Wednesday, 29 July 2015

ኊባማ ዚአፍሪካን ገዢዎቜ እያዋዛ ደቆሳ቞ው! – መስፍን ወልደ ማርያም




ኊባማ በአፍሪካ ኅብሚት ያደሚገው ንግግር ብዙ ጥያቄዎቜን መልሷል፤ ዚኊባማ ጉብኝት ያስኚተለው ጫጫታ ሁሉ መልስ አገኘ፤ ዹሰው ልጆቜ በመሀኹላቾው ምንም ዓይነት ዚአድልዎ ልዩነት ሳይደሚግባ቞ው በሰውነታ቞ው ብቻ በተፈጥሮ ያገኙትን ክብራ቞ውንና መገሣ቞ውን አስኚብሚው መኖር እንዳለባ቞ው በአጜንኊት ተናገሹ፤ ዛሬ ዚአሜሪካኑ ፕሬዚደንት ያደሚገው ንግግር ኚፕሬዚደንትና ጠቅላይ ሚኒስትር ጀምሮ እስኚፖሊሶቜ፣ መርማሪዎቜና አዛዊቻ቞ው፣ እስኚጊር ኃይሉና አዛዊቻ቞ው፣ አስኚዓቃብያነ ሕግና ዳኞቜ፣ እስኚወህኒ ቀት ጠባቂዎቜና አዛዊቜ በዚሥልጣን ተዋሚዱ ላይ ሆነው ዚኢትዮጵያውያንን ዚሰውነትና ዚዜግነት እኩልነት አፈራርሰው በጎሣ መሠሚት ላይ ሊበታትኑት ዚሚሞክሩትን በኃይለኛ ቃላት ኚመሬት በታቜ ኚቶአ቞ዋል፤ ማሰብና ማስተዋል ዹጎደለው፣ ኚአፍንጫ ዚራቀ አመለካኚት ዚሌለበት፣ አገርን ዚሚያጠፋ፣ ኚሰውነት ጎዳና ዚሚያወጣ ዚድንቁርና መንገድ መሆኑን ገልጧል፡፡


ኊባማ ዚኢትዮጵያን ገዢዎቜ ብቻ ሳይሆን ዚአፍሪካን ገዢዎቜ በሙሉ አላግጊባ቞ዋል፤ በሥልጣን ላይ ሙጭጭ በማለታ቞ው፣ በሙስና቞ው፣ በአፈናቾው፣ ልክ ልካ቞ውን ሲነግራ቞ው እፍሚታ቞ውን ውጠው ያጚበጭቡለት ነበር፤ ዚአፍሪካ ገዢዎቜ ሕጉን እንደፈለጉ ዚሚጠመዝዙትን መሳቂያ አድርጓ቞ዋል፤ በአዳራሹ ውስጥ ዚነበሩ ወጣቶቜ ዚኊባማን ንግግር በማድነቅ በጭብጚባና በጩኞት ይገልጹ ነበር፤ ለወግ ብቻ ዹሚደሹግ ምርጫ ዚዎሞክራሲ መግለጫ አይሆንም አለ፤ ዎሞክራሲ ነጻና ትክክለኛ ምርጫን፣ ሀሳብን በነጻነት መግለጜን፣ በነጻነት መደራጀትንና መሰብሰብን ያካትታል፤ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድሚጅቶቜን ማገድና መገደብ ለዎሞክራሲ እንቅፋትና ለእድገት ጾር ነው፡፡

አገዛዞቜ ነጻነትን በማፈናቾው ሁለት ዋና ዋና ዚማኅበሚሰብ ዓምዶቜን ማለትም ደኅንነትንና ሰላምን ያጣሉ፤ ሰላምና ደኅንነት ሰጠፋ ማኅበሚሰቡ ዚጉልበተኞቜ መጫወቻ ሆኖ ይደናበራል፤ ይህ አደገኛ ጉዞ ነው፤ መልካም አስተዳደር ኹሰፈነ ሜብርተኛነት ዚሚበቅልበት መሬት አያገኝም፤ ሰዎቜ ሁሉ በሰውነታ቞ውና በዜግነታ቞ው እኩልነት ሰብአዊ መብቶቻ቞ው ሁሉ ኚተኚበሩላ቞ው ወደኃይል እርምጃ ዚሚወስደውን መንገድ ዚሚኚተሉበት ምክንያት ዹለም፤ እድገት ዚነጻነትና ዚዎሞክራሲ ውጀት ነው፤ ነጻነት ዹሰው ልጆቜ ሁሉ ዓላማ ነው፡፡

