Monday 29 January 2018

በወልዲያ ተቃውሞ ዳግም ተቀሰቀሰ

መሀል ወልዲያ ዛሬ ጠዋት ከፍተኛ የህዝብ ተቃውሞ ሲደረግና የመንግስት ተቋማት ላይ ጥቃት ሲሰነዘር እንደነበርም ለማወቅ ተችሏል።

ከቀትር በኋላ በቤት ውስጥ የመቀመጥ የስራ ማቆም አድማ የተመታ ሲሆን ወልዲያ ሁሉ ነገር ከእንቅስቃሴ ውጭ ሆኖ እንደዋለም ታዉቋል። ህዝባዊ አመጹ በተለያዩ ከተሞች እየተካሄደ ነው። የመርሳ ከተማ አስተዳዳሪ መገደላቸውም ታውቋል። በሲሪንቃ በርካታ ተሽከርካሪዎች ተቃጥለዋል። መንገዶች ተዘግተዋል። የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጧል። የመርሳው ተቃውሞ ለሶስተኛ ቀን መቀጠሉም ይነገራል። የሰሜን ወሎ ዋና ዋና መንገዶች በሙሉ ከአገልግሎት ውጪ መሆናቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

ኢሳት


0 comments:

Post a Comment