግንቦት 7 ህዝብ ግንኙነት “የመከላከያ፣ የፌደራል ፖሊስ፣ የልዩ ኃይል እና የሚሊሻ ጦር ሰራዊት አባላት ሆይ! የምትሞቱት ለማን ነው?” በማለት ከዚህ የሚከተለውን መግለጫ ይፋ አድርጓል።
================================================
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ በረሃ ወርዶ ነፍጥ በማንሳት ወደ ጦርት የገባው ተገዶ ነው፡፡ ያስገደደውም ተፋላሚው ቡድን አሁን በስልጣን ላይ የሚገኘው የህዝባዊ ሓርነት ትግራይ አገዛዝ ነው፡፡ የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ አገዛዝ ምን፣ ምን አይነት ግፍ እና በደል እያደረሰ እንደሚገኝና ምን አይነት መንግስታዊ ስርዓት እያራመደ እንዳለ ለእናንተ ለመከላከያ፣ ለፌደራል ፖሊስ፣ ለልዩ ኃይልና ለሚሊሻ ጦር ሰራዊት አባላት መንገር ለቀባሪው ማርዳት ነው፡፡ ምክንያቱም እናንተም የአገዛዙ የግፍ ሰለባ ሌላኛው አካል ስለሆናችሁና ፍዳውን እያየ ከሚገኘው ህዝብ አብራክ ስለተከፈላችሁ የህዝቡ ብሶት ብሶታችሁ ስለሆነ ነው፡፡

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ የሚዋጋው በጉልበት ስልጣን ይዞ በመንግስትነት ስም ኢትዮጵያን እያዋረደ፣ ህዝቧን እየገደለ እያስገደለ፣ እያሰረ፣ እያሰደደ፣ እያስራበ እና እያሳረዘ የሚገኘውን ህወሓት የሚሰኝ ዘረኛ ቡድን በኃይል ደምስሶ ህዝቡን ብቸኛው ሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት ለማድረግ በማለም ነው፡፡ አርበኞች ግንቦት 7 ህወሓትን በጥይት በመደብደብ ገድሎ ጉድጓዱን አርቆ በመቆፈር ከቀበረው በኋላ የሽግግሩን ሂደት ከማገዝና የህዝቡ የስልጣን ባለቤትነት በተግባር እንዲረጋገጥ ከማድረግ ውጭ በምርጫ ተወዳድሮ የመንግስት ስልጣን የመያዝ ዓላማ ፈፅሞ የለውም፡፡ አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞካራሲ ንቅናቄ ስልጣን የህዝብ እና የህዝብ ብቻ አንዲሆን አንጂ አምርሮ የሚታገለው መንግስት የመሆን ምኞት ኖሮት አይደለም፡፡ በታሪክ እስካሁን ከተደረጉት የነፃነት ትግሎች የአርበኞች ግንቦት ሰባትን ትግል ልዩ የሚያደርገው አንዱና ዋነኛው ጉዳይ ይሄ ነው፡፡

እኛም እናውቃለን፣ የኢትዮጵያ ህዝብም ያውቃል፣ እናንተም ታውቃላችሁ የአገሪቱን ሀብት እየዘረፉ በብልፅግና ላይ ብልፅግና እየተጎናፀፉ፣ ከመኪና መኪና እያማረጡ፣ በዲዛይነር የተሰራ ሱፍና ከረባት እየለበሱ፣ ጮማ እየቆረጡ ዊስኪ እየተራጩ፣ የተንደላቀቀ የቤተ መንግስት ህይወት የሚመሩት የህወሓት ባለስልጣናት ወደ ስልጣን ሲመጡ ምንም የከፈሉት ዋጋ የለም በድሃው የኢትዮጵያ ህዝብ ልጅ ደም እንጂ፡፡ አሁንም ስልጣናቸውን ማስቀጠል የሚፈልጉት የደሃውን ህዝብ ልጅ ለጦርነት በማሰለፍ በእሱ ደም እንጂ እነሱና ዘመድ አዝማዶቻቸው ምንም የሚከፍሉት ዋጋ አይኖርም፡፡

