Thursday, 24 July 2014

የጥቁር ሽብር ሂደት እና የጋዜጠኛ አብይ አፈወርቅ መልዕክት


(ኢ.ኤም.ኤፍ) ለዛሬው ወደ እስር ቤት አካባቢ እንወስዳችኋለን። መቼም በኢትዮጵያ የሚገኙ እስር ቤቶች ሰውን ለማረም ሳይሆን፤ በአመለካከት የተለየን ሰው ለማሰቃየት ተብለው የተሰሩ ነው የሚመስለው። በአሁኑ ወቅት ሰርቆ እና ሰው ገድሎ እስር ቤት ከገባ ሰው ይልቅ ኢህአዴግን ወቅሶ የጻፈ እና የተናገረ ሰው ብዙ ስቃይ እንደሚደርስበት ምንም መጠያየቅ ወይም መረጃ መቀያየር አያስፈልግም። በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ እነዚህ ሁሉ ነገሮች የሚደረጉት በህግ ሽፋን ነው። የህጉም አንቀጽ “ሽብርተኝነት” መሆኑ በግልጽ ተደንግጎ በነጋሪት ጋዜጣ ላይ ወጥቷል። ይህ መንግስት በህዝቡ ላይ የሚያደርሰው ጥቃት “ጥቁር ሽብር” የሚል ስያሜን አግኝቷል። እናም የሰሞኑ የጥቁር ሽብር ሰለባዎችን ጉዳይ እናስነብባችሁ እና በመጨረሻም አንድ ቅንብር እንጋብዛችኋለን።

በቅድሚያ አቤት ያደረሰንን አዲሰ መረጃ እናካፍላችሁ። በቅርቡ የታሰሩትን የኢህአዴግ ተቃዋሚዎች አስመልክቶ እንዲህ ይላል።
ወያኔ በህገ ወጥ እስር በማእከላዊ እያሰቃያቸው የሚገኙት የሺዋሰ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ፣ ሃብታሙ አያሌውና ዳንኤል ሺበሺ በተለያዩ ጨለማ ክፍሎች ከየብቻ ታስረው እንደሚገኙና ሌሊት ሌሊት ከፍተኛ ድብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሚገኝ ለእስር ቤቱ ቅርብ ከሆኑ ምንጮች ያገኘኋቸው መረጃዎች አረጋግጠውልኛል፡፡ እነዚህ ሰላማዊ ታጋዮች በየቀኑ በሚደረግባቸው ድብደባ እና ስቃይ ምክንያት የሰውነታቸው ክብደት በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የሙስሊሙ ድምጽ የሆነው ቢ.ቢ.ኤን “መንግስት በኮሚቴዎቻችን ቤተ ሰቦች ላይ የተለያየ ጥቃት እና በደል እያደረሰ ነው፡ በማለት

በጥይት የተመታው የኡስታዝ ያሲን ኑሩ ወንድም ወደ ማእከላዊ የተወሰደ መሆኑን እንዲህ ሲል መረጃውን ለቋል።
ጁምዓ ሐምሌ 11 ቀን 2006 የመንግስት ሃይሎች በአንዋር መስጂድ በሰላማዊ መንገድ ድምጹን ሊያሰማ የተሰባሰበው ህዝበ ሙስሊም ላይ በወሰዱት ኢ-ሰብኣዊ የ‹‹ጥቁር ሽብር›› የሃይል እርምጃ በጥይት የተመታው የኡስታዝ ያሲን ኑሩ ወንድም ወደ ማእከላዊ ተወሰደ::
BBN ቢቢኤን የናንተው ድምፅ

በመጨረሻም የሙያ ባልደረባችን የሆነው ጋዜጠኛ አብይ አፈወርቅ ዛሬ ከአውስትራልያ የላከልን መልእክት በኢትዮጵያ ውስጥ እየደረሰ ያለውን ጥቁር ሽብር በዝርዝር ገልጿል።

በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጸሙ አሰቃቂ የማሰቃያ (torture) አይነቶችን በሚመለከት የተጠናቀረውን ልዩ ዝግጅት ጋዜጠኛ አቢይ አፈወርቅ (አውስትራሊያ -ሲድኒ) እንዲህ ያቀርበዋል።






