Friday, 9 October 2015

Video: A long line of young Ethiopian women arrive in Beirut in just one day

Poverty at home drives thousands of Ethiopian women to flock to Middle Eastern countries to work at domestic workers, where they are treated as slaves.

"We are not humans in Lebanon. We are treated like animals or maybe a machine or a robot that they can charge to work," Miryam Kessaya of Ethiopia tells Al Jazeera. "I'm not treated as a human. I'm not treated like a woman," said Miryam, who is struggling to form a union of domestic workers along with other activities from India, Philipines etc.


Thursday, 8 October 2015

ባልተፈጸመ ወንጀል፣ ባልቀረበ ማስረጃ ዜጎችን ማንገላታት ይቁም

በዛሬው ዕለት በነሶልያና የክስ መዝገብ በዞን ዘጠኝ ጦማርያን ላይ ማለትም በሶልያና ሽመልስ (በሌለችበት)፣ አቤል ዋበላ፣ አጥናፍ ብርሃኔ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና በፍቃዱ ኃይሉ ላይ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ችሎት ዳኞች "አዳማ ስልጠና ላይ ናቸው" በሚል ባለመገኘታቸው ምክንያት ለጥቅምት 5/2008 ዓ/ም ለ 38ተኛ ጊዜ ቀጠሮ መሰጠቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የሁለቱ ዳኞች የመሃል ዳኛው አቶ ሸለመ እና አቶ ዘርሁን ተቀይረዋል የሚባል መረጃ የተገኘ ሲሆን አቶ ታረቀኝ ብቻ ችሎቱ ላይ ይቀጥላሉ ተብሏል። ለችሎቱ አዲስ የተሾሙት ዳኞች ማንነት እስካሁን አልታወቀም።

በእስር 531ኛ ቀናቸውን እያሳለፉ የሚገኙት ጦማርያኑ ይህ የ"ፍርድ ቤት" ቀጠሮአቸው ለ38ኛ ጊዜ የተሰጣቸው ነው ፣ የቀረበባቸው ማስረጃን ገምግሞ ይከላከሉ ወይስ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ ይሰናበቱ የሚለውን ውሳኔ ለማሰማት "ፍርድ ቤቱ" የዛሬውን ጨምሮ ለ5ኛ ጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ስሜት የማይሰጡ ክሶች እና የተራዘሙ የፍርድ ሂደቶች ዜጎችን በአገራቸው የበለጠ ተስፋ እንዲቆርጡ የሚያደርጋቸው ከመሆኑም በላይ ያለዋስትና በፍርሃት እንዲኖሩ የሚያደርግ ነው፣ ይህ እንዲሆን ካልተፈለገ በቀር በቀጠሮዎች መራዘም ንጹሃንን ጥፋተኛ ማድረግ እንደማይቻል የዞን9 ጦማርያን እናምናለን፡፡


ባልተፈጸመ ወንጀል፣ ባልቀረበ ማስረጃ ዜጎችን ማንገላታት ይቁም፡፡

ዞን9
 

ረሃቡ ከገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት የመነጨ መሆኑን ሰማያዊ ፓርቲ ገለፀ

• ‹‹ለችግሮቻችን ምንጭ የሆነውን ስርዓት በቁጥርጠኝነት መታገል አለብን››

ሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ መስከረም 27/2008 ዓ.ም በፅ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ረሃቡ ከገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት የመነጨ ነው ብሏል፡፡ ፓርቲው ‹‹ረሃቡ የገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት ነው!›› በሚል በሰጠው መግለጫ ‹‹ገዥው ፓርቲ ችግር ቢከሰት እንኳ በአደጋ ጊዜ ለዜጎች የሚበቃ እርዳታ አቀርባለሁ ሲል የነበረ ቢሆንም ለወገኖቻችን ግን የሚደርስላቸው አልተገኘም፡፡›› ሲል ወቅሷል፡፡ ‹‹ለዜጎች ዓለም አቀፍ ተቋማት እንዳይደርሱላቸው የተፈጠረው ረሃብ የራሱ የፖሊሲ ውድቀት መሆኑን የሚያውቀው ስርዓቱ የዜጎቻችን ስቃይና መከራ ሲሸፋፍን እንደቆየና ከአቅሙ በላይ ሲሆን ችግሩ እንደተከሰተ ቢገልፅም ለዜጎች ተገቢውን እርዳታ በሚያስገኝ መልኩ እርምጃ እየወሰደ አይደለም›› ብሏል መግለጫው፡፡ ለተከሰተው የረሃብ አደጋ ተገቢው ትኩረት መነፈጉም ገዥው ፓርቲ እመራዋለሁ ለሚለው ህዝብ ደንታ ቢስነቱን የሚያረጋግጥ እንደሆነ አስታውቋል፡፡