መከላከያ ሰራዊት፣ ፌደራል ፖሊስ፣ ልዩ ኃይል እና ሚሊሻ ሆይ! በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ሞትክ፣ በሶማሊያ ጦርነት ሞትክ፣ ኦጋዴን፣ ጋምቤላ፣ ሚዛን ቴፒ፣ አርማጭሆ… ላይ ደጋግመህ ሞትክ አሁን ደግሞ ትግራይ ክልል ውስጥ እየሞትክ ትገኛለህ፡፡ በአንተ ክቡር ህይወት፣ በአንተ ደምና አጥንት፣ በአንተ ታሪክ… ሊወድቅ የዘመመው የህወሓቶች የስልጣን ደሳሳ ጎጆ ለጊዜውም ቢሆን ተደግፎ ቆሞ አየህ እንጂ ለአንተ፣ ለቤተሰብህ፣ ለአገርህ ኢትዮጵያ፣ ለበቀልክበት ህዝብ ምን አተረፍክ? ባንተ ሞት እነማን ሹመትና ሽልማት እንዳገኙ ኑሯቸው እንደ ተቃና አንተው ራስህ ጠንቅቀህ ታውቀዋለህ፡፡ የምትሞተው አንተ፤ የምትዋረደው አገርህ ኢትዮጵያ፤ የሚረገጠው የወለደህ ህዝብ፤ የምትሞትለት መልሶ እየገደለህ የሚገኘው አንተው ራስህን ነው፡፡

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ የጀመረው ጦርነት የጥቃት ስልቱን እየቀያየረ ከህወሓት አድማስ ረቀቅና ወሰብሰብ ባለ መልኩ በኢትዮጵያ አራቱም ማዕዘናት ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ ነገር ግን ፍልሚያው አንደኛው ጭቆናን ለማስወገድ ሌላኛው ጭቆናን ለማስቀጠል ሲባል ጎራ ለይተው በተሰለፉ ሁለት ጭቁን ወንድምአማች ኢትዮጵያዊያን መካከል መሆኑ ግን አርበኞች ግንቦት ሰባትን በእጅጉ ያሳስበዋል፡፡ በመሆኑም ህወሓት በእናንተ ሞት ነግሶ ለመኖር አስታጥቆ ለእርድ ያሰለፋችሁ የመከላከያ፣ የፌደራል ፖሊስ፣ የልዩ ኃይል እና የሚሊሻ ጦር ሰራዊት አባላት የታጠቃችሁትን ጦር መሳሪያ አፈሙዝ የኢትዮጵያ ህዝብ እና የእናንተ ጠላት ወደሆነው ህወሓት እንድታዞሩ አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ጥሪውን ያቀርባል፡፡ አለበለዚያ ግን የምትከፍሉት ዋጋ ከመቸውም ጊዜ በላይ በእጅጉ የከፋ ነው የሚሆነው፡፡ ጦርነቱ በጣም ፈታኝ፣ ይህ ነው ተብሎ በቃላት ሊገለፅ የማይችል ዋጋ የሚያስከፍል፣ እስካሁን በተለያዩ ቦታዎችና ወቅቶች ሲደረግ ከነበረው የጎሬላ ውጊያ የተለየ የረቀቁ የውጊያ ስልቶችን የሚከተል መሆኑን ቃፍታ መሲን፣ ኮርጃሙስ፣ ማይ ሰገል፣ በዋል፣ ጓንጋ አሳግላ እና ማይ እምቧ ላይ በተደረገው ጦርነት በየዋህነት ተማግደው የተረፉ ጓዶቻችሁ ካሉ ጠይቃችሁ እውነታውን ማረጋገጥ ትችላላችሁ፡፡

ህወሓት የኢትዮጵያ ህዝብ በጠቅላላ አንቅሮ የተፋው የበሰበሰ ስርዓት መሆኑንም እንድታስታውሱ አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባችኋል፡፡ ዘረኛው የህወሓት ቡድን ያቋቋመው መንግስት በቅርቡ ብትንትኑ መውጣቱ አይቀርም የእናንተ ለስልጣኑ መጠበቂያ አሽከርነት ያቆማችሁ የመከላከያ፣ የፌደራል ፖሊስ፣ የልዩ ኃይልና የሚሊሻ ሰራዊት አባላት ከንቱ ሞት ግን አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄን ከወዲሁ በእጅጉ ያሳስበዋል ያሳዝነዋልም፡፡ ዘላለማዊ ክብር ለጀግኖች ሰማዕታት ድል ለአርበኞች ግንቦት 7 ጀግኖች ሞት ለዘረኛውና ፋሽስቱ ወያኔ!

Sunday 5 July 2015

ወያኔ አርበኞች ግንቦት 7 የከፈተበትን ጦርነት ከህዝብ ለመደበቅ እየሞከረ ነው

ባለፉት ሦስት ቀናት የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች ትግራይ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የወያኔን ሃይል ገጥመው የወያኔ መኮንኖችን ጨምሮ በርካታ የወያኔ ሰራዊት አባላትን እንደገደሉ በቃል-አቀባያቸው አማካኝነት ለኢሳት ቴሌቪዥን ገልጸዋል። ለጥቀውም እስከ ትላንት ድረስ ውጊያው ቀጥሎ እንደሚገኝ በድጋሜ ዜናውን አብስረዋል።