ማንም ቢሆን ኹሕግ በታቜና ለሕግ ተገዢ መሆን አለበት፤ ሕገ መንግሥቱን ለእሱ እንደሚበጀው እያደሚገ በመተርጎም በሥልጣን ላይ መቆዚት አይቻልም፤ ሊፈቀድም አይገባም፤ በአጠቃላይ አባማ በአፍሪካ ኅብሚት በአደሹገው ንግግር ዚአፍሪካ ገዢዎቜን ሁሉ ቁስላ቞ውን በአልኮል ሲያጥብላ቞ው እዚለበለባ቞ው ተመልክተውታል፤ አዳምጠውታል፤ አንዳንዶቹም እያፈሩ አጚብጭበውለታል፡፡

ዹዚህ ንግግር ዚመጚሚሻው ግብ ያልገባ቞ው ዚአፍሪካ ገዢዎቜ ክፉ ነገር ይጠብቃ቞ዋል፤ በሜብርተኛነት መነገድ መልኩን ሊለውጥ ነው፤ ካላወቁበት ዚማያውቁት ሜብር ቀታ቞ውን ይጠርግላቾዋል!

Tuesday, 21 July 2015

ዹተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮቜ መቃወሚያ ውድቅ ተደሹገ


• ለነሀሮ 14/2007 ዓ.ም ለብይን ተቀጥሚዋል
በነገሹ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

በእነ ዘላለም ወርቃገኘው ዚክስ መዝገብ ኹ1-6ኛ እንዲሁም ዹ9ኛ ተኚሳሟቜ ጠበቃ ዚሆኑት ተማም አባቡልጉ በደንበኞቻ቞ው ላይ በቀሚበባ቞ው ዚክስ ማስሚጃ ላይ ያቀሚቡት ባለ 10 ገፅ መቃወሚያ በፍርድ ቀቱ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ ተደርጓል፡፡ ጠበቃው ተኚሳሟቹ ሀምሌ 1/2006 ዓ.ም ተይዘው ኚሶስት ወር በኋላ ጥቅምት 7/2006 ዓ.ም ኚብሄራዊ መሹጃና ደህንነት ተገኘ ዚተባለ መሹጃ ኚአቃቀ ህግ ማስሚጃዎቜ ማስሚጃ ዝርዝርነት እንዲወጣ፣ ተኚሳሟቹ ለፖሊስ መሹጃ ዚሰጡበት መንገድና ፖሊስ ዚሰነድ ማስሚጃዎቜን ዚያዘበትን መንገድም አቃቀ ህግ ህጋዊ መሆኑን ስላላሚጋገጠ በደንበኞቌ ላይ በማስሚጃነት እንዳይያዝ ሲሉ መቀወወሚያ አቅርበው ነበር፡፡

ኚተኚሳሟቹ መካኚል በዛሬው ቜሎት አንደኛ ተኚሳሜ ዘላለም ወርቃገኘሁ ‹‹áˆ˜á‰ƒá‹ˆáˆšá‹«á‹ ዹቀሹበው ኚተኚሳሟቜ እጅ ተገኙ ዚተባሉት ማስሚጃዎቜ በህጋዊ መንገድ ዹተገኙ ስለመሆና቞ው አቃቀ ህግ በማስሚጃ ስላላሚጋገጠ ነው›› ሲል ፍርድ ቀቱ መቃወሚያውን እንዲቀበለው ጠይቋል፡፡ ሆኖም ዛሬ ሀምሌ 14/2007 ዓ.ም በልደታ ፍርድ ቀት 19ኛ ወንጀል ቜሎት መቃወሚያውን ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጎታል፡፡ በሌላ በኩል ፍርድ ቀቱ ተኚሳሟቹ በነፃ ይሰናበቱ ወይንም ይኚራኚሩ ዹሚለውን ለመወሰን ለብይን ለነሀሮ 14/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

