Monday, 3 October 2016

የቢሾፍቱው እልቂት የህወሓት መቀበሪያ ጉድጓድ ቁፋሮ ነው!!!- አርበኞች ግንቦት 7

ዛሬ መስከረም 22 ቀን 2009 ዓም ዓመታዊ ባህላዊ የእሬቻ በዓል ለማክበር በሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ ቢሾፍቱ (ደብረዘይት) ከተማ የሚገኝ ሀይቅ ዳር ተሰባስቦ ነበር። በበዓሉ ትውፊት መሠረት ለፈጣሪ ምሥጋና ለማቅረብ ብዙዎች ቄጠማ፣ ለምለም ሳርና አበባዎችን ይዘው ነበር። ሕዝቡ አጋጣሚውን በመጠቀም የህወሓት አገዛዝ በክልሉና በመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚያደሰውን በደል ለመቃወም የተቃውሞ ድምጾችን አሰማ፤ የተቃውሞ ምልክቶችን አሳየ።

ሕዝባዊ ተቃውሞ ባጋጠመው ጊዜ ሁሉ የሚሸበረው የህወሓት አገዛዝ ለሰላማዊ ተቃውሞ የሰጠው ምላሽ እንደተለመደው ጥይት ነበር። ሕዝብ በማንኛውም ቦታ ተቃውሞ የማቅረብ መብት አለው። በየትኛውም ዓለም ሕዝባዊ በዓላት ዓይነተኛ የተቃውሞ ማቅረቢያ ቦታዎች ናቸው። ተቃውሞው የቀረበበት ድባድ በጣም ሰላማዊየነበረ በመሆኑ የተለየ ጥበቃ ሊሰጠው ሲገባ የአገዛዙ ምላሽ ግን ከተለመደው የባሰ ሆነ። በታንኮች ላይ ከተጠመዱ መትረሶች ተኩሰው በርካታ ሰው መፍጀታቸው አልበቃ ሲላቸው በሄሊኮፕሮች ላይ በተጠመዱ መትረሶች ሕዝቡን ፈጁ። የሞተውና የቆሰው ሕዝብ ብዛት ምን ያህል እንደሆነ መናገር ለጊዜው አይቻልም፤ ያም ሆኖ ግን ሟቶች በመቶዎች ቁስለኞች ደግሞ በሺዎች ነው የሚቆጠሩት።

ዛሬ መስከረም 22 ቀን 2009 ዓም የአየር ኃይል፣ የፌደራልና የኦሮሚያ ክልል ፓሊስ ሠራዊትና የአጋዚ ክፍለ ጦር አባላት የፈፀሙት እጅግ አሳፋሪ ፋሽስታዊ ተግባር ለዘመናት የማይሽር ቁስል ፈጥሯል። “ነፃነታችንን እንፈልጋለን። የኦህዴድ ቅጥረኝነት ይብቃ፤ አማራን፣ ትግሬን፣ ጉራጌን፣ ኮንሶን፣ … ኢትዮጵያውያንን በሞላ እንወዳለን! አንጣላላችሁም!” ማለታቸው ነው በጥይት ያስፈጃቸው። ይህ ዋጋ የሚያስከፍል ግፍ ነው። ዋጋ የሚስከፍል መሆኑ ደግሞ እያየን ነው፤ ሕዝባዊ እምቢተኝነቱ በመላው ኦሮሚያ እንደገና እየተቀሰቀሰ ነው። አሁን ኦሮሚያ ብቻውን አይደለም፤ የአማራ ወገኑ ከጎኑ አለለት፤ ኮንሶው፣ ሲዳማው፣ ጉራጌው፣ አፋሩ፣ ሶማሌው፣ ትግሬው … የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድነት ይነሳል። የቢሾፍቱው እልቂት የህወሓት መቀበሪያ ጉድጓድ ቁፋሮ ነው።

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዛሬ መስከረም 22 ቀን 2009 ዓም በቢሾፍቱው እልቂት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ለሰማዕታቱ ቤተሰቦች እየገለፀ መጽናናትን ይመኛል፤ እንደዚሁም የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖቻችንም የተሰማውን ጥልቅ ስሜት ይገልፃል። አርበኞች ግንቦት 7 ከነገ ጀምሮ ያሉት ሶስት ተከታታይ ቀናት የሐዘን ቀናት እንዲሆኑ ያሳስባል።

ለሰማዕታትና ቁስለኛ ወገኖቻችን የሐዘን መግለጫዎችን መስጠት ችግሩን አይፈታውም፤ ይልቁንም የሞቱለትና የቆሰሉበት ዓላማ ከግብ ለማድረስ ጠንክረን መታገል ይኖርብናል። የህወሓት አገዛዝን በቢሾፍቱ በቆፈረው ጉድጓድ ውስጥ ለመቅበር ሁላችንም ተባብረን መነሳት የሚኖርብን ወቅት ላይ እንገኛለን።