arbegnoch-ginbot7-fighters

በወያኔ ዘረኛና ግፈኛ አገዛዝ የተንገፈገፈው የኢትዮጵያ ህዝብም ጆሮውን አቅንቶ ሁኔታውን በመከታተል ላይ ነው። ቀድሞውንም የወያኔ ሥርዓት ያለ ሃይል ትግል አይንበረከክም፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የፖለቲካም ሆነ የሥርዓት ለውጥ ሊመጣ የሚችለው በተቃውሞው ጎራ የተሰለፉት ተባብረው በወያኔ ላይ ክንዳቸውን ሲያሳርፉ ብቻ ነው ብለው የሚያምኑት ኢትዮጵያውያን አርበኞች ግንቦት 7 በወያኔ ላይ የከፈተውን ማጥቃት በከፍተኛ ደስታ ነው የተቀበሉት።

አንዳንዶች አርበኛውን በገንዘብ ለመደገፍ እና ለማጠናከር ከወዲሁ እንቅስቃሴ ጀምረዋል።
ይህ በዚህ እንዳለ በወያኔ ጎራ በኩል ይህን ጉዳይ በተመለከተ ምንም የተሰማ ነገር የለም። ጥያቄው… ለወትሮው ትንሽ ትልቁን “የግንቦት 7” አባል ነው ብሎ በመፈረጅ ንጹሃንን እስርቤት የሚወረውረው ወያኔ በይፋ ስለተከፈተበት ጦርነት ለምን ዝምታን መረጠ? ነው።

ዘረኛውና አምባገነኑ የወያኔ ሥርዓት ህዝብ እጅግ እንደጠላውና ሆ ብሎ ሊነሳበት እንዳቆበቆበ ይረዳል። ስለዚህም ጉዳዩ ከቁጥጥሩ ውጭ ሆኖ የህዝብ መነጋገሪያ እንዲሆን አይፈልግም። ያ ሆነ ማለት የተዳፈነው ፍም እሳት ፊቱ ላይ ተረጨ ማለት ነው።
ለዚህም ይመስላል በአርበኞች ግንቦት 7 የተሰነዘረበትን ጥቃት ለማብረድ ድምጹን አጥፍቶ መውተርተርን የመረጠው።
ሌላው ተጨማሪ ማስረጃ ደግሞ ወያኔ በአርበኞች ግንቦት 7 የተሰነዘረበትን ጥቃት ለመመከት ወደ አካባቢው እያሰማራ ያለው የጦር ክፍል ከአንድ ጎሳ የውጡና ቀደም ሲል በጡረታ ተሰናብተው ወያኔ ከወልቃይት ህዝብ ላይ ነጥቆ በሰጣቸው ለም መሬቶች ላይ የግብርና ስራ እያካሄዱ የሚገኙ የቀድሞ የህወሃት አባላት መሆናቸው ነው።

Obama’s Planned Visit to Ethiopia is Incompatible with Claims of Democratic Principles of the US Government

Statement from Oromo Liberation Front (OLF)
asxaa_oromoThe Oromo Liberation Front (OLF) strongly opposes the planned visit to Ethiopia of the US President Barack Obama on the end of July 2015. As Ethiopia is one of the most brutal regimes of the world, OLF believes that such a visit will result in strengthening the dictatorial minority regime, will boost the regime’s confidence to strengthen its ruthless human rights violations, will give a green light to the regime to continue its repression, economic exploitation, and marginalization of various nations and nationalities of the country under its usual pretense of democracy. OLF also believes that a lasting national and security interest of the US is better protected not by blessing and supporting such a well-known ruthless regime, but by being on the side of the people, supporting the struggle of the peoples of the country for freedom, democracy, and justice by using its leverage through exerting the necessary pressure on the regime on power.

In 1991 when the dictatorial military regime of Mengistu Hailemariam was overthrown by the combined struggle of the oppressed peoples of Ethiopia and a Transitional Government was about to be established, a commitment given from the US government to the Ethiopian people was an assurance of “no democracy, no cooperation”. It was the then US Assistant Secretary of State for African Affairs, Herman Cohen, who gave such assurance in public. However, the TPLF/EPRDF group who took over the government not only by using the military upper hand it had but also using the blessing of the US official Herman Cohn demonstrated its anti-democratic nature in practice in a matter of less than one year. Several organizations who struggle for the right of their people, including the Oromo Liberation Front (OLF), opposed the tyrannical and authoritarian practices of the TPLF/EPRDF party as the dominant force and left the then Transitional Government of Ethiopia.