ፓርቲው በመግለጫው ‹‹ረሃቡ፣ ርዛቱ፣ ድህነቱ፣ ስደቱ፣ ስራ አጥነቱ፣ የኑሮ ውድነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዜጎችን በብርቱ እየተፈታተኑ በሚገኝበት ወቅት ገዥው ፓርቲና በስሩ ያሉ ድርጅቶች ተመሰረትንበት የሚሉትን ጊዜ ለወራት በቅንጦት በማክበር በብዙ ሚሊዮን ገንዘብ ከኢትዮጵያውያን ጉሮሮ ነጥቆ ድግስ ሲደግስና አሸሸ ገዳሜ ሲል በርካታ ኢትዮጵያውያንን አሳዝኗል፡፡›› ብሏል፡፡ ለተከሰተው ረሃብ ኢህአዴግ ለይስሙላ ቆሜለታለሁ የሚለውን አርሶ አደርና አርብቶ አደርን ህይወት ለማሻሻል የረባ ስራ እንዳልሰራ አረጋግጧል ያለው መግለጫው ግብርናው ኢኮኖሚውን ይመራል ቢልም እስካሁን ግን በየአመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የረሃብ ሰለባ እንደሆነ መቀጠሉን ገልፆአል፡፡ መሬት የመንግስት ነው በሚል ሽፋን አርሶ አደሩን ከቀየው እያፈናቀለ ለስርዓቱና ደጋፊዎችና ለባዕዳን መሬትን እየሸጠ አርሶ አደሩን ለረሃብ ተጋላጭ አድርጎታል ሲልም ለርሃቡ ምክንያት የኢህአዴግን የፖሊሱ ውድቀት እንደሆነ ገልፆአል፡፡

ገዥው ፓርቲ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ የጠየቀው ሰማያዊ ፓርቲ ስለ ችግሩ ለኢትዮጵያውያንና ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ የሚያስረዳ ገለልተኛ አካል ተቋቁሞ በረሃብ ለተጠቁት ዜጎች መፍትሄ እንዲፈለግም ጠይቋል፡፡ ስርዓቱ ደካማና ኃላፊነት የጎደለው እንደሆነ የገለፀው ሰማያዊ ፓርቲ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ኢትዮጵያውያንና የዓለም ማህረሰብ ማህበረሰቡ ከተጎጅዎቹ ጎን እንዲቆሙ ጠይቋል፡፡ ‹‹የኢትዮጵያውያን መከራ የመነጨው ከገዥው ፓርቲ የተሳሳተ ፖሊሲ፣ የአፈፃፀም ብቃት ችግርና ለኢትዮጵያውያንም ባለው ግድ የለሽነት በመሆኑ ለችግሮቻችን ምንጭ የሆነ ስርዓት በቁጥርጠኝነት መታገል አለብን›› ሲልም ለህዝብ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ፓርቲው ረሃቡ በተከሰተባቸው አካባቢዎች መረጃ በማሰባሰብና በማጣራት ለህዝብ እንደሚያሳውቅም ገልፆል፡፡

Wednesday, 7 October 2015

Court urged to acquit and free four Zone 9 bloggers still held

The Addis Ababa court that is trying the four members of the Zone 9 blogging collective who are still detained is due to issue a verdict when the 37th hearing in their trial is held on 8 October. Reporters Without Borders (RSF) calls for their acquittal and immediate release. 

Arrested in April 2014 under the 2009 anti-terrorism law, Atnaf Berhane, Befekadu Hailu, Abel Wabella and Natnail Feleke are facing the possibility of 10 to 15 years in prison on charges of “working with foreign organizations claiming to defend human rights” and “receiving funding in order to incite the public to violence via social media.”