በዘላለም ወርቃገኘሁ ዚክስ መዝገብ ኹ1-6ኛ እንዲሁም 9ኛ ተኚሳሟቜ ጠበቃ ዚሆኑት ተማም አባቡልጉ ኚጥብቅና በመታገዳ቞ው ምክንያት ሰባቱም ተኚሳሟቜ በዛሬው ቜሎት ያለ ጠበቃ ቀርበዋል፡፡ በዚህ መዝገብ ተኹሰው አቶ ተማም መቃወሚያ ካቀሚቡላ቞ው መካኚል አቶ ዚሞዋስ አሰፋ፣ አቶ አብርሃ ደስታ፣ አቶ ሀብታሙ አያሌውና አቶ ዳንኀል ሺበሜ ይገኙበታል፡፡

Thursday, 16 July 2015

Newly-freed Ethiopian Journalist Vows to Continue Work

Reeyot Alemu, an Ethiopian journalist who was unexpectedly released from prison last week after being convicted on terrorism charges, vows to continue her work as a reporter.Reeyot Alemu is a budding Ethiopian poet, essayist, and journalist.
“I am sure I will continue my writings because it’s my job, and also its my passion to write,” she said. “And also I want to serve my country. I want to make Ethiopia a democratic country, it is my responsibility as a citizen and as a journalist also.”
Reeyot had spent four years and 17 days in prison after a conviction many believe was a result of her articles which criticized the Ethiopian government.
She believes that her writings may lead to future imprisonment, as she does not believe this government allows anyone to live safely in Ethiopia while opposing those in power.
In 2011, Reeyot was arrested and then sentenced to 14 years in prison, which was reduced to five years after appeal. Her release last week came one day after five other imprisoned journalists and bloggers were released unannounced.
During most of her imprisonment, Reeyot shared one room with four other prisoners. The most difficult part, she says, was not not being able to receive visitors while dealing with a breast tumor.
“They denied my rights to be visited by my friends, my legal advisors. Even with my sister, they allow her these two months,” she lamented. “Before that for one year and eight months, even I did not see my sister. Only my parents, my mother and my father.”
Her father is also her lawyer, but during visitations they were not allowed to discuss legal matters.
While in prison, she says there were many offers for early release under the condition that she would agree to sign a letter admitting her wrongdoings or falsely accusing others. Reeyot refused and as a result, was ordered to spend another 11 months in prison.
These days Reeyot’s house is filled friends, family and other visitors welcoming her back. Next week she will go for a medical check up to continue treatment for her breast tumor.
Reeyot also plans on doing what she missed very much – reading books on political issues.
“I want to read how this country is, about the world,” she explained. “Because these four years I did not know, I did not get many information.”
Many international organizations continuously pressured the Ethiopian government to release the imprisoned journalists. The country has been frequently criticized by human rights organizations for repressing dissident voices.
The Committee to Protect Journalists says Ethiopia is Africa’s second worst journalist jailer with 11 other journalists and bloggers still imprisoned.
On social media, some people commented that the decision to release the journalists is linked to the visit of U.S. President Barack Obama to Ethiopia later this month.

ፍርድ ቀቱ አቶ አንዳርጋ቞ው ፅጌ ዚመኚላኚያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ወሰነ

ዚልደታ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት አቶ አንዳርጋ቞ው ፅጌ በእነ ዘመነ ካሎ መዝገብ ኹ2ኛ እስኚ 5ኛ ድሚስ ለተጠቀሱት ተኚሳሟቜ ዚመኚላኚያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ወሰነ፡፡ ዚፌደራል አቃቀ ህግ ‹‹áŠšáŠ áŠ•á‹³áˆ­áŒ‹á‰žá‹ ጋር በአካል ተገናኝታቜኋል›› ዹሚል ክስ ዚመሰሚተባ቞ው ተኚሳሟቹ ‹‹áŠšáŠ áŠ•á‹³áˆ­áŒ‹á‰žá‹ ጋር ተገናኝታቜኋል ኚተባለ አቶ አንዳርጋ቞ው ኢትዮጵያ ውስጥ ታስሚው ዹሚገኙ በመሆናቾው መኚላኚያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ፍርድ ቀቱ ይታዘዝልን›› ዹሚል ጥያቄ ማቅሚባ቞ው ይታወሳል፡፡