Today, 24 years have passed under the totalitarian TPLF/EPRDF regime erected and protected by the West, mainly the United States of America. It is impossible to enumerate the widespread political repression, economic exploitation, and monopoly of a minority regime in all sectors political, economic and social life. Among many other reports, the repeated reports of human rights organizations such as Amnesty International, Human Rights Watch, Human Rights League of the Horn of Africa, including the Country Report US State Department all shed light to the atrocities of the current Ethiopian regime committed on the peoples of the country, mainly on the Oromo people. Nonetheless, it has to be noted that all these and many other reports show only a small fraction of the repression and brutalities perpetrated by the regime. Most of the political killings, barbaric acts of torture, politically charged arrests, abductions and disappearances carried out by the regime are hidden and remain unreported. The OLF has ample evidence that most acts of ruthlessness committed on the Oromo nationals in several parts of Oromia are not reported at all.

Overall, although some knowingly or unknowingly deny or diminish the repressive nature of the current Ethiopian regime, the truth is that the basic democratic and human rights and freedom of peoples of the country is denied in Ethiopia. While Ethiopia has never seen democratic election in its history, the undemocratic and fake nature of so called “election” carried by the current regime has no parallel even in the Ethiopian standard. Over the last 24 years, the Ethiopian people have been forced to “elect” the TPLF/EPRDF party under the barrel of the gun. The 2015 so called “election” is a clear evidence that, for the people of the country, let alone electing whoever they want, any suspicion about electing the opposition parties the government conveniently put in the election drama has been a crime subjecting citizens to severe punishment. While the so called election drama and its result in which the TPLF/EPRDF declared 100% victory are officially over, as we speak, thousands of Oromo and other nationals are being hunted down and thrown into jail for suspicion of “electing” the few opposition who didn’t even win a single seat in the parliament.

If the US’s claims of strengthening democratic process were true, what is expected of President Obama at the moment was not to plan official visit to Ethiopia, but to use his leverage to put pressure on the minority Woyane (TPLF) regime to stop terrorizing its citizens and hold democratic election by openly condemning the process and rejecting the results of the current sham election. It is disturbing that, to the contrary, the US government, looking at the temporary benefit it may or may not get from alliance with the brutal regime and ignoring the suffering of the peoples of the country, is encouraging the regime towards committing more crimes and rewarding the regime for the endless atrocities it has already committed. This is not what is expected of a country which claims to be democratic and acts as the “police” of our planet.

It is to be recalled that, the US Under Secretary for Political Affairs Wendy Sherman, appeared in Finfinnee (Addis Ababa) on one of the days leading to the regime’s “election” drama of 2015, and endorsed the election by suggesting that “Ethiopia had made great strides toward an open and inclusive electoral process”. She went on saying that the US hopes the then upcoming election would be “free, fair, inclusive, and peaceful”. Her endorsement and blessing of the so called “election” as an official US position came at a time when the regime was completing its preparation to run a sham election marred with harassment, arrest, intimidation, and several schemes of vote rigging.

The irresponsible blessing and approval by Wendy Sherman of an election which is universally well-known to be full of fraud was condemned by many human rights and other international organizations. Clearly, the endorsement and blessing of this US official has bolstered the confidence of the government to continue its crackdown on dissenting voices, blatantly harass the entire public, and finally committed naked election fraud and now shamelessly declared 100% victory. The current planned visit of President Obama has no benefit to the peoples of Ethiopia or the region. To the contrary, it is another endorsement and blessing of an election which is very well known by the Ethiopian people and the entire world to be bogus.

The Oromo Liberation Front (OLF) earnestly appeals to the US government to reconsider its position and cancel the planned visit to Ethiopia of President Barack Obama. The OLF would like to reiterate that, although such a visit of a US President could temporarily seem to reinforce the confidence of the brutal regime on power, it will never reverse or pull back the struggle the oppressed peoples of the country are waging to gain their freedom. The history of the struggle of the peoples of the region confirms that no external force can reverse the just fight of people against dictators. Sooner or later, brutal regimes will disappear like a dust. It is only a matter of time.