The two other members of the collective and three journalists who were arrested at the same time and on the same grounds were released in July after the justice ministry decided to drop the charges against them without further legal justification.

While it welcomed their release at the time, the withdrawal of charges ordered by the justice ministry could be challenged in future before the courts, according to observers.

RSF therefore calls for a not-guilty verdict that would prevent any future prosecution of the bloggers on similar grounds. Since the release of two of the Zone 9 bloggers in July, the prosecutor has not presented any new evidence against the four still held.

“We urge the court and the authorities to be fair and open with the Zone 9 bloggers,” said Clea Kahn-Sriber, the head of the Reporters Without Borders Africa desk. “If there is no solid evidence against them, they should be freed at once and they should be acquitted so that there is no danger of any subsequent prosecution for the same facts.” 

Zone 9 calls itself as “an informal group of young Ethiopian bloggers working together to create an alternative independent narration of the socio-political conditions in Ethiopia.”
The collective’s name alludes to the eight detention zones in Addis Ababa’s notorious Kality prison (where human rights defenders and journalists are held).

The blog was blocked by the authorities within Ethiopia soon after its creation in 2012 but remained accessible abroad and the group continued to post information and comments on social networks. Because of constant harassment by the authorities, they suspended activity seven months before their arrests, which occurred immediately after they announced that they were going to resume blogging.
There has been a dramatic decline in the number of media outlets in Ethiopia, which is ranked 142nd out of 180 countries in the 2015 Reporters Without Borders press freedom index.

Many reporters and editors with privately-owned print media fled the country in 2014 after being threatened by the authorities. Prosecutions of journalists under the 2009 anti-terrorism law. which provides for long jail terms, have been almost systematic.


ሰማያዊ ፓርቲ በመሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግ ጠየቀ

• የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ ውይይት ላይ እንደማይሳተፍ አስታውቋል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

ሰማያዊ ፓርቲ ከትራንስፎርሜሽን ረቅቅ ዕቅድ በፊት ለመሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ቅድሚያ ተሰጥቶ ውይይት እንዲደረግ ጠየቀ፡፡ መንግስት መስከረም 28 እና 29/2008 ዓ.ም በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ ላይ ለመወያየት ከሀገር አቀፍ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ከጠራው የእቅድ ውይይት ላይ እንደማይገኝም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በፃፈው ደብዳቤ ገልፆአል፡፡ ፓርቲው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በፃፈው ደብዳቤም የብዙሃን ፓርቲ ዴሞክራሲ፣ የሰብአዊ መብት አያያዝ፣ የነፃ መገናኛ ብዙሃንና ሲቪክ ማህበራት ከእቅዱ በፊት ቅድሚያ ሊሰጣቸው እንደሚገባ ጠቁሟል፡፡

በእቅዱ ዝርዝር ከመወያየት በፊትም በኢትዮጵያ አንድነትና ብሄራዊ መግባባት አስፈላጊነትና አፈፃፀሙን በተመለከተ ቅድሚያ ሰጥቶ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር መወያየትና መፍትሄ መፈለግ ለኢትዮጵያ ሰላም፣ ዕድገትና ልማት አስፈላጊ መሆኑን ፓርቲው እንደሚምን ገልጾአል፡፡

በመሆኑም ፓርቲው መሰረታዊ ጉዳዮች መፍትሄ ባልተበጀላቸው ሁኔታ በዕቅድ ዝርዝር የአፈፃፀም ሁኔታ ላይ መወያየት ለኢትዮጵያ የሚመኘውን ዕድገትና ብልፅግና ያመጣል ብሎ እንደማምን እና ከትራንስፎርሜሽን እቅዱ ውይይት በፊት መሰረታዊ ጥያቄዎች መፍትሄ እንዲያገኙና የውይይት ቅድሚያ እንዲሰጣቸው ጠይቋል፡፡

መንግስት መስከረም 28ና 29/2008 ዓ.ም በትራንስፎርሜሽን እቅዱ ላይ ውይይት ለማድረግ በኢ.ሲ.ኤ አዳራሽ ሀገራዊ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን የጋበዘ ሲሆን ሰማያዊ ፓርቲ 20 አባላቱን በውይይት እንዲያሳትፍ በደብዳቤ ተጠይቋል፡፡