41 organizations call for release of bloggers, jornalists

Washington, D.C.: Today, Freedom Now joined 40 other human rights and civil society organizations in a letter to Ethiopian Prime MinisterHailemariam Desalegn expressing grave concern at the continued targeting of journalists and bloggers on terrorism charges. The letter, also joined by organizations such as Human Rights Watch, Amnesty International, the PEN American Center, and the Committee to Protect Journalists, highlighted the recent terror charges laid against seven bloggers associated with the Zone 9 website (one in absentia) and three independent journalists in Ethiopia.
In calling on the Prime Minister to facilitate the immediate release of those writers detained under the widely-criticized 2009 Anti-Terrorism Proclamation, the letter (below) noted that previous prosecutions under the same law have been found by international institutions, such as the UN Working Group on Arbitrary Detention, to violate Ethiopia’s obligations under international law. In closing, the regional and international organizations urge the Prime Minister to facilitate the immediate release all Ethiopians wrongly detained on terrorism charges and amend the law so that it complies with international human rights standards.
###
Prime Minister Hailemariam Desalegn
Federal Democratic Republic of Ethiopia
Office of the Prime Minister
P.O. Box 1031
Addis Ababa, Ethiopia
24 July 2014
Re: Detained Journalists and Bloggers
Dear Prime Minister Hailemariam Desalegn,
We write to you to express our grave concern regarding the terrorism charges laid against seven bloggers associated with the “Zone 9” website and three independent journalists in Ethiopia. Ethiopia is a party to the International Covenant on Civil and Political Rights and the African Charter on Human and Peoples’ Rights—which both expressly protect the right to freedom of expression. We therefore urge your government to fulfill its obligations under international law and release all individuals who have been arbitrarily detained in violation of their fundamental rights.
As you may be aware, six of the bloggers (Zelalem Kibret, Atnaf Berahane, Natnael Feleke, Mahlet Fantahun, Befeqadu Hailu, and Abel Wabela) and the three journalists (Tesfalem Waldyes, Asmamaw Hailegeorgis, and Edom Kassaye) were arrested in late April, shortly after it was announced that the Zone 9 website would resume its activities after suspending operations because of increasing harassment and surveillance. All nine detainees were subsequently held for nearly three months before any specific allegations were presented or formal charges filed against them. Most concerning, however, are reports that some of the detainees have complained of serious mistreatment by investigators and that defense lawyers and their clients have been excluded from some of the proceedings.
Recent reports now indicate that the detained bloggers and journalists have been charged under the widely-criticized 2009 Anti-Terrorism Proclamation, including provisions that provide for the death penalty, in addition to charges of committing “outrages against the constitution.” A seventh blogger, Soleyana Shimeles, was also charged in absentia. In accordance with the requirements of both Ethiopian and international law, we call on you to ensure that all allegations of torture or other forms of ill-treatment are promptly investigated and that no statements obtained through such means are admitted in court. Further, we call on you to ensure that the detainees have full access to the assistance of legal counsel and that the proceedings related to this case are open to the public, the media, and members of the diplomatic community.
Unfortunately, these prosecutions are only the most recent example of a worrying pattern. Outspoken Ethiopian journalists Eskinder Nega, Reeyot Alemu, and Woubshet Taye have all received long prison terms under the 2009 Anti-Terrorism Proclamation, in trials marred by procedural flaws. Similarly, opposition activists including Andualem Arage have received sentences of up to life imprisonment on such grounds.
While your office has asserted that the prosecution of these individuals is unrelated to their work as journalists, independent inquiries have found that this is not the case. For example, the United Nations Working Group on Arbitrary Detention held that the imprisonment of Mr. Nega violated Ethiopia’s obligations under international law and requested his immediate release. In addition to procedural violations, the Working Group found that the detention of Mr. Nega resulted directly from his exercise of free expression and that the overly broad offenses established by the 2009 Anti-Terrorism Proclamation constituted “an unjustified restriction on expression rights and on fair trial rights.” Despite such a finding, however, Mr. Nega remains in prison.
Other international bodies have similarly criticized your country’s Anti-Terrorism Proclamation for being overly broad and a tool through which freedom of expression is limited. The African Commission on Human and Peoples’ Rights adopted a resolution in 2012 stating that it was “gravely alarmed by the arrests and prosecutions of journalists and political opposition members, charged with terrorism and other offences, including treason, for exercising their peaceful and legitimate rights to freedom of expression and freedom of association.” This message reinforced an earlier statement by five United Nations special procedure mandate holders, including the Special Rapporteur on Counter-Terrorism and Human Rights, which expressed their “dismay at the continuing abuse of anti-terrorism legislation to curb freedom of expression in Ethiopia.” During Ethiopia’s Universal Periodic Review earlier this year, similar concerns were raised by a number of countries, including security allies of Ethiopia such as the United States of America.
Despite these clear findings that the targeting of writers under the 2009 Anti-Terrorism Proclamation is inconsistent with Ethiopia’s international obligations, prosecutors have now charged the seven Zone 9 bloggers and three independent journalists under that very law. As a result, they face exceedingly long prison sentences or even death. Such a practice violates international law and threatens to undermine the legitimacy of international security efforts in the region.
In light of these serious concerns, we urge you to facilitate the immediate release of all journalists and bloggers imprisoned under the 2009 Anti-Terrorism Proclamation and to revise the Proclamation to comply with regional and international human rights standards.
Sincerely,
1.    Amnesty International
2.    ARTICLE 19 Eastern Africa
3.    Central Africa Human Rights Defenders Network (REDHAC), Central Africa
4.    CIVICUS: World Alliance for Citizen Participation
5.    Civil Rights Defenders, Sweden
6.    Coalition pour le Développement et la Réhabilitation Sociale (CODR UBUNTU), Burundi
7.    Committee to Protect Journalists
8.    Community Empowerment for Progress Organization (CEPO), South Sudan
9.    Conscience International (CI), The Gambia
10.    East and Horn of Africa Human Rights Defenders Project
11.    Egyptian Democratic Association, Egypt
12.    Electronic Frontier Foundation
13.    Ethiopian Human Rights Project (EHRP)
14.    Elma7rosa Network, Egypt
15.    English PEN
16.    Freedom Now
17.    Front Line Defenders, Dublin
18.    Human Rights Watch
19.    International Women’s Media Foundation (IWMF)
20.    Ligue des Droits de la personne dans la region des Grands Lacs (LDGL), Great Lakes
21.    Ligue Iteka, Burundi
22.    Maranatha Hope, Nigeria
23.    Media Legal Defence Initiative
24.    National Civic Forum, Sudan
25.    National Coalition of Human Rights Defenders, Kenya
26.    Niger Delta Women’s movement for Peace and Development, Nigeria
27.    Nigeria Network of NGOs, Nigeria
28.    Paradigm Initiative Nigeria, Nigeria
29.    PEN American Center
30.    PEN International
31.    Réseau africain des journalistes sur la sécurité humaine et la paix (Rajosep), Togo
32.    Sexual Minorities Uganda (SMUG), Uganda
33.    South Sudan Human Rights Defenders Network (SSHRDN), South Sudan
34.    South Sudan Law Society, South Sudan
35.    Tanzania Human Rights Defenders Coalition, Tanzania
36.    Twerwaneho Listeners Club (TLC), Uganda
37.    Union de Jeunes pour la Paix et le Développement, Burundi
38.    WAN-IFRA (The World Association of Newspapers and News Publishers)
39.    West African Human Rights Defenders Network (ROADDH/ WAHRDN), West Africa
40.    Zambia Council for Social Development (ZCSD), Zambia
41.    Zimbabwe Human Rights NGO Forum, Zimbabwe

Source: Addisvoice

Wednesday, 23 July 2014

ኢሕአዴግ ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን በሽብርተኝነት መወንጀሉን እንዲያቆም መድረክ ጠየቀ


የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) ገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ ሰላማዊ ታጋዮችን በሽብርተኝነት መወንጀሉን እንዲያቆም ጠየቀ፡፡
መድረክ ለሪፖርተር በላከው መግለጫ ኢሕአዴግ ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን እያሰረና እያሰቃየ ያለው በአምባገነናዊ አገዛዝ ለመጠቀል የነበረው ምኞት ሥጋት ውስጥ መውደቁን በመረዳቱ እንደሆነ አመልክቷል፡፡
ኢሕአዴግ እያካሄደ ባለው የእስር ዕርምጃ የመድረክ አባል የሆነው የዓረና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የመድረክ ጠቅላላ ጉባዔ አባል የሆኑት አቶ አብርሃ ደስታ ከሚኖሩበትና ከሚሠሩበት መቀሌ ከተማ ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ መደረጉን መግለጫው አመልክቷል፡፡ ከሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ የታሰሩት አቶ አብርሃ በቤተሰቦቻቸውም ሆነ በጓደኞቻቸው እንዲጎበኙ አለመፈቀዱንም መግለጫው ያትታል፡፡
ከአቶ አብርሃ ደስታ በተጨማሪ የአንድነት አመራር አባላት የሆኑትን የአቶ ሀብታሙ አያሌውና አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ እንደዚሁም የሰማያዊ አመራር አባል የሆኑት የአቶ የሺዋስ አሰፋን እስርም መድረክ ተቃውሟል፡፡
ገዥው ፓርቲ ከወሰደው የፖለቲካ ፓርቲ አመራርና አባላት እስር ጋር በአገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች የሚገኙ አባላቱ ለእስር፣ ስቃይና እንግልት መጋለጣቸውንም መድረክ አስታውቋል፡፡ በተለይም በትግራይና በኦሮሚያ ክልሎች የሚገኙ አባላቱ ላይ እየደረሰ ያለው እስርና ግፍ እየተስፋፋ መሄዱ፣ አገሪቱ ውስጥ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት ጥያቄ ውስጥ እንደሚከተው አስገንዝቧል፡፡
መድረክ የኢሕአዴግ ዕርምጃ በቀጣይ ዓመት ከሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ጠቁሞ፣ ዕርምጃው አስቀድሞ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችንና እንቅስቃሴያቸውን ለማዳከም ያለመ እንደሆነ አስታውቋል፡፡ ‹‹ዕርምጃዎቹ የጠቅላይነትና ብቸኛ ገዥ ፓርቲነት ምኞት ነፀብራቆች ናቸው፤›› ያለው መግለጫው፣ የአገሪቱን ውስብስብ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ችግሮችን ለመፍታት ውይይትን የገፋ ዕርምጃ እንደማይጠቅም አመልክቷል፡፡
ፓርቲው በመጨረሻም ኢሕአዴግ በሰላማዊ መንገድ የመቃወም ሕገ መንግሥታዊ መብቶችን በመግፈፍ የሚፈጽማቸውን የማሰርና የማሰቃየት ዕርምጃዎች እንዲያቆምና ሰላማዊ ታጋዮችን በአስቸኳይ እንዲፈታ ጠይቋል፡፡
Source: Zehabesha

Tuesday, 22 July 2014

የአዲስ ጉዳይ ፎቶ ጋዜጠኛ በፖሊስ እስር ላይ ናት

አዲስ ጉዳይ መጽሄት ዛሬ እንዳሳወቀው ከሆነ; ላለፉት 3 አመታት የመጽሄቱ ፎቶግራፍ አንሺ የሆነችው አዚዛ መሃመድ አርብ እለት በስራዋ ላይ እያለች በፖሊስ ተይዛ በ እስር ላይ መሆኗን የአዲስ ጉዳይ መጽሄት ዝግጅት ክፍል እንዲህ በማለት በዝርዝር ሁኔታውን ገልጿል:: ላለፉት ሶስት ዓመታት በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ በፎቶ ጋዜጠኝነት በመስራት ላይ ያለችው ፎቶ ጋዜጠኛ አዚዛ መሐመድ አርብ ሐምሌ 11 ቀን 2006 ዓ.ም አንዋር መስጂድ ተፈጥሮ የነበረውን ሁከት በተመለከተ ፎቶ ዘገባ ለመስራት ወደስፍራው በተንቀሳቀሰችበት ወቅት በጸጥታ ሃይሎች ተይዛ ታስራለች።
የአዲስ ጉዳይ ባልደረቦች የአዚዛ ስልክ ዝግ መሆኑን ተከትለው በጸጥታ ሃይሎች ተይዛ ታስራ ሊሆን እንደሚችል ባደረባቸው ጥርጣሬ በተለያዩ የፖሊስ ጣቢያዎች ፍለጋ ሲያደርጉ ከቆዩ በኋላ እሁድ ሐምሌ 13 ቀን 2006 ዓ.ም ቀድሞ 3ኛ ተብሎ በሚጠራውና ወደሰሜን ሆቴል በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኘው አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እስር ላይ እንደምትገኝ ማረጋገጥ ችለዋል።
ፎቶ ጋዜጠኛ አዚዛ መሐመድ አርብ እለት እስከ ቀኑ 9፡00 ሰዓት ድረስ በመስጊድ አካባቢ በሥራ ላይ እንደነበረችና ከዚህ ሰዓት በኋላ ግን ስልኳ ዝግ እንደሆነ ነው አዲስ ጉዳይ የተገነዘበው።የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ ባልደረቦች የአዚዛ መሐመድ በእስር ላይ መሆን በእለቱ ሊፈልጓት ለሄዱት የመጽሄቱ አባላት አረጋግጠዋል።ቅዳሜ ዕለት ፍርድ ቤት ቀርባ እንደነበር ቢናገሩም ፎቶ ጋዜጠኛዋ የተያዘችበትን ምክንያት ግን ከመግለጽ ተቆጥበዋል።
የአዚዛ መሃመድ መርማሪ ፖሊስ ለአዲስ ጉዳይ ባልደረቦች “ቅዳሜ ሐምሌ 12 ቀን 2006 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ቂርቆስ ክፍለከተማ ምድብ ችሎት መቅረቧንና ፖሊስ በጠየቀው የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ምክንያትም ለሐምሌ 17 ቀን 2006 ዓ.ም መቀጠሯን” ተናግረዋል።አዲስ ጉዳይ በስም ወደተጠቀሰው ፍርድ ቤት በመሄድ ጉዳዩን ሲያጣራም መርማሪው የተናገሩት ትክክል መሆኑንና አዚዛ ከሌሎች ብዛት ካላቸው ግለሰቦች ጋር ለተባለው ቀን በቀጠሮ እንድትቀርብ ችሎቱ መወሰኑን መገንዘብ ችሏል።እንደፖሊስ ሁሉ የፍርድ ቤቱ ሰራተኞችም አዚዛ የተጠረጠረችበትን ወንጀል ለመግለጽ ፍቃደኛ አልነበረም።
አዲስ ጉዳይ መጽሄት አዚዛ መሃመድ በዕለቱ ሙያዋ ከሆነው የፎቶ ጋዜጠኝነት ሥራዋ ውጪ በየትኛውም የወንጀል ተግባር ላይ ተሳታፊ ሆናለች የሚል እምነት የለውም።አዚዛ መሃመድ ከባህሪዋ እና ለሙያዋ ካላት ፍቅር አኳያ በምትሰራበት አዲስ ጉዳይ መጽሄት የምትታወቀው ዘወትር የታዘበቻቸውንና ለዜና ይሆናሉ ብላ የምታስባቸውን ማናቸውንም ክስተቶች በፎቶግራፍ በማስቀረት የጋዜጠኝነት ተግባሯን ህጋዊነትን በተከተለ መንገድ ብቻ በማከናወኗ ነው።
በአብዛኛው ጥበባዊ በሆኑ ዝግጅቶች ላይ የፎቶ ጋዜጠኝነት ስራዋን የምታከናውነው አዚዛ የፎቶ ጋዜጠኝነት ሙያዋ የሚጠይቀውን የረጅም ጊዜ ትምህርት ከመውሰዷ ባሻገር በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስነጥበብ ትምህርት ቤትም የስዕል ትምህርት ተከታትላለች።
በባህሪዋ እውነተኛ እና ስነምግባር ያላት ባለሙያ መሆኗን ዝግጅት ክፍሉም ይሁን በስራ አጋጣሚ አዚዛን የሚያውቋት የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ባልደረቦችም ምስክርነታቸውን የሚሰጡላት ፎቶ ጋዜጠኛ ናት።
የአዲስ ጉዳይ መጽሄት በፎቶ ጋዜጠኛ ባልደረባው ላይ ምርመራ በማካሄድ ላይ እንደሆነ የገለጸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ክፍል አዚዛ በፖሊስ የተያዘችበትን ምክንያት በተመለከተ ዝግጅት ክፍሉ ላቀረበው ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጠው ይጠይቃል። ከዚህ በተጨማሪም በሃገሪቱ ህገመንግስት መሰረት የተያዙ ሰዎች የሚኖራቸውን መብት በማክበር ከስራ ባልደረቦቿ እና ከቤተሰቦቿ ጋር እንድትገናኝ እንዲያደርግ እንዲሁም የሚደርስባትን መጉላላት ለማስቀረት በተቻለ ፍጥነት የተያዘችበትን ምክንያት በማጣራት ከወንጀል ነጻ መሆኗን አረጋግጦ በነጻ ትለቀቅ ዘንድ ውሳኔ እንዲያሳልፍ ጥያቄ ያቀርባል።