Victory to the Oromo People!
Oromo Liberation Front
July 04, 2015

የሳሙኤልን ገዳይ መደበቅ ያልቻለው ድራማ

ዜጎች በተራ ‹‹ወንጀል›› 14 ከዚህ አለፍ ሲል 28 ቀን እየተቀጠሩ በሚመላለሱበትና በሚጉላሉበት ሀገር፣ አባሪው እንኳ ባልተያዘበት ሁኔታ፣ ይህ ነው የሚባል ምርመራ ሳይደረግ የሳሙኤል አወቀ ገዳይ በ17 ቀን ውስጥ 19 አመት እስራት እንደተፈረደበት ተሰምቷል፡፡ ትናንት ችሎቱን የተከታተሉት ሰዎች በግምት ከምሽቱ ሶስት ሰዓት አካባቢ አዲስ አበባ ለሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች የነበረውን ድራማ በስልክ ሪፖርት ያደርጋሉ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን ስልክ የሚጠልፈው ኢህአዴግ ሪፖርቱ ‹‹ሳሙኤልን አልገደልነውም›› የሚለውን ድራማቸውን የሚያራክስ መሆኑን ተረድቷል፡፡ የፍርድ ቤቱ ድራማ ቀድሞ በሰማያዊ በኩል እንዳይወጣ ጉዳዩ ለሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ሪፖርት ከተደረገ ከደቂቃዎች በኋላ በራሱ ካድሬዎች በኩል ቀድሞ ‹‹ፍርዱን!›› ይፋ አደረገ፡፡ ዛሬ ደግሞ እነ ፋና እየተረባረቡበት ነው፡፡ ከምንም በላይ ወንጀሉን የግል ሲያደርጉት ድምፀታቸው ግን ሳሙኤልን ማን እንደገደለው ግልጽ እያደረገባቸው ነው፡፡

 Samuel Awoke, member of Semayawi party, killed by TPLF


ሳሙኤል አወቀ ከአንድ አመት በላይ ካድሬዎችና ደህንነቶች ‹‹እንገድልሃለን›› እያሉ እየዛቱበት መሆኑን በማህበራዊ ገጹ አስቀምጧል፡፡ በፖለቲካ አመለካከቱ ምክንያት በፖሊስ ታድኖ ታስሯል፡፡ ከሀገር ውጣልን ብለውት ‹‹አልሰደድም›› ብሎ ነገረ ኢትዮጵያ ላይ ጽፏል፡፡ ከደህንነት፣ ካድሬዎችና የፖሊስ አዛዦች የሚደርስበት ማስፈራሪያና ዛቻ ከሶስት ጊዜ በላይ በነገረ ኢትዮጵያ ተዘግቧል፡፡ ለአብት ያህል ሰኔ 10/2006 ዓ.ም ነገረ ኢትዮጵያ ላይ ‹‹ጠበቃው በፖሊስ እየታደነ ነው›› በሚል ዜና ‹‹ህዝብ እየተበደለ ነው ብለህ የአስተያየት መስጫ ሳጥን ላይ አስተያየት ሰጥተሃል:: አገር ለቀህ ካልተሰደድክ እንገድልሃለን›› መባሉ በዋቢነት ተቀምጧል፡፡

የደንበኞች አስተያየት መስጫ ላይ የጻፍከው አንተ ነህ ተብሎ በተከሰሰበት ወቅት የምስራቅ ጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸጋዬ መንግስቴ ዳኞች በተገኙበት ‹‹በማንኛውም ጊዜ መንገድ ላይ ይዛችሁ ማሰር ትችላላችሁ፡፡ ዴሞክራሲያዊም ሆነ ሰብአዊ መብት የሚባል አይሰራም›› ብለውታል፡፡ የደብረማርቆስ ፖሊስ ኮማንደር ‹‹አስደፋሃለሁ!›› ብሎ ዝቶበታል፡፡ ከመገደሉ አንድ ወር በፊት እግሩን ሰብረውታል፡፡ ከመገደሉ ሁለት ሳምንት በፊት በተፈጠረበት ከፍተኛ ስጋት ‹‹ብታሰርም መንፈሴ አይታሰርም፣ ከገደሉኝም ትግሌን አደራ›› ሲል ተናዝዟል፡፡

ሳሙኤል አወቀ ድብደባ ሲፈፀምበት፣ ከዛም በኋላ ሲገደል በድንገት መብራት መጥፋቱን የአካባቢው ነዋሪዎች እማኝነታቸውን ሰጥተዋል፡፡ ሳሙኤል አወቀ የተገደለው ከምሽቱ 1፡30 አካበቢ ነው፡፡ በዚህ ወቅት እሱን ሌት ተቀን ይከታተሉት የነበሩት ፖሊሶች እንኳን በቦታው አልነበሩም፡፡ የተገደለው መሃል ከተማው ላይ ሆኖ እያለ ፖሊስ የደረሰው ከአንድ ሰዓት ተኩል በኋላ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ ነው፡፡ ከ1፡30 በኋላም በቦታው የደረሰው ፖሊስም ሳሙኤልን በግል የሚያውቀው መሆኑ ምን አልባት ‹‹አርፈህ ተቀመጥ!›› ተብሎም ስላልቻለ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ያም ሆኖ ተሰቃይቶ እንዲሞት ስለተፈለገ በሚመስል መልኩ ፖሊስ ደርሶ እስኪጣራ ተብሎ ሀኪም ቤት እንዳይደርስ ተደርጓል፡፡