Tuesday, 6 October 2015

የኃይለማርያም ካቤኔ አባላት ታወቁ * ሬድዋን ወደ ወጣቶች እና ስፖርት ሚ/ር ተገፉ * ሶፍያን አህመድ ተሰናበቱ * ሕወሓት አሁንም የአንበሳውን ድርሻ ይዟል



(ዘ-ሐበሻ) የሕዝብ ተወካዮች የሌሉበት የኢህ አዴግ ፓርላማ ዛሬ ተሰብስቦ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ያቀረቡትን የካቢኔ አባላት አጸደቀ:: በዚህ ካቢኔ ውስጥ አሁንም ሕወሓት ዋና ዋና የስልጣን ቦታዎችን ይዟል:: የውጭ ጉዳይ ሚኒስተርነቱ; ኢኮኖሚው በሕወሓት ስር እንዲቆይ ሲደረግ አሁን ደግሞ በተጨማሪም አቶ ሬድዋን ሁሴን ይመሩት የነበረውን የመንግስት ኮሙዩንኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ሀላፊ ሚኒስትር ቦታም ወስዷል:: በዚህም ቦታ ላይ የሕወሓቶ አቶ ጌታቸው ረዳ ተሹመዋል:: ለረዥም ጊዜ የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር ሁነው ሲሰሩ የቆዩት አቶ ሶፍያን አህመድ በአቶ አብዱላዚዝ መሀመድ ተተክተዋል::
የሕወሓቱን የካዛንቺሱን መንግስት የሚላላኩት የካቤኔ አባላቱ ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል::

አቶ ደመቀ መኮንን – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የማህበራዊ ዘርፍ ክላስተር አስተባባሪ
ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል – በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
ወይዘሮ አስቴር ማሞ – በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ እና የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ ሲራጅ ፈጌሳ – የመከላከያ ሚኒስትር
ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም – የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
አቶ ካሳ ተክለብርሃን – የፌደራል ጉዳዮችና አርብቶ አደር አካባቢ ልማት ሚኒስትር
አቶ ጌታቸው አምባዬ – የፍትህ ሚኒስትር
አቶ አብዱላዚዝ መሀመድ – የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር
አቶ ተፈራ ደርበው – የእርሻ እና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ ስለሺ ጌታሁን – የእንሰሳትና የዓሳ ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ አህመድ አብተው – የኢንዱስትሪ ሚኒስትር
አቶ ያዕቆብ ያላ – የንግድ ሚኒስትር
አቶ አብይ አህመድ – የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
አቶ ወርቅነህ ገበየሁ – የትራንስፖርት ሚኒስትር
አቶ ሙኩሪያ ሀይሌ – የከተማ ልማት እና ቤቶች ሚኒስትር
ዶክተር አምባቸው መኮንን – የኮንስትራክሽን ሚኒስትር
አቶ ሞቱማ መቃሳ – የውሃ፣ መስኖ እና ኤሌክትሪክ ሚኒስትር
አቶ ሽፈራው ሽጉጤ – የትምህርት ሚኒስትር
አቶ ቶሎሳ ሻጊ – የማዕድን፣ የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስትር
ዶክተር ከሰተብርሀን አድማሱ – የጤና ጥበቃ ሚኒስትር
አቶ አብዱልፈታህ አብዱላሂ – የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር
ኢንጂነር አይሻ መሀመድ – የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር
ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ -የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ሚኒስትር
ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም – የአካባቢ ደን ልማት እና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር
አቶ ሬድዋን ሁሴን – የወጣቶች እና ስፖርት ሚኒስትር
ወይዘሮ ደሚቱ ሀምቢሳ – የመንግስት የልማት ድርጅቶች ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።

በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሚኒስትር ማዕረግ የካቢኒ አባል የሆኑ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ሹመትን ለምክር ቤቱ አቅርበው አስፀድቀዋል።

በዚህም መሰረት
አቶ በከር ሻሌ – የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬከተር
አቶ ጌታቸው ረዳ – የመንግስት ኮሙዩንኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ሀላፊ ሚኒስትር
አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ – የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር
ዶክተር ይናገር ደሴ – የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ተሹመዋል።