Tuesday 16 September 2014

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሕወሃት/ኢሕአዴግን ስብሰብ ረግጠው ወጡ !

ገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ፣ ሕግ መንግስቱን በጣሰና የከፍተኛ ተቋማት ገለልተኛነትን በመጋፋት፣ ተቋማት የሚጠበቅባቸውን የሞያ ስልጠና ከመስጠት አልፈው ተራ የፕሮፖጋንዳ መንዢያ ቦታዎች እንዲሆኑ በማድረግ፣ የፖለቲክ ስልጠና በሚል፣ የተለያዩ ስብሰባዎችን በተለያዩ የአገሪቷ ክፍሎች እየጠራ መሆኑ ይታወቃል። በስብሰባዎቹ ተማሪዎች ለባለስልጣናቱ የተለያዩ ጥያቄዎች በመጠየቅ፣ ስልጠናዎቹ እንደታሰበው አለመሄዳቸው በስፋት ተዘግቧል።
aa_university1
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተደረገው ስብሰባ፣ አገዛዙን ወክለው የመጡት አቶ ሬድዋን ሁሴን በሚናገሩበት ጊዜ ተማሪዎች ስብሰባዉ ረግጠነው እንደወጡ ዘገባዎች ይጠቁማሉ። በከፍተኛ ተቋማት የሚገኙ ተማሪዎች በዘር በመከፋፈል፣ መግባባትና መመካከር እንዳይኖር ማድረጉ፣ ዋን መሳርያው የሆነው ገዢው ፓርቲ፣ ሰሞኑ በከፍተኛ ተምህርት ተቋማት እየታየ ያለው የተማሪዎች መተባበር፣ ትልቅ ራስ ምታት እንደፈጠረም ተንታኞች ይናገራሉ።
« የወያኔን ስብሰብን ርግጦ እስከ መዉጣት ሰው ከደረሰ፣ ፖለቲካው መክረሩን አመላካች ነው» ያሉት በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የፖለቲካ ተንታኝ « በተለይም ደግሞ የተማሪዎች ተቃዉሞ በአንድ ቦታ ብቻ ሳይሆን በሁልም የአገርቷ ክፍሎች ባሉ ተቋማት መሆኑ፣ ለአገዛዙ ሁኔታዎች በጣም ያወሳስበዋል» ሲሉ ሕወሃት/ኢሕአዴግ በአስገዳጅነት እያደረገ ያለው የተማሪዎች ስልጠና ፣ በራሱ እግር ላይ ሽጉጥ እንደመተኮስ እንደሆነበት ይናገራሉ።
በደርግ ጊዜ ከፍተኛ ተቋማት ዲያለከትካል ማቴሪኡአልም የኮሚኒስ ማኒፌስቶ የመሳሰሉ ኮርሶችን ተማሪዎች እንዲወስዱ ይደረግ እንደነበረ ያስታወሱት እኝሁ ተንታኝ፣ አሁንም ሕወሃት/ኢሕአዴግ በኢቲቪና በመሳሰሉት ሕዝብን የሚያደነቁረው አንሶት፣ ተማሪዎች፣ ሳይንስ፣ አርት፣ ኢንጂነሪን፣ ሕክና በሚማሩበት ተቋማት ፣ ለእውቀታቸዉና ለጊዜያቸው የማይመጥን ፣ ተራና ኋላቀር ስልጠናዎችን ለመስጠት መሞከሩ፣ ዳግማዊ ደርግ መሆኑን የሚያመላከት እንደሆነ አክለው ይናገራሉ።

0 comments:

Post a Comment