ስለሆነም የተለየ ጥሪ ወይም የተለየ አመራር ሳትጠብቅ በሥርዓቱ የተማረርክ ሁሉ ከወዳጆችህ ጋር እየተቧደንክ ተነስ ! በየአካባቢው የሚገኘውን የአገዛዙን ወዋቅር እያፈረስክ የራስህን ጊዜዓዊ የሕዝብ አስተዳደር መስርት። አገራዊ ዓላማ ይኑርህ ትኩረት ግን በአካባቢያዊ ጉዳዮች ላይ ይሁን። ሁሉም አካባቢውን ከህወሓት አገዛዝ ነፃ ያውጣ!

አንድነት ኃይል ነው !
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!

Sunday, 2 October 2016

Ethiopian regime forces massacred hundreds of Oromos at the annual Irreecha celebration

Attack helicopters from the sky and the notorious TPLF-Agazi forces from the ground unleashed live bullets against millions of unarmed Irreecha festival participants in Bishoftu (Debre Zeyit).
Hundreds dead and many are injured.

Disturbing photos and video footage are starting surfacing on social media under the hashtag #OromoProtests and #Irreechamassacre







Friday, 30 September 2016

ሕወሓት “ትግሬ አይደለሁም; አማራ ነኝ” ባሉት ኮለኔል ደመቀ ዘውዱ ላይ በአሸባሪነት ክስ ሊመሰርት መሆኑን የሚያሳይ ደብዳቤ ወጣ

(ዘ-ሐበሻ) አማራ ነኝ ስላሉ ብቻ እስር ቤት የገቡት እና የአማራው ተጋድሎ ግንባር ቀደም መሪ ተደርገው የሚወሰዱት ኮለኔል ደመቀ ዘውዱ ላይ የትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት የአሸባሪነት ክስ ሊመሰርት መሆኑን የሚያሳይ ደብዳቤ ወጣ::

በሶሻል ሚድያዎች የተሰራጨው ይኸው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው ለአማራ ክልል ፍርድ ቤት የተጻፈ ደብዳቤ ይልና ኮለኔል ደመቀ ዘውዱ በተጠረጠሩበት የሽብር ፈጠራ ወንጀል የሰው እና የሰነድ ማስረጃ ለማሰባሰብ 28 ቀን ቀጠሮ ይሰጠኝ ይላል:: ከደብዳቤው መረዳት እንደተቻለው “ትግሬ አይደለሁም አማራ ነኝ” ያሉት ኮለኔሉ በአሸባሪነት ይከሰሳሉ::

ይህን ተከትሎ በተለይ በአማራ ጉዳይ ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረገ የሚገኘው አክቲቭስት አቻምየለህ ታምሩ በኮለኔል ደመቀ ዘውዱ የሽብር ክስ ዙሪያ የሚከተለውን አስተያየት በፌስቡክ ገጹ አስፍሯል:-
“ፋሽስት ወያኔ እነኮሎኔል ደመቀን “በሽብር ፈጠራ» ክስ ሊመሰርት ነው። በቤተ ወያኔ አማራ ነኝ ማለት በአሸባሪነት የሚያስቀስፍ ወንጀል ስንል ከመሬት ተነስተን አይደለም። የነኮሎኔል ደመቀ ወንጀል አማራ መሆናቸው ብቻ ነው። እነኮሎኔል አማራነታቸውን በአደባባይ በመግለጻቸው ከኦሳማ ቢን ላድን እኩል በአሸባሪነት ክስ ሊመሰረትባቸው ነው። ይህ የወያኔ ልግጫ ዛሬ አማራው እያደረገው ያለውን ትግል የበለጠ በሞትና ህይወት መካከል የሚደረግ ፍልሚያ፤ ላለመሞት ሲል ሊገድለው ከሚመጣ ጨካኝ አውሬ ለመዳን የሚያደርገውን ተጋድሎን ተገቢ ብቻ ሳይሆን ህጋዊም ያደርገዋል።”

Thursday, 29 September 2016

በጎንደር እና ጎጃም የሚታፈሱ ወጣቶች አያያዝ ከፍተኛ ስጋት በውስጡ ፈጥሯል

በደብረ ማርቆስ እና ጎንደር በርካታ ወጣቶች በአፈሳ መታሰራቸው ተነገረ፡፡ አሁንም ድረስ አንጻራዊ መረጋጋት በሌለባቸው የሰሜናዊ ምዕራብ አማራ ክልል ከተሞች፣ የመንግስት ወታደሮች በተለይ ወጣቶችን በዘመቻ መልክ እያፈሱ መሆኑን መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡ በደብረ ማርቆስ ከተማ ወጣቶች ለመስቀል በዓል የሚዘምሩትን የመዝሙር ግጥም እስከማስለወጥ የደረሱት የመንግስት ወታደሮች፣ በዚህም ምክንያት በነዋሪው እና በደህንነቶቹ መካከል ግጭት መከሰቱን ከስፍራው የተገኘው መረጃ አመልክቷል፡፡