Monday, 21 July 2014

በአብርሃ ደስታ ቤተሰብ ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ ከልክ አልፏል

(ኢ.ኤም.ኤፍ) ብዙዎች እንደሚያውቁት አብርሃ ደስታ በትግራይ የሚገኘው የአረና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ነው። አረና ፓርቲ የህወሃት ተፎካካሪ ፓርቲ በመሆኑ፤ ወያኔዎች በአባላቱ ላይ ግፍ እና በደል ሲያደርሱ ቆይተዋል። አብርሃ ደስታም ትግራይ ሆኖ በዚያ የሚደረገውን ስር አት አልበኝነት በማጋለጡ፤ የትግራይን ህዝብ እንደካደ ተደርጎ ከድብደባ ጀምሮ የእስር እንግልት ደርሶበታል።  አሁንም ማዕከላዊ እስር ቤት ውስጥ መኖሩ ይነገራል እንጂ፤ ህዝብ እንዲያየውም ሆነ እንዲጠይቀው አልተፈቀደም። ፍርድ ቤት ያቀረቡትም ሰውነቱ በጣም ደክሞ እና ተጎሳቅሉ ከእኩለ ለሊት በኋላ ነው።
Abraha Desta
Abraha Desta

ይህ በአብርሃ ደስታ ላይ የሚደርሰው ስቃይ እና መከራ እንዳለ ሆኖ፤ እሱ ከታሰረ ጀምሮ ደግሞ በቤተሰቡ ላይ ከፍ ያለ ግፍ እየተፈጸመ መሆኑን ከትግራይ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። እንዲህ ይነበባል።
• የአብርሀ ታናሽ እህትና የጤና ባለሙያ (የጤና መኮንን/ HO) የሆነችው ተኽለ ደስታ የኢህአዴግ አባልም ሁና የአብርሀ እህት ስለሆነች ብቻ ከስራ ተባራለች፣ ቢሮ እንዳትገባም በዘበኞች ተከልክላለች፣ መልቀቂያም ከልክለዋታል፤ ቀጣዩ ውሳኔም ቁጭ ብላ እንድትጠባበቅም ተነግሯታል፡፡
• ሁለቱ አዲስ ምሩቃን ወንድሞቹ ኣረጋዊ ደስታና ገ/ገርግስ ደስታ በከፍተኛ ብልጫ ሰቅለው የተመረቁ ቢሆንም ዩኒቨርሲቲው እነሱን ላለመቅጠርና ከነሱ ያነሰ ነጥብ ያላቸውን መቅጠሩ ተሰምቷል፤ አዋሳ ዩኒቨርሲቲም ተወዳድረው እንዳለፉ ሲነገራቸው ቆይቶ ሌሎች ከነሱ በታች የነበሩ ሲጠሩ እነሱ እስካሁን አልተጠሩም፡፡
• እናቱ ሙሉ ኣለማየሁ “አንቺ የዐረናው እናት፣ እንቺ የከሀዲው እናት ይህ የህ.ወ.ሐ.ት ምድር ነው- ወዴትም ውጪልን” ድረስ የሚደርሱ ከፍተኛ በደሎች፣ ለቃላት የከበዱ ግፎች እየተፈፀሙባት ነው፤
• ሌሎች ዘመድ አዝማዶቹም በተዋረድ በከፍተኛ ጭንቅ ውስጥ ገብተዋል፣ ነገ በነሱ ላይም ምን እንደሚመጣ ስጋት ገብቷቸዋል፤
• ጀግናን መውለድ እዳው ብዙ ነው፤ በተለይም ደግሞ እዚህ በጭቆናዋ ምድር- በትግራይ! — ይላል የዘገባው መጨረሻ።

Sunday, 20 July 2014

Ethiopia-stop using “anti-terrorism” law to stifle dissent.

Michael Aboye


In 2009 a controversial anti-terrorism law (Proclamation No. 652/2009) was established in Ethiopia. The law criminalises any contact or reporting that encourages individuals or groups which the government labelled ‘terrorists.’  Since then, opposition members and journalists are convicted by the broad and ambiguous anti-terrorism law.

That proclamation has been thoroughly condemned and criticized by all of the major international human rights organization. For instance, Human Rights Watch criticized that “law” for providing “an extremely broad and ambiguous definition of terrorism that could be used to criminalize non-violent political dissent and various other activities that should not be deemed as terrorism.” Even the U.S. State Department expressed its disapproval of the “extremely harsh and politicized use of Ethiopia’s anti-terrorism law” in persecuting political opponents.

Since Ethiopia’s anti-terrorism law was adopted in 2009, the independent media have been decimated by politically motivated prosecutions under the law. The government has systematically thwarted attempts by journalists to establish new publications. Blogs and Internet pages critical of the government are regularly blocked, and in 2012 printing houses came under threat for printing publications that criticized the authorities.
Since the laws’ passing, what has precipitated is exactly what rights groups predicted. In less than four years, over 200 people have been arrested under the anti-terrorism law and more than 35 journalists and opposition leaders had been convicted of terrorism.

One of the journalists sentenced under the law who remain in prison is Eskinder Nega , a veteran Ethiopian journalist. He had been detained numerous times, and was sentenced in July 2012 to 18 years in prison for conspiracy to commit terrorist acts, as well as participation in a terrorist organization. The United Nations Working Group on Arbitrary Detention, a panel of independent experts, concluded in November 2013, that Eskinder’s imprisonment was arbitrary and “a result of his peaceful exercise of the right to freedom of expression.”

Human Rights Watch has repeatedly raised concerns about the anti-terrorism law’s overly broad definition of “terrorist acts.” The law’s provisions on support for terrorism contain a vague prohibition on “moral support” under which only journalists have been convicted.

The latest victims of this repressive policy regime seem to be six young professionals that are part of a group of bloggers called Zone 9 and three journalists. A group of Ethiopian bloggers and journalists detained for nearly three months have been charged with “terrorism” for having links to outlawed groups and for planning attacks.

On May 2, this year, the UN High Commissioner for Human Rights, Navanethem  Pillay, expressed deep concern at the arrest of these bloggers and journalists. The High Commissioner called for a reform of the country’s anti-terrorism legislation to come into line with international human rights law and stated that
“The fight against terrorism in Ethiopia cannot be used as an excuse to intimidate and silence journalists, bloggers, activists and members of civil society organizations.”|

The United States said it is deeply concerned by the Ethiopian Federal High Court’s decision to press charges against six bloggers and three independent journalists under the Anti-Terrorism Proclamation.
Human rights watch reportedly said the Ethiopian government should immediately drop politically motivated charges brought against 10 bloggers and journalists on July 17, 2014, under the country’s deeply flawed anti-terrorism law.

As many human rights groups have said, Ethiopia’s anti-terrorism “law” is merely a convenient mechanism for “politically motivated trials and convictions of opposition figures, activists, journalists, and bloggers, as well as increased restrictions on print media.”  It is State terrorism through the use of “anti-terrorism law” and violation of the rule of international law. The “war on terrorism” should not be a war on international law where anti-terrorism efforts become a convenient justification for thuggery.

The Ethiopian regime should cease using its overly broad anti-terrorism law against journalists and peaceful political activists. International actors should pay close attention to the recent, intensified crackdown of freedom of expression. Expressing critical views is not a terrorist act.  The “Terrorism” charges against bloggers and journalists are politically motivated. The fight against terrorism in Ethiopia cannot be used as an excuse to intimidate, silence and detain journalists and activists. Using “anti-terror” law to stifle peaceful dissent has to stop.

Journalism is not a crime!

የኢትዮጵያው ጓንታናሞ ቤይ ‹‹ ማዕከላዊ ››


ማዕከላዊ
አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ሂዩማን ራይትስ ዎች እንዳለፉት አመታት ሁሉ የኢትዮጵያን መንግስት የሚያስቆጣ ባለ 70 ገጽ ሪፖርት ከሁለት ሳምንታት በፊት ይፋ አድርጓል፡፡ የተቋሙን ሪፖርት ከሌላው ጊዜ የተለየ የሚያደርገው በአንድ ርዕሰ ጉዳይ በአንድ ተቋም በማጠንጠኑ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ከሚገኙ የወንጀል ምርመራ ማዕከሎች መካከል በአዲስ አበባ ዕምብርት በሚገኘው ማዕከላዊ ተጠርጣሪዎች ግርፋት፣ማሰቃየትና ድብደባ እንደሚፈፀምባቸው ሪፖርቱ አትቷል፡፡
አሜሪካ በሁለቱ የኒውዮርክ መንትያ ህንጻዎቿ ላይ በአልቃይዳ የተቀነባበረ ጥቃት ከተሰነዘረባት በኋላ ‹‹ሽብርተኛ›› በማለት የሰየመችውን ቡድን አባላት ከምድረ ገጽ ለማጥፋት በጆርጅ ቡሽ ፊት አውራሪነት የሽብር ቡድኑ ዋነኛ መጠለያ ያለቻችትን አፍጋኒስታንን ወረረች፡፡ በዘመቻው በቁጥጥር ስር የዋሉ የአልቃይዳ አባላትና ተጠርጣሪዎች በጄኔቭ ስምምነት መሠረት በህግ የመዳኘት መብት እንዳያገኙ ለማድረግ የቡሽ አስተዳደር ከግዛቱ ውጪ በኩባ ድንበር የሚገኘውን ጓንታናሞ ቤይን ከዛሬ አስር አመታት በፊት ከጦር ካምፕነት ወደ ማሰቃያ ማዕከልነት አሸጋገረው፡፡
‹‹በሽብርተኝነት›› ተጠርጥረው ወደ ጓንታናሞ ቤይ እንዲገቡ የተደረጉ ተጠርጣሪዎች የዜግነት ስብጥር የሚበዛበት ቢሆንም አንዳንድ መረጃዎች የሚበዙት ተጠርጣሪዎች አፍጋናዊያን፣ ኢራቃዊያን፣ የመናዊያን፣ ሊቢያዊያንና ግብጻዊያን ስለመሆናቸው ይጠቁማሉ፡፡ ከታሳሪዎቹ መካከል 99 ከመቶ ያህሉም የሙስሊም እምነት ተከታዮች ናቸው፡፡
አሜሪካ በህገ መንግስቷ ተጠርጣሪዎች ዋስትና፣ ጠበቃ፣ ጎብኚና ነጻ የፍትህ ስርዓት እንዲያገኙ ለማድረግ ቃል የገባች ቢሆንም በጓንታናሞ ቤይ የተጣሉ ተጠርጣሪዎች ለረዥም አመታት ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እንዳይታይ፣ ጎብኚዎች እንዳያገኙ፣ ግርፋትና ስነ ልቦናዊ የሆነ ቶርቸር እንዲደርስባቸው በማድረግ ከህገ መንግስቷ የተጣረሰ ኢ ሰብአዊ ድርጊት ስትፈጽምባቸው ቆይታለች፡፡
እስረኞቹን አጋቾቻቸው እጅና እግሮቻቸውን ለ24 ሰዓታት በሰንሰለት በማሰር ሲያሰቃዩአቸው ቆይተዋል፣ በረመዳን የጾም ወቅት እስረኞቹ የሃይማኖታቸውን ትዕዛዝ ለመፈጸም ከምግብ ተከልክለው ወሩን ለማሳለፍ ቢዘጋጁም የማጎሪያው ሃላፊዎች ሀይልን በመጠቀም በቀን ለሁለት ጊዜያት ምግብ እንዲመገቡ በማድረግ ጥቃት ፈጽመውባቸዋል፡፡
የአሜሪካ መንግስት (የቡሽ አስተዳደር) ይህንን ግፍ በጓንታናሞ ቤይ ሲፈጽም የከረመው በገዛ ዜጎቹ ላይ ባይሆንም በሰብአዊ ፍጥረት ላይ የሚደርስን በደል የአገሪቱ ህዝብ በራሱ እንደደረሰ በመቁጠር የቡሽን የበቀል እርምጃ በተለያዩ መድረኮች ሲቃወም ተስተውሏል፡፡
ጥቁር አሜሪካዊው ባራክ ሁሴን ኦባማ ለፕሬዝዳንትነት ያደርጓቸው በነበሩ ቅስቀሳዎች ‹‹ጓንታናሞን›› ከተመረጡ እንደሚዘጉ መግለጻቸውም በአስገራሚ ሁኔታ የአገራቸውን ህዝብ ድጋፍ እንዲያገኙ ረድቷቸዋል፡፡ ኦባማ የማሰቃያ ማዕከሉን ለመዝጋት ፕሬዝዳንት ሆነው ከተመረጡ በኋላ እንቅስቃሴ ቢጀምሩም ከተፎካካሪዎቻቸው ጠንከር ያለ ተቃውሞ ማስተናገዳቸው አልቀረም፡፡ አሁን የኦባማ ምኞት እውን ሆኖ ጓንታናሞ ሙሉ ለሙሉ ሊባል በሚችል መልኩ ተዘግቷል፡፡ ፍትህ ተነፍገው የወታደሮች መጫወቻ ሆነው የቆዩ ተጠርጣሪዎችም በወታደራዊ ፍርድ ቤቶች እንዲቀርቡ ተደርገዋል፣የሚበዙትም ከአልቃይዳ ጋር ምንም አይነት የሚያገናኛቸው መስመር እንደሌለ በመረጋገጡ ከቤተሰቦቻቸው እንዲቀላቀሉ ተደርገዋል፡፡
በኢትዮጵያው ጓንታናሞ ቤይስ?
የዛሬው የአፍሪካ ህብረት ህንጻ የቆመበት መሬት በዘመነ ደርግ ላቅ ያለ የስቃይ ምድር ነበር፡፡ ከርቸሌ ብዙ ሺህ ወጣት ኢትዮጵያዊያንን በልታለች፣ በወታደራዊው መንግስት ላይ ተቃውሞን ያሰሙ ዜጎች በከርቸሌ ፊደል የማይተርከውን ስቃይ አስተናግደዋል፡፡ በኢትዮጵያውያኑ የለቅሶና የደም መሬት ላይ የአፍሪካ መሪዎች አመታዊ ስብሰባቸውን ለማድረግ ሲመጡ በቻይና እርዳታ የተሰራላቸውን ህንጻ ውበት እንጂ በከርቸሌ የፈሰሰው ደም፣ የባከነው አእምሮና የተፈፀመው ግፍ አይታሰባቸውም፡፡ በዘመነ ደርግ ለከርቸሌ እስረኞችን ይመግብ የነበረው የምርመራ ማእከል ደግሞ ማዕከላዊ ነው፡፡
ማዕከላዊን በመገንባት የተቃዋሚዎቻቸውን በአደባባይ ለመገንፈል ያሰፈሰፈ ቁጣ መሸበብ የጀመሩት አጼ ኃይለስላሴ ናቸው፡፡ ንጉሱ ተማሪዎችን፣ አመጽ ያማራቸውን ወታደሮች፣ ስልጣኔ የሸተታቸውን ሰራተኞችና የባላባት ጭሰኛ መሆን የመረራቸውን ገበሬዎች በምስጢር ፖሊሶቻቸው አማካኝነት እያደኑ ማስፈራሪያና ግርፊያ ይፈጽሙባቸው እንደነበር ለዚህ ፊቸር ያናገርኳቸው ሰዎች እማኝነታቸውን ሰጥተውኛል፡፡ ደርግ የንጉሱን ወንበር በመገልበጥ ስጣኑን እንደተረከበ የተነሳበትን ተቃውሞ ለማፈን ከሁሉም የማጎሪያ ካምፖች በተሻለ ማዕከላዊን ስለመጠቀሙ በዛ ያሉ ምስክሮችን መቁጠር ይቻላል፡፡
የኢህአፓ ወጣቶች በማዕከላዊ የሚያውቁትን ምስጢር እንዲያወጡ፣ያልተያዙ ጓደኞቻቸውን እንዲጠቁሙ በሚል በወታደሮች ተደብድበዋል፣ ሴቶቹ ተደፍረዋል፣ በኤሌከትሪክ ሽቦ ተጠብሰዋል፣ ጥፍሮቻቸው በጉጠት እንዲነቀሉ ተደርገዋል፣ ሰውነታቸው ተገልብጦ ውስጥ እግራቸው በበሬ ቆለጥ ተገርፏል፡፡ ድብደባውን መቋቋም ተስኗቸው ይህችን ጨካኝ አለም የተሰናበቱ የት የሌለ ናቸው በማዕከላዊ፡፡የወቅቱ የምርመራ ሰራተኞች ብቃት የሚለካው እየገረፉና እያሰቃዩ በሚያገኙት መረጃ እንጂ መረጃውን ለማግኘት በሚጠቀሙት ፖሊሳዊ የምርመራ ጥበብ አልነበረም፡፡ይህ ጥበብም እነሆ እስካሁን ድረስ እየተወራረሰ ይገኛል፡፡
በ1983 የሰርዓት ለውጥ ተደርጎ ራሱን ነጻ አውጪ በማድረግ የሚቆጥረው ኢህአዴግ ስልጣነ መንግስቱን ሲቆናጠጥ ማዕከላዊ ዑደቱን እንዲያቋርጥ አለመደረጉን በየጊዜው ከማዕከላዊ የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ ፡፡
በ1987 ዓ.ም የፀደቀው ህገ መንግስት ተጠርጣሪዎች ህገ ወጥ ለሆነ አያያዝ እንደማይደረጉ፣ ኢሰብአዊ የሆነ ጥቃት እንደማይደርስባቸው፣ በ48 ሰዓት ውስጥ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ፣ በምርመራ ወቅት የሰጡትን የእምነት ክህደት ቃል በፍርድ ቤት መለወጥ እንደሚችሉ ቢደነግግም በማዕከላዊ እነዚህ ህገ መንግስታዊ መብቶች ሆን ተብለው እንደሚጣሱ በምርመራ ጣብያው ዘግናኝና የሰቆቃ ጊዜያትን ያሳለፉ ሰዎች ይናገራሉ፡፡
ሂዩማን ራይትስ ዎች ላወጣው ሪፖርት እማኝ እንደሆኑ የተነገረላቸው 35 በማዕከላዊ የነበሩ እስረኞችም የተናገሩት ለወራት ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ መቆየታቸውን፣ በጨለማ ቤት መክረማቸውን፣ ከጠያቂዎች ጋር እንዳይገናኙ መደረጋቸውንና በምርመራ ወቅት ግርፋት፣ ማሰቃየትና ማስፈራራቶች ይፈፀምባቸው እንደነበር ነው፡፡
ከሪፖርቱ ውጪ ጀሚል አክበር፣ ስዬ አብርሃ፣ ደበበ እሸቱና ኢንጂነር ኃይሉ ሻወል በጻፏቸው መጻህፍት በማዕከላዊ የምርመራ ማእከል ቆይታቸው ለጆሮ የሚሰቀጥጡ ስቃዮችን ማለፋቸውንና መስማታቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ የመጻሕፍቱ መልእክት አንድና አንድ ነው፡፡ በኢትዮጵያ የመንግስታት ለውጥ ቢደረግም ማዕከላዊ ግን የየስርዓቱን ተቃዋሚዎች፣ ጋዜጠኞችና ተቺዎች ማሰቃ በመሆኑ ቀጥሏል፡፡
ጣውላ፣ ጨለማ ቤትና ሸራተን በማዕከላዊ
በማዕከላዊ የምርመራ ማዕከል እንዲገቡ የተፈረደባቸው ዜጎች ቆይታ ለሚያደርጉባቸው ክፍሎች ተገቢ ነው ያሏቸውን ስያሜዎች አውጥተውላቸዋል፡፡ ጨለማ ቤት እጅግ ቀዝቃዛና ዘና ብሎ ለመተኛት የማያወላዳ የተፈጥሮ አልያም የሰው ሰራሽ ብርሃን አልቦ ነው፡፡ ወደዚህ ክፍል የሚገቡ ሰዎች ቀንና ሌሊት በጨለማ የሚዋጡ በመሆናቸው ሰዓት፣ ቀንና ምሽትን ለመለየት ይቸገራሉ፡፡ የቅንጅቱ ሊቀመንበር የነበሩት ኃይሉ ሻውል በቅርቡ ባሳተሙት መጽሐፍ ለ28 ቀናት ጨለማ ቤት እንዲቆዩ መደረጋቸውን በመጨረሻም መርማሪዎቹ ‹‹መብራት የሚሰራልን አጥተን ነው ይቅርታ›› በማለት አምፑል በማስገባት እንዳበሩላቸው ገልጸዋል፡፡ እንደ ሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት ሪፖርት ከሆነ በዚህ ጨለማ ክፍል የቆዩ ሰዎች ጊዜያቸውን በማጠናቀቅ ወደ ውጪ ሲወጡ ለከፍተኛ የአይን ህመም ይዳረጋሉ፡፡
ጣውላ ቤት የተሻለ ስፋትና አጋር እስረኛ የሚገኝበት ከመሆኑ ባለፈ በጨለማ የተዋጠ ነው፡፡ ቤቱ ከጣውላ የተሰራ በመሆኑም ድምጽ ከየትኛው ክፍል እንደሚመጣ አይታወቅም፡፡ ይህም እስረኞቹ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው እንዲያንጎረጉሩ፣ የመሰላቸውን እንዲናገሩ ይረዳቸዋል፡፡ አንደኛው እስረኛ ለመጸዳዳት ከክፍሉ ወጣ በሚልበት አጋጣሚም ከሌላው እስረኛ ጋር የሚገናኝበት፣ የሚተያይበት በመሆኑም ለታሳሪዎቹ ህይወት እንድትሸታቸው ያደርጋል፡፡ ሸራተን በማዕከላዊ የቅንጦት ክፍል ነው፡፡ የክፍሉ ስፋት በመጠኑ የሚያወላዳ ከመሆኑም በላይ የመብራት ባለቤት ነው፡፡በዛ ያሉ እስረኞች የሚገኙበት በመሆኑም በማዕከላዊ እንደ ቅንጦት ተቆጥሮ ሸራተን ለመሰኘት በቅቷል፡፡ ሸራተን የገቡ እስረኞች በአብዛኛው የምርመራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ በመሆናቸው በጨለማ ቤትና በጣውላ ቤት ያሳለፉትን መከራ እያነሱና እየጣሉ ከሌሎች ታሳሪዎች ጋር ፍርድ ቤት የሚያሳልፍባቸውን ውሳኔ ይጠባበቃሉ፡፡
የመንግስት ምላሽና ሪፖርቶች
ሂዩማን ራይትስ ዎቹ በኢትዮጵያ እስር ቤቶች ኢሰብአዊ ድርጊቶች እንደሚፈጸሙ ሲያጋልጥ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ የመንግስት ኃላፊዎችም ሪፖርቱን ከመንግስት ተቃዋሚዎች የተሰበሰበና እውነታውን የማያሳይ በማለት ከማጣጣል ተቆጥበው አያውቁም፡፡
የአሜሪካ መንግስት /ስቴት ዲፓርትመንት/ በሚያወጣቸው ሪፖርቶች የእስረኞች አያያዝ እንዳሳሰበው የገለጸባቸው አጋጣሚዎች በዛ ያሉ ናቸው፡፡ በ2007 ኤፕሪል በዊኪሊክስ አማካኝነት የወጣ መረጃም በኢትዮጵያ የሚገኙ እስረኞችን ጉዳይ በቅርበት የሚከታተሉት የፕሪዝን ፌሎው ሺፕ መስራች ፓስታር ዳንኤል ለአሜሪካ ኤምባሲ ሰዎች መንግስት በእስረኞች ላይ ግርፋት፣ ማስፈራራትና ማሰቃየት እንደሚፈጽም መናገራቸውን አትቶ ነበር፡፡ በቅርቡ ሂዩማን ራይትስ ዎች ላወጣው ሪፖርት የመንግስት የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ ሽፈራው በጽሁፍ እንዲሁም የመንግስት ኮሚኒኬሽን ምክትል ኃላፊ አቶ ሽመልስ ከማል ለኤኤፍፒ በሰጡት ምላሽ ክሱን አጣጥለውታል፡፡
በማዕከላዊ የወንጀል ምርመራ ቆይታ አድርገው የነበሩት ሁለቱ ስዊዲናዊያን ጋዜጠኞች ማርቲን ሺብዬና ዮሃን ፒርሰን ‹‹ፖሊስ ሁሉም ነገር የሚያልቀው በፍርድ ቤት እንደሆነ ይናገራል፣ ነገር ግን ሁሉም ነገር የሚሆነው በምርመራ ወቅት ነው፡፡ ፖሊስ በሀይል ተጠርጣሪዎች የተጠረጠሩበትን ጉዳይ መፈፀማቸውን እንዲያምኑ ያደርጋል›› ይላሉ፡፡
በሪፖርቱ ዙሪያ ለኤ.ኤፍ.ፒ በእስር ላይ ስለምትገኘው ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ የተናገሩት ወላጅ አባቷና ጠበቃዋ አቶ አለሙ ጌቤቦ ለሦስት ወራት ያህል ልጃቸውን በማዕከላዊ ማየት እንዳልቻሉ በመጥቀስ በእነዚያ 90 ቀናት ውስጥ ከቤተሰብና ከጠበቃዋ ለይተው ምን ሲፈጽሙባት እንደቆዩ እንደማያውቁ ተናግረዋል፡፡ ርዕዮትን ከሦስት ወራት በኋላ እንዲመለከቷት ሲፈቀድላቸው ተጎሳቁላ ማግኘታቸውንና ለዘጠኝ ቀናት ያህል ምግብ ሳትመገብ መቆየቷን መረዳታቸውን መስክረዋል፡፡
በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ወደ ማዕከላዊ የገቡ ሌሎች ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች ከርዕዮት ጋር የሚመሳሰል ታሪክ እንዳላቸው የታሳሪዎቹ ቤተሰቦች ይናገራሉ፡፡
ፓስተር ዳንኤል በእስር ቤቶች ኢሰብአዊ ድርጊት የሚፈጽሙ መርማሪዎች መኖራቸውን መንግስት ከደረሰበት በኋላ የሚበዙትን ከስራ እንዳባረራቸው ለአሜሪካው ዲፕሎማት መናገራቸውን ዊኪሊክስ ቢዘግብም የመረጃ መረቡ ባወጣው ሪፖርት ፓስተሩ ነገሩን ለማድበስበስ ያህል እንደተናገሩት እንደቆጠረባቸው አትቷል፡፡
በምርመራ ላይ የቆዩ ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት በሚቀርቡባቸው አጋጣሚዎች በምርመራ ወቅት ድብደባ፣ ማስፈራራትና ማሰቃየት እንደደረሰባቸው የተናገሩባቸው አጋጣሚዎችም በዛ ይላሉ፡፡ ዳኞች እንዲህ አይነት የመብት ጥሰት አቤቱታ ሲቀርብላቸው ፖሊሶች ላይ ጫን ያለ እርምጃ እንዲወሰድ አለማድረጋቸው የምርመራ ውስጥ ስቃዩ እንዲቀጥል የበኩሉን አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡
የእኛ ኦባማ የት ነው?
የኢትዮጵያ መንግስት ኃላፊዎች የሰብአዊ መብት ተቋማት፣ የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ ድርጅቶች አልያም የአለም ባንክ ለሚያወጧቸው ሪፖርቶች የሚሰጧቸው ምላሾች አንድ ጫፍ የረገጡ ናቸው፡፡ የሪፖርቶቹን መውጣት ተከትሎ ጉዳዩን ለማጣራት ገለልተኛ ቡድን እንዲዘጋጅ የተደረገበት ጊዜ የለም፡፡ ጆርጅ ቡሽም እንዲህ ነበሩ፡፡ በጓንታናሞ ለሚፈጸም የሰብአዊ መብት ጥሰት ጆሮ አልነበራቸውም፡፡ ወታደሮቻቸው ሴት እስረኞችን እንደሚደፍሩ፣ ታሳሪዎችን በረመዳን የጾም ወቅት በኃይል እንዲመገቡ ማድረጋቸው፣ ተጠርጣሪዎች ለወራት ፍትህ ሳያገኙ መቆየታቸው ሲነገራቸው ለመስማት አልፈቀዱም፡፡ በፕሬዝዳንቱ እምነት እየተሰቃዩ የሚገኙት ሰዎች ሳይሆኑ ‹‹ሽብርተኞች›› ናቸው፡፡
ኦባማ ግን እንደ ቡሽ በጭፍን ጥላቻ የታወሩ አልነበሩም፡፡ ጓንታናሞ የሰብአዊ መብት ረገጣ የሚፈፀምበትና አሜሪካ ቆሜለታለሁ ለምትለው ዲሞክራሲ ተቃራኒ መሆኑን በመረዳት ጓንታናሞን ላይከፍቱት ቆለፉት፡፡
የእኛው ማዕከላዊ በእኛው ዜጎች እኛው ላይ ኢ- ህገ መንግስታዊና ኢሰብአዊ ድርጊት የሚፈፀምበት ማዕከል ነው፡፡ በጓንታናሞ አሜሪካዊያኑ የገረፉት፣ ያሰቀዩት አፍጋኑን፣ ግብጻዊውን፣ ኢራቃዊውን፣ አፍሪካዊውን ነው፡፡ በማዕከላዊ መሰቃየቱንና ህገ መንግስታዊ መብቱ እንደተጣሰበት የሚናገረው ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ ኦባማ ጓንታናሞን ስለ አሜሪካዊያን አልዘጉትም፡፡ ስለ ፍትህ እንጂ፡፡ የእኛ ኦባማ ለጊዜው እዚህ ነኝ ባይለንም የመጣ ቀን ግን ማዕከላዊን ስለእኛ ይዘጋዋል፡፡
Source: Zehabesha