ዚፌደራል አቃቀ ህግ በበኩሉ አቶ አንዳርጋ቞ው ፅጌ በእነ ጀኔራል ተፈራ ማሞ መዝገብ እና በእነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ መዝገብ ላይ ክስ ቀርቊባ቞ው በእድሜ ልክና በሞት እንዲቀጡ ተወስኖባ቞ው ዚህዝባዊ መብታ቞ው ዚተሻሚ በመሆኑ በምስክርነት ሊቀርቡ አይቜሉም ብሎ ተቃውሟል፡፡ ዚአቶ አንዳርጋ቞ው ፅጌ ህዝባዊ መብት በመሻሩ ለፍርድ ስራ ልዩ አዋቂ ወይንም ነባሪ ሆነው መስራት አይቜሉም ያለው ዚፌደራል አቃቀ ህግ አቶ አንዳርጋ቞ው ፅጌ በተጚማሪ ምስክርነት ቀርበው መመስኚር አይገባ቞ውም ሲል ዚተኚሳሟቹ ጥያቄ ውድቅ እንዲሆን ለፍርድ ቀቱ አመልክቶ ነበር፡፡

ሆኖም ፍርድ ቀቱ ተኚሳሟቹ አቶ አንዳርጋ቞ው እንዲቀርቡላ቞ው ዚጠዚቁት ለዋስት አሊያም ልዩ አዋቂ ምስክር ሆነው ሳይሆን ነበሩበት ዚተባለውን ጉዳይ ለመናገር ለምስክርነት በመሆኑ፣ ምስክርነትም ግዎታ እንጅ መብት በመሆኑ ሰኞ ሰኔ 13/2007 ዓ.ም በእነ ዘመነ ካሎ መዝገብ ለተኚሰሱት ተኚሳሟቜ ልደታ ፍርድ ቀት ቀርበው እንዲመሰክሩ ወስኗል፡፡ ተኚሳሟቹ አቶ አንዳርጋ቞ው ዚት እንደሚገኙና ማዘዢያው ዚት ተብሎ ሊፃፍላቾው እንደሚገባ ተጠይቀው ለቃሊቲ ማሚሚያ ወይንም ለፀሹ ሜብር ግብሚ ኃይል ሊጻፍላ቞ው እንደሚገባ፣ ካልቀሚቡላ቞ውም ክሳ቞ው ኚአቶ አንዳርጋ቞ው ፅጌ ጋር ዹተገናኘ በመሆኑ አቶ አንዳርጋ቞ው በመኚላኚያ ምስክርነት እንዲቀርቡ እስኚ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድሚስ አቀቱታ እንደሚያቀርቡ ገልጾዋል፡፡

ተኚሳሟቹ አቶ አንዳርጋ቞ው ፅጌ በመኚላኚያ ምስክርነት እንዲቀርቡላ቞ው በጠዚቁበት ወቅት በዳኞቜና በአቃቀ ህጎቜ ላይ ኹፍተኛ ድንጋጀ መፈጠሩንና ኚአቶ አንዳርጋ቞ው ይልቅ ሌሎቜ መኚላኚያ ምስክሮቜን ማቅሚብ እንደሚቜሉ፣ አቶ አንዳርጋ቞ውን በመኚላኚያ ምስክርነት ለማቅሚብ መሞኹር እንደሌለባ቞ው እንደገለፁላ቞ው ታውቋል፡፡ ዳኛው በድንጋጀ ‹‹áŠ¥áŠ› እዚህ ጉዳይ ላይ ዚለንበትም›› ማለታ቞ውን ተኚሳሟቹ ቂሊንጩ ማሚሚያ ቀት ውስጥ ላነጋገራ቞ው ዹነገሹ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ገልጞውለታል፡፡
በነገሹ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

Wednesday, 15 July 2015

Rights groups press Obama to meet activists on trip to Kenya and Ethiopia

President Obama pauses as he speaks

The groups voiced concerns about “grave and worsening human rights challenges” in the two countries.