የሳሙኤል አወቀ ገዳዮች ከተባሉት መካከል አንዱ ወዲያውኑ ማታ እንደተያዘ ተነገረ፡፡ ተባባሪዎቹ ግን ሊያዙ አልቻሉም፡፡ እንግዲህ ተባባሪዎቹ ባልተያዙበት፣ በዚህ ፍትህ በሚራዘምበት ሀገር የሳሙኤል አወቀን ገዳይ ሰኔ 25/2007 ዓ.ም በተገደለ በ17 ቀን ውስጥ የ19 አመት እስር ተፈርዶበታል ተብሏል፡፡ በትናንትናው ዕለት በዋለው ችሎት የሳሙኤል ቤተሰቦችና ሌሎች ወጣቱን የሚያውቁት ግለሰቦችም ተገኝተው እንደታዘቡት፣ አቶ ተቀበል ገዱ 19 አመት ተፈረደበት በተባለበት ችሎት ዳኛው ስለ ፍርድ ሂደቱ ምንም ነገር አላነበቡም ተብሏል፡፡ ፍርዱ ሲነበብ ሳሙኤል እንዴት እንደተገደለ በምርመራና በፍርድ ሂደቱ የተገኙት ሀቆች መገለጽ አለባቸው፡፡ ግን ደግሞ የሚያሳጡ ሆኑና በፍጥነት 19 አመት እንደተፈረደበት ተናግረው ወጥተዋል፡፡

ገዳይ ተብሎ የተያዘው አቶ ተቀበል ገዱ ‹‹እኔ ሳሙኤል አወቀ የሚባለውን ሰው አላውቀውም፡፡ ግደለው ተብዬ ገንዘብ ስለተሰጠኝ ነው የገደልኩት፡፡›› ማለቱ ከእስር ቤት ሾልኮ ወጥቷል፡፡ ‹‹ማን ነው ገንዘቡን የከፈላችሁ?›› ሲባል ደግሞ ‹‹እኔ እሱንም አላውቀውም፡፡ ለእኔ ገንዘቡን የሰጠኝ ያልተያዘው ጓደኛዬ ነው፡፡ እንድንገድልለት የፈለገውም ሰውም የሚያውቀው እሱ ነው›› ማለቱን እስረኞቹ ተናግረዋል፡፡

በተመሳሳይ ከዚህ በፊት በዋለ ሌላ ችሎት ገዳይ የተባለው ሰው ‹‹ለምን ገደልከው?›› ሲባል ሻይ ቤት ውስጥ በተፈጠረ አለመግባባት ሳሙኤል ቀድሞ በዱላ ስለመታው እንደገደሉት ገልጾአል፡፡ ይሁንና ይህ ከሳሙኤል ግላዊ ባህሪ ጋር የሚሄድ አይደለም፡፡ ይህንንም ገዳይ ተብሎ የተያዘውና የተፈረደበት አቶ ተቀበል ገዱ እንደገና እጁን አውጥቶ ዳኛው እድል ሲሰጡት ‹‹ቅድም ሻይ ቤት ውስጥ ስለተጣላን ነው የገደልኩት ያልኩት አቃቤ ህጉ በል ስላለኝ ነው፡፡ አላውቀውም፡፡›› እንዳለ ችሎቱን የተከታተሉት ይናገራሉ፡፡

ሳሙኤል በተገደለ ማግስት ካድሬዎች ግድያው ከጥብቅና ጋር በተያያዘ ነው በሚል ጉዳዩን ከኢህአዴግ ካድሬዎችና ደህንነቶች እራስ ለማውረድ ጥረው ነበር፡፡ በወቅቱም ሳሙኤል የተገደለው ለጥብቅና ቆሞለት ከነበረው አርሶ አደር ጋር አለመግባባት በመፈጠሩ ነው እያሉ ለማስመሰል ጥረዋል፡፡ ይሁንና በትናንትናው የፍርድ ቤት ውሎ ፍርድ ቤቱ ለገዳዩ ማቅለያ ሲያቀርብ ‹‹የቀን ሰራተኛ በመሆንህና በዚህ ስራም ቤተሰብን የምትደጉመው አንተ በመሆንህ አንቀፁን ከ38 ወደ 31 አውርደንልሃል›› ሲሉ ተደምጧል፡፡ በዚህም መጀመሪያ ካሉት ከአርሶ አደርነት ወደ ቀን ሰራተኝነት ቀይረውታል፡፡ ይህም መጀመሪያ ግድያው ፖለቲካዊ አይደለም ለማለት ካድሬዎች ከደንበኝነት ጋር ያያዙትን ውድቅ የሚያደርግ ነው፡፡ በእርግጥ የውስጥ ምንጮች እንደሚሉት መጀመሪያ አካባቢ አቃቤ ህግ ሳሙኤል የተገደለው ከደንበኝነት ጋር በተያያዘ ለማስመሰል ጥረው ነበር፡፡ ይህኛው ድራማ አላስኬድ ሲል በትዕዛዝ እንዲቋረጥ ተደርጓል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የሳሙኤል አወቀን ቤተሰቦች ለማስተዛዘን ወደ ጎጃም ያቀኑት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት አባይ በርሃ ላይ ተይዘው እስከ ምሽቱ 2፡30 ከታሰሩ በኋላ ቢፈቱም ወደ ለቅሶው እንዳይሄዱ መኪና እና ቁሳቁሶቻቸውን መነጠቃቸው ይታወሳል፡፡ በወቅቱ መርማሪዎቹ በተደጋጋሚ ይጠይቁት የነበረው ጥያቄ ‹‹ሳሙኤልን ማን ገደለው?›› የሚል ነበር፡፡ ይህም የሚያሳየው መረጃዎች ያጋለጡትን የሳሙኤል ገዳይ በድራማ ለመደበቅ ያደረጉት መንደፋደብ ነው፡፡ ከመጀመሪያው ጀምሮ እስከ ትናንትናው የፍርድ ውሎና አሁንም ድረስ የቀጠለው ፕሮፖጋንዳ የሚያሳየው ሳሙኤል በፖለቲካ አመለካከቱ የተገደለ መሆኑን ነው፡፡ ይህን ለመሸፈን ፍርድ ቤት አድርጎት የማያውቀውን እጅግ የተፋጠነ ‹‹ፍርድ›› ሰጥቷል፡፡ መጀመሪያ ከደንበኝነት ጋር በተያያዘ ነው የተገደለ ብለው አሁን የማያውቀው የቀን ሰራተኛ ነው የገደለው ብለዋል፡፡ እነሱ ‹‹ሻይ ቤት ውስጥ ተጣልተን ነው የገደልኩት›› እንዲልላቸው ቢፈልጉም እሱ ግን እንደገና ‹‹ይህን እነሱ ናቸው በል ያሉኝ›› ብሎ መስክሮባቸዋል፡፡ ገዳይ ተብሎ ለተያዘው ሰው ገንዘብ የሰጠው አባሪ አልተያዘም፡፡ በእርግጠኝነት አምልጦ አይመስለኝም፡፡ ግድያውን ካቀነባበረው ሰው ጋር የሚያገናኝ ድልድይ በመሆኑ እንዳይያዝ ስለሆነ እንጅ፡፡ ሆኖም ይህ ሁሉ ድራማ ገዳዩን መደበቅ አልቻለም፡፡ ከምንም በላይ ድራማው ሳሙኤል ባለፈው አንድ አመት በሚዲያና በማህበራዊ ደረ ገጹ ያሰፈራቸው እማኝነቶችና ሌሎችን መረጃዎች ያጋለጡትን ገዳይ መደበቅ አልቻለም፡፡

Friday 3 July 2015

ሜሮን አለማየሁ 6 ወር ተፈረደባት

መንግስት አይ ኤስ አይ ኤስን ለመቃወም በጠራው ሰልፍ ሰበብ ታስራ ‹‹ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ በማወክ›› የተከሰሰችው ሜሮን አለማየሁ የ6 ወር እስር ተፈረደባት፡፡ ሜሮን አለማየሁ ሚያዝያ 14 በተጠራው ሰልፍ ላይ ‹‹ወያኔ ሌባ፣ መንግስት የለም፣ አትነሳም ወይ፣ የታረደው ወገን ያነተ አይደለም ወይ›› በሚል ሁከትና ብጥብጥ ፈጥራለች ተብላ በተከሰሰችበት በዋስ ወጥታ ጉዳዩን ስትከታተል የቆየች ሲሆን ዛሬ ሰኔ 26/2007 ዓ.ም በጎፋ ፍርድ ቤት ቀርባ 6 ወር ተፈርዶባታል፡፡

አቃቤ ህግ በክሱ ሜሮን አለማየሁ ድንጋይ እንደወረወረች ቢጠቅስም፣ የአቃቤ ህግ ምስክሮች ስትወረውር አላየንም ብለው፡፡ በተጨማሪም አቃቤ ህግ ሜሮን ከ200-300 የሚሆኑ ሰዎችን በመምራት ሁከትና ብጥብጥ እንደፈጠረች ጭብጥ ቢያስይዝም ምስክሮቹ አቃቤ ህግ እንዳለው ሳይሆን ሜሮን አለማየሁን ከ20-30 ከሚሆኑ ሰዎች ጋር እንዳዩዋት መስክረዋል፡፡ በተመሳሳይ አቃቤ ህግ ሜሮን አለማየሁ ብጥብጡን የፈጠረችው መስቀል አደባባይ ላይ ነው ሲል ምስክሮቹ አቃቤ ህግ ባለው ሰዓት ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ በሚወስደው መንገድ እንዳዩዋት መስክረዋል፡፡

አቃቤ ህግ ሜሮን አለማየሁ ብጥብጡን የፈጠረችው ከ3 ሰዓት እስከ 4 ሰዓት ባለው ጊዜ ነው ያለ ሲሆን የሜሮን አለማየሁ የመከላከያ ምስክሮች ከ3፡20 እስከ 5 ሰዓት ከእሷ ጋር አምባሳደር አካባቢ እንደነበሩ አስረድተዋል፡፡ ሆኖም ፍርድ ቤቱ ምስክሮቹ ከ3፡20 በፊት የት እንደነበረች አላስረዱም እንዲሁም ካፌ ውስጥ የጠጡትን ለስላሳ አልገለጹም በሚል ምስክርነቱን ውድቅ አድርጌዋለሁ ብሏል፡፡

Wednesday 1 July 2015

የእስር ጊዜያቸውን ጨርሰው ሲወጡ ሌላ ክስ የተመሠረተባቸው የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በዋስ ተለቀቁ


የአይኤስ አሸባሪ ቡድን ሊቢያ ውስጥ በኢትዮጵያውያን ላይ በፈጸመው አሰቃቂ ግድያ ምክንያት መንግሥት በጠራው ሰላማዊ ሠልፍ ላይ ረብሻ በመፍጠር ተከሰው የተፈረደባቸው የሰማያዊ ፓርቲ አባላት፣ የእስር ጊዜያቸውን ጨርሰው ሲወጡ ከማረሚያ ቤት በራፍ ላይ ተይዘው ከተመሠረተባቸው ክስ በዋስ እንዲለቀቁ ብይን ተሰጠ፡፡

የፓርቲው አባላት ሰኔ 23 ቀን 2007 ዓ.ም. እያንዳንዳቸው በ5,000 ብር ዋስ እንዲለቀቁ የፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቄራ ምድብ ችሎት ብይን የሰጠው በወይንሸት ሞላ፣ በኤርሚያስ ፀጋዬ፣ በዳንኤል ተስፋዬና በቤተልሔም አካለ ወርቅ ላይ ነው፡፡
በተከሳሾቹ ላይ ሰኔ 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ፍርድ ተሰጥቶ የነበረው፣ ሰላማዊ ሠልፉን በማወክ የተለያዩ ስድቦችን መንግሥትንና ዜጎችን በመሳደብ፣ ሥርዓቱን በማንጓጠጥና በፖሊስ አባላት ላይ ድንጋይ በመወርወር ወንጀል ተከሰው ነው፡፡

ፍርደኞቹ ሰኔ 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ለፍርድ በቀረቡበት ዕለት ሁለት ወር ከአንድ ቀን በእስር መቆየታቸው በመረጋገጡ፣ በዕለቱ ከእስር እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ የሰጠ ቢሆንም ፖሊስ ሌላ ወንጀል መፈጸማቸውን በመግለጽ፣ ሰኔ 16 ቀን 2007 ዓ.ም. ከእስር ተፈትተው ወደ ቤታቸው ለማምራት ማረሚያ ቤት ደጃፍ ላይ ሲደርሱ ተይዘው ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስደዋል፡፡
ፖሊስ ለፍርድ ቤት ያቀረበው ክስ፣ ተከሳሾቹ ቀደም ብሎ በተከሰሱበት ወንጀል ላይ በምስክርነት ያቀረባቸውን ማስፈራራታቸውንና መዛታቸውን በመግለጽ ነው፡፡ ፍርድ ቤቱ ክሱን ተቀብሎ ለሰኔ 23 ቀን 2007 ዓ.ም. መዛታቸውን የሚያስረዱለትን ምስክሮቹን እንዲያቀርብ ቀጠሮ የሰጠ ቢሆንም፣ ፖሊስ ምስክሮቹን በተለያዩ ምክንያቶች ሊያቀርብ አለመቻሉን ገልጾ፣ ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል፡፡

ተከሳሾቹ ግን ፖሊስ ምስክሮቹን በተሰጠው ቀጠሮ ቀን ማቅረብ እንደነበረበት ገልጸው፣ ፍርድ ቤቱ ዋስትና እንዲፈቅድላቸው ጠይቀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ጥያቄውን ተቀብሎ እያንዳንዳቸው በ5,000 ብር ዋስ እንዲለቀቁ ፈቅዷል፡፡ በሌላ በኩል ተከሳሾቹ ቀደም ብሎ ሰኔ 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ሁለት ወራት ተፈርዶባቸው በነበረውና እስራቸውን ጨርሰው በወጡበት ክስ፣ ዓቃቤ ሕግ ይግባኝ እንዳለባቸውና ሰኔ 24 ቀን 2007 ዓ.ም. በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ተጠቁሟል፡፡