ግጭቱን ተከትሎ ቁጥራቸው በርከት ያለ ወጣቶች መታሰራቸውን የሚገልጹት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ወታደሮቹ የደመራውን በዓል ለማሰሪያነት እንደ ሰበብ ተጠቀሙበት እንጂ፣ እነማን መታሰር እናዳለባቸው አስቀድሞ ከቀበሌ አስተዳዳሪዎች ጋር መምከራቸውን ገልጸዋል፡፡ ‹‹ለዚህም ነው በበዓሉ ወቅት ራሳቸው ሁከት እንዲፈጠር አድርገው ልጆቹን ያሰሯቸው›› ሲሉ ነዋሪዎቹ አክለዋል፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ በጎንደርም ብዙ ወጣቶች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፣ የሰሜን ጎንደር ከተሞችም በህወሓት ጥርስ ውስጥ መግባታቸውን ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ የጸጥታ ኃይሎቹ በሰሜን ጎንደር ከተሞች ሰማይ ላይ ሄሊኮፍተር እያጓሩ፣ ነዋሪውን ለማሸበር መሞከራቸውም ታውቋል፡፡ በጎንደር አንዳንድ አካባቢዎች በነበረው የበዓል ስነ-ስርዓት ላይ በመንግስት ወታደሮች አስጀማሪነት በተፈጠረው ሁከት፣ በርከት ያሉ ወጣቶች ለእስር መዳረጋቸውን መረጃዎች ጠቁመዋል

በአፈሳ መልክ ታስረው የተወሰዱ ሰዎች ኢሰብዓዊ በሆነ የእስር ቤት አያያዝ ስር መውደቃቸውን የገለጹት የመረጃ ምንጮች፣ ታሳሪዎቹ የሚወሰድባቸው እርምጃም ከበድ የሚል እንደሆነ መረጃዎቹ አክለው ገልጸዋል፡፡ በቁጥጥር ስር የዋሉት ወጣቶችን አፋር ክልል የሚገኙ የበረሃ እስር ቤቶች በመውሰድ ከባድ ቅጣት እንደሚያደርሱባቸው የገለጹት ምንጮች፣ በተወሰደባቸው እርምጃ ህይወታቸውን ያጡ ወጣቶች መኖራቸውንም ምንጮቹ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ ልጆቻቸውን ፍለጋ ወደ ፖሊስ ጣብያ ያመሩ ወላጆችም ለጊዜው ልጆቻቸውን ማግኘት እንደማይችሉ ተነግሯቸው መመለሳቸው ታውቋል፡፡

ታፍሰው የተወሰዱ ወጣቶች በተለያዩ ማሰልጠኛ ካምፖች ትምህርት እየተሰጣቸው መሆኑን የሚገልጹት የመንግስት ኃላፊዎች፣ በታሳሪ ወጣቶች ላይ እየደረሰ ያለውን መከራ ዓይን ባወጣ ቅጥፈት ለማስተባበል ሞክረዋል፡፡ ከተያዙት ወጣቶች መካከል 99 ፐርሰንቶቹ የጸባይ ማረሚያ ዓይነት ትምህርት ወስደው እንደሚፈቱ የመንግስት ኃላፊዎች ቢገልጹም፣ ምንጮች ግን የታሳሪዎቹ ህይወት ከባድ አደጋ ላይ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡

በቃሊቲ በሚገኙ እስረኞች ላይ የሚደረገው ጫና መቀጠሉ ተነገረ

በቃሊቲ ወህኒ ቤት በሚገኙ የፖለቲካ እስረኞች ላይ የሚፈደረገው ጫና እና ማሰቃየት መቀጠሉ ታወቀ። የ18 ዓመታት እስራት ተፈርዶበት ላለፉት 5 አመታት በዚህ ወህኒ ቤት በሚገኘው በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ላይ በእስር ቤቱ ሃላፊዎች የሚፈጸመው ጥቃት መቀጠሉን እንዲሁም የማበሳጨት ዕርምጃዎች መጨመራቸውን መረዳት ተችሏል።

በቅድሚያ የጻፋቸውን ማስታወሻዎች፣ በኋላም ማናቸውንም የጽህፈት መሳሪያና ባዶ ወረቀቶች ጭምር የነጠቁት የእስር ቤቱ አዛዦች የተለያዩ ቁሳቁሶች እንዳወደሙበትም በቅርቡ ከእስር ቤት የወጣ ግለሰብ ለኢሳት አብራርቷል።
በዚህ እስረኛ ገለጻ መሰረት ሰሞኑን ፍተሻ በሚል ብርበራ ያካሄዱት የእስር ቤቱ ሃላፊዎች እስክንድር ልብስ የሚያስቀምጥበት ሻንጣ ሲወሰዱ፣ ልብሱን ሜዳ ላይ እንደበተኑት የገለጸ ሲሆን፣ ሻንጣውን ሲወስዱ የሰጡም ምክንያት አልነበረም። እስረኛው እስሩን ጨርሶ እስከወጣበት ዕለት ድረስ ሻንጣዎም ሆነ ሌሎች ንብረቶች እንዳልተመለሰለት ገልጿል። 

ከአንድነት አመራሮች አንዷለም አራጌና ናትናዔል መኮንን ጋር መስከረም 3 ቀን 2004 ዓም የታሰረው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ባለፉት 5 አመታት በወህኒ ቤት የቆየ ሲሆን፣ የ18 ዓመታት እስራት እንደተፈረደበትም ይታወሳል። 


ከፔን አሜሪካና ሂውማን ራይትስ ዎች ከመሳሰሉ የሰብዓዊና የጸሃፊያን ድርጅቶች አለም አቀፍ ሽልማት የተቀበለው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ሃሳቡን በነጻነት በመግለጹ ሳቢያ መታሰሩን የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጆን ኬሪ ምስክርነት መስጠታቸው አይዘነጋም።


ኢሳት

Wednesday, 28 September 2016

Gondar uprising leader charged with terrorism

The leader of the the movement in the Amhara region that is campaigning to restore areas forcefully annexed to Tigray by the Tigrian-led regime has been charged with terrorism.

Colonel Demeke Zewdu, seen by many Ethiopians as the leader of the ongoing uprising against a minority regime in Amhara region, was charged Wednesday after several court adjournments.

The colonel was taken to the custody of the Amhara police in July after he shot dead three operatives of the regime who went all the way to his house from Tigray to arrest him without a court warrant.
At the time of his arrest, the colonel was spearheading a committee that was demanding the regime that the areas of Wolkait, Tegede and Telemt in North Gondar to be returned to the Amhara region and for the people residing in those areas recognized as Amharas.

The regime, upon its ascension to power 25 years ago, had annexed the regions in North Gondar to Tigray and declared the residents Tigrians despite widespread resistance.

Residents of Gondar, who flocked to the court for Wednesday’s hearing, denounced the charges as bogus. They say the regime, instead of attending to the demands of the people, have brought trumped-up charges against the Colonel. They vowed to fight against the injustice to the end. The court was adjourned again till October 13, 2016.

The campaign by the people of North Gondar to restore their land and identity reached its peak when people in the Amhara and other regions of Ethiopia joined the movement and staged protest rallies demanding the removal of the tyrannical regime in Ethiopia.

Security forces killed at least 200 people this summer in the Amhara region alone. Protests are still continuing in the Oromo and other regions of Ethiopia, despite a military administration put in place by the regime to silence opposition. Over a thousand people were killed in the Oromo region this year, while tens thousands remained in detention.

Meanwhile , security forces have continued arresting people in the Amhara region. There are also reports of deaths at concentration camps in Bir Sheloko and Benishangul, where detainees have reportedly been going through unimaginable torture.

Colonel Demeke fought alongside the TPLF against the former military government. But he fell out of favor when he began challenging the regime on the issue of the regions in North Gondar that were forcefully incorporated into the Tigray region.

                                                      Col. Demeke Zewdu

Five killed in one week in Oromo region

Security forces killed a student in Mendi, west Wellega, Oromo region of Ethiopia on Monday as residents were preparing to celebrate Meskal, the finding of the true cross.

Lideta Imana was killed by a sniper after he left home to join the celebration at a bonfire ceremony on the eve of Maskal on Monday. Lideta is the fifth person to be killed since the transfer of power last week in the Oromo region. The regime replaced the leaders of the Oromo People’s Democratic Organization last week with two individuals, Lema Megersa and Workineh Gebeyehu, who have ties to the intelligence and security of the regime.

Mamo Garene in West Arsi, Yifa Adisu in Nekemt, Eyasu Solomon in Tejo and Mohammed Abdella Ousman in Somali region were killed in just one week alone.

The funeral of Lideta was conducted on Tuesday in the town of Mendi. Angry residents came out for the funeral, shutting down the town on Tuesday.

The protest in the Oromo region of Ethiopia is nearing one year with the killings still continuing unabated. It is estimated that over one thousand peaceful civilians were reportedly killed by security forces in the Oromo region alone.

The protest against the tyrannical regime in Ethiopia had spread to the Amhara region this summer where at least 200 people were reportedly killed in two months of protests. Tens of thousands of people were also incarcerated in various prisons and secrete locations all over the country without due process.


                                             Funeral of Lideta Imana