MORE than 50 African and global human rights groups on Tuesday called on US President Barack Obama to publicly meet democracy activists when he visits Ethiopia and Kenya later this month.



In a letter delivered to the White House, groups welcomed Obama’s planned visit but voiced concerns about “grave and worsening human rights challenges” in his host countries.
Signatories included a host of African non-governmental groups as well as Human Rights Watch, Freedom House, the Open Society Foundation and the Robert F. Kennedy Human Rights Center.
“We believe it imperative that you take the opportunity of your visits to meet publicly with pro-democracy and human rights activists,” the letter said.

Citing the arrest of six bloggers in Ethiopia—five of whom have recently been released—and sanctions against two Kenyan human rights groups, the signatories described a “shrinking civic space” in both countries.

Obama’s willingness to meet activists, they said, would afford the groups protection and send a message that Washington stands with them.

Obama is due to visit Ethiopia later this month as well as Kenya, where his father was born.
A presidential visit to Kenya had been put on ice while President Uhuru Kenyatta faced charges of crimes against humanity for his role in 2007-2008 post-election violence.
The International Criminal Court has since suspended that prosecution, citing a lack of evidence and Kenya’s failure to cooperate.

Human rights groups have criticised the Kenya trip, but have also questioned why Obama is visiting Ethiopia so soon after a contested election, which saw the ruling party win all parliamentary seats.
The White House stressed that it frequently addresses issues of democracy and political rights with countries in the region.

Source: Mail & Guardian Africa

Tuesday, 14 July 2015

ሰማያዊ ኚምርጫ ማግስት እዚተወሰደ ያለው እስርና ግድያ እንዲቆም ጠዹቀ

ሰማያዊ ፓርቲ ኹ2007 ሀገራዊ ‹‹á‹šá‹áˆžá‰µ ምርጫ›› ማግስት በገዥው አካል እዚተወሰደ ዹሚገኘው ግድያ፣ እስር፣ ኚስራ ማፈናቀል፣ ማሾማቀቅና ድብደባ በአስ቞ኳይ እንዲቆም ጠዹቀ፡፡

ፓርቲው ዛሬ ሐምሌ 7/2007 ዓ.ም ‹‹á‹šá‹ˆáˆˆá‹°á‹áŠ• ዚሚሳ ብሶት ዹወለደው ስርዓት! ዚዘመቻ እስርና ግድያ ተጠናክሮ ቀጥሏል!›› በሚል በጜ/ቀቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እዳመለኚተው፣ ምርጫው ኚተጠናቀቀበት ግንቊት 16 ቀን 2007 ዓ.ም ማግስት በምርጫው በንቃት ይሳተፉ ዚነበሩና በአስተሳሰባ቞ው በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያላ቞ውን ዜጎቜ በማንአለብኝነት መደብደብ፣ ኚሰራ ማፈናቀል፣ ማሰር፣ ማሾማቀቅና መግደል ዹአገዛዙ ዋና መገለጫ ሆኗል፡፡

ሰማያዊ በመግለጫው ‹‹á‰ áˆ°áˆ‹áˆ›á‹Š መንገድ ዚሚታገሉ ዹሰማዊ፣ ዚመኢአድ፣ ዚቀድሞው አንድነት፣ ዚመድሚክና ዚሌሎቜም ዚፖለቲካ ፓርቲ አባላት በተለዬ ኢላማ ተጠምደው እዚተሳደዱ፣ እዚተደበደቡና በጅምላ እዚታሰሩ አለፍ ሲልም በአሰቃቂ ሁኔታ እዚተገደሉ ይገኛሉ›› ሲል ገልጟአል፡፡


አሁን በገዥው አካል እዚተወሰደ ያለው ድርጊት ዜጎቜ በሰላማዊ መንገድ ለውጥ እናመጣለን ዹሚለውን አስተሳሰባ቞ውን ዚሚያጚልምና ዹሰላማዊ ትግል አቀንቃኞቜን አንገት ዚሚያስደፋ ይዋል ይደር እንጅ መዘዙም ለማንም ወገን በተለይም ለገዥው መደብ ዹማይጠቅም መሆኑንም ፓርቲው በመግለጫው አስገንዝቧል፡፡


‹‹á‹šáŠ áˆáŠ“á‹ ስርዓት ብዙ ዓይነት አስተሳሰብና ልዩነት ባለባት ኢትዮጵያ ምርጫን መቶ በመቶ አሾንፌአለሁ ቢልም ሃቁ ግን ዚዲሞክራሲና ዚመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግብዓተ መሬት እዚተቃሚበ መምጣቱን ዚሚያሳይ ነው፡፡ ይህንን እውነታ ገዥው ቡድንም ዹማይክደው መሆኑን በምርጫው ማግስት ጀምሮ ዚተዘፈቀበት ህዝብን እንደጊር ዚመፍራት አባዜው ገሃድ አድርጎታል›› በሏል ፓርቲው በመግለጫው፡፡ 


ሰማያዊ ፓርቲ ገዥው አካል ኹሚፈፅማቾው ህገ ወጥና ዹማን አለብኝነት ተግባሩ እንዲቆጠብ፣ ዚዜጎቜ ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶቜ እንዲኚበሩ ደጋግሞ መጠዹቁን አስታውሶ፣ አሁንም ይህ አይነቱ ህገ-ወጥና ዚማንአለብኝነት ድርጊት በአስ቞ኳይ እንዲቆም ጠይቋል፡፡ 


መግለጫውን ዚሰጡት ዚፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት እንደተናገሩት አሁን ያለው ትግል ‹‹áŠšáŠ áŒˆá‹›á‹ ወደ ዎሞክራሲ ዹሚደሹግ ዚነጻነት ትግል›› ነው፡፡
በመጚሚሻም ፓርቲው ሕዝብ ዚስልጣን ባለቀትነቱን እንዲያሚጋግጥ በሚያደርገው ትግል ሁሉ ኹጎኑ እንዲሰለፍ ጥሪውን አቅርቧል፡፡


Sunday, 12 July 2015

“ዚኢትዮጵያ ህግ ልዕልና ኚአሜሪካ ፕሬዘዳንት ክብር በላይ ሊሆን ይገባዋል” – በስደት ኹሚገኙ ዚኢትዮጵያ ነጻ-ፕሬስ ጋዜጠኞቜ ዹተሰጠ መግለጫ

obama ethiopia







– በስደት ኹሚገኙ ዚኢትዮጵያ ነጻ-ፕሬስ ጋዜጠኞቜ ዹተሰጠ መግለጫ
ዚኢትዮጵያ ነጻ ፕሬስ ጋዜጠኞቜን “አሞባሪዎቜ” ብሎ በማሰር እና ኹአገር እንዲሰደዱ በማድሚግ ዚኢህአዎግ መንግስት ያላቋሚጠ ዚሰብአዊ መብት ጥሰቶቜን ሲፈጜም ቆይቷል። ይህን ዚሰብአዊ መብት መተላለፍ በመቃወም፤ በአገር ውስጥ እና በውጭ ዹሚገኙ ኢትዮጵያውያን ድምጜ ለሌላቾው ድምጜ በመሆን ወገናቾን ታድገዋል። ሃሳባ቞ውን በነጻነት በመግለጻ቞ው ብቻ፤ “አሞባሪ” ተብለው በእስር ሲማቅቁ ኚነበሩት ጋዜጠኞቜ እና ጊማርያን መካኚል ተስፋለም ወልደዚስ፣ ዘላለም ክብሚት፣ አስማማው ሀ/ጊዮርጊስ፣ ርዕዮት አለሙ፣ ማህሌት ፋንታሁን እና ኀዶም ካሳዬ ተፈትተዋል።

 áˆ™áˆ‰á‹áŠ• መግለጫ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2015/07/Press-Release